reporter issue 1334

80
ገጽ 1 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPRIT | ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ የእሑድ እትም የካቲት 3 ቀን 2005 ትኩስና ተጨማሪ መረጃዎችን በድረ ገጻችን ያገኛሉ www.ethiopianreporter.com ቅፅ 18 ቁጥር 25/1334 ጳጉሜን 6 ቀን 1987 ተመሠረተ ዋጋው ብር 10.00 ወደ ክፍል 1 ገጽ 42 ዞሯል የመከላከያ ሠራዊታችን ሕገ መንግሥታዊ ታማኝነትና ሕዝባዊ ባህርይ እንደተጠበቀ ይኑር! 2 ወደ ክፍል 1 ገጽ 41 ዞሯል በዮሐንስ አንበርብር የአገር መከላከያ ሚኒስቴር በሕገ መንግሥቱ ከተጣለበት የአገሪቱን ደኅንነት ማረጋገጥና ሕገ መንግሥቱን ማስከበር ተልዕኮው ውጪ፣ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ አገሪቱን ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለማሸጋገር ለተያዘው እንቅስቃሴ መሠረት እየጣለ መሆኑን ባዘጋጀው ዓውደ ርዕይ አሳየ:: የኢትዮጵያ መንግሥት በየዓመቱ የካቲት 7 የመከላከያ ሠራዊት ቀን ሆኖ እንዲከበር በወሰነው መሠረት፣ የመጀመርያው ዓመት የሠራዊቱ ቀን መከላከያ ሠራዊት የኢንዱስትሪ ሽግግር መሠረት መሆኑን አሳየ ‹‹ከከሸፈው መፈንቅለ መንግሥት በኋላ በኤርትራ ያለውን ሁኔታ በጥብቅ እየተከታተልን ነው›› የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም ኢሕአዴግ ለአዲስ አበባ ምርጫ አምስት ከፍተኛ ባለሥልጣናትን አቀረበ የትራንስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ድሪባ ኩማ ቀጣዩ ከንቲባ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል ... በዮሐንስ አንበርብር በኤርትራ መከላከያ ሠራዊት ጥቂት አባላት ተሞክሮ ከሸፈ የተባለውን መፈንቅለ መንግሥት ተከትሎ በአገሪቱ ሊፈጠር የሚችለውን ፖለቲካዊ ሁኔታ በጥብቅ እየተከታተሉት መሆኑን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ገለጹ:: ሚኒስትሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ባለፈው ሐሙስ ያቀረቡ ቢሆንም፣ ሪፖርታቸው ግን ከሁለት ሳምንታት በፊት በኤርትራ ስለተከናወነው ድንገተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ያለው ነገር የለም:: በኤርትራ የተሞከረው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ከሚኒስቴሩ የስድስት ወራቱ የሥራ ክንውን ወቅት በኋላ የተፈጸመ በመሆኑ በሚኒስትሩ ሪፖርት ውስጥ ሊካተት ባይችልም፣ ከምክር ቤቱ አባላት ግን ሚኒስቴር መሥርያ ቤቱ ለጉዳዩ ስለሰጠው ትኩረትና እስካሁን በዚህ ዙሪያ የተሠራውን እንዲያብራሩ ተጠይቀዋል:: ‹‹በኤርትራ ያለውን ሁኔታ በጥብቅ እየተከተለን መሆኑን ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ፤›› ያሉት ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ፣ ከከሸፈው መፈንቅለ መንግሥት በኋላ በአገሪቱ ያለው ፖለቲካዊ ሁኔታ ምን ይመስላል? ለኢትዮጵያና ለአካባቢው አገሮች ያለው እንደምታ ምንድነው? ወዴት አቅጣጫ ሊያመራ ይችላል? የሚለውን በዝርዝርና በመረጃ ላይ በመመሥረት እየተከታተሉ መሆኑን አስረድተዋል:: ‹‹ይህንን መሠረት በማድረግም ዕርምጃችንን እያስተካከልን እንሄዳለን፤ ምክንያቱም ለእኛም የሚተርፍ ነገር ፎቶ በሪፖርተር/ናሆም ተስፋዬ አቶ ድሪባ ኩማ ዝርዝሩን በገጽ 42 ይመልከቱ አቶ ተፈራ ደርበው አቶ ሲራጅ ፈጌሳ አቶ መኩርያ ኃይሌ አቶ ወርቅነህ ገበየሁ የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ወሳኝ ፕሮጀክቶች በኃላፊነት እየሠራ ነው አዲሶቹን ባቡሮች መገጣጠምና የማዳበሪያ ፋብሪካ ጥቂቶቹ ናቸው ሰው አልባ አውሮፕላን ገጣጥሞ ታጥቋል በመከላከያ ዓውደ ርዕይ ላይ ከግራ ወደ ቀኝ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ብርጋዴር ጄኔራል ክንፈ ዳኘው፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም፣ የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ካሳ ተክለ ብርሃን፣ ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹም ጄኔራል ሳሞራ የኑስና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደኅንነት አማካሪ አቶ ፀጋዬ በርኼ ተገኝተው ነበር

Upload: fiker-konjo

Post on 01-Nov-2014

364 views

Category:

Documents


0 download

DESCRIPTION

Jornal

TRANSCRIPT

Page 1: Reporter Issue 1334

ገጽ 1 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005

FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPRIT | ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ

የእሑድ እትም

የካቲት 3 ቀን 2005 ትኩስና ተጨማሪ መረጃዎችን በድረ ገጻችን ያገኛሉ www.ethiopianreporter.com

ቅፅ 18 ቁጥር 25/1334 ጳጉሜን 6 ቀን 1987 ተመሠረተ ዋጋው ብር 10.00

ወደ ክፍል 1 ገጽ 42 ዞሯልየመከላከያ ሠራዊታችን ሕገ መንግሥታዊ ታማኝነትና

ሕዝባዊ ባህርይ እንደተጠበቀ ይኑር!

2

ወደ ክፍል 1 ገጽ 41 ዞሯል

በዮሐንስ አንበርብር

የአገር መከላከያ ሚኒስቴር በሕገ መንግሥቱ ከተጣለበት የአገሪቱን ደኅንነት ማረጋገጥና

ሕገ መንግሥቱን ማስከበር ተልዕኮው ውጪ፣ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ አገሪቱን ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለማሸጋገር ለተያዘው እንቅስቃሴ መሠረት እየጣለ መሆኑን ባዘጋጀው ዓውደ ርዕይ አሳየ::

የኢትዮጵያ መንግሥት በየዓመቱ የካቲት 7 የመከላከያ ሠራዊት ቀን ሆኖ እንዲከበር በወሰነው መሠረት፣ የመጀመርያው ዓመት የሠራዊቱ ቀን

መከላከያ ሠራዊት የኢንዱስትሪ ሽግግር መሠረት መሆኑን አሳየ

‹‹ከከሸፈው መፈንቅለ መንግሥት በኋላ በኤርትራ ያለውን ሁኔታ በጥብቅ እየተከታተልን ነው››የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም

ኢሕአዴግ ለአዲስ አበባ ምርጫ አምስት ከፍተኛ ባለሥልጣናትን አቀረበየትራንስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ድሪባ ኩማ ቀጣዩ ከንቲባ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል

...

በዮሐንስ አንበርብር

በኤርትራ መከላከያ ሠራዊት ጥቂት አባላት ተሞክሮ ከሸፈ የተባለውን መፈንቅለ መንግሥት ተከትሎ በአገሪቱ ሊፈጠር የሚችለውን ፖለቲካዊ ሁኔታ በጥብቅ እየተከታተሉት መሆኑን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ገለጹ::

ሚኒስትሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ባለፈው ሐሙስ ያቀረቡ ቢሆንም፣ ሪፖርታቸው ግን ከሁለት ሳምንታት በፊት በኤርትራ ስለተከናወነው ድንገተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ያለው ነገር የለም::

በኤርትራ የተሞከረው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ከሚኒስቴሩ የስድስት ወራቱ የሥራ ክንውን ወቅት በኋላ የተፈጸመ በመሆኑ በሚኒስትሩ ሪፖርት ውስጥ ሊካተት ባይችልም፣ ከምክር ቤቱ አባላት ግን ሚኒስቴር መሥርያ ቤቱ ለጉዳዩ ስለሰጠው ትኩረትና እስካሁን በዚህ ዙሪያ የተሠራውን እንዲያብራሩ ተጠይቀዋል::

‹‹በኤርትራ ያለውን ሁኔታ በጥብቅ እየተከተለን መሆኑን ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ፤›› ያሉት ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ፣ ከከሸፈው መፈንቅለ መንግሥት በኋላ በአገሪቱ ያለው ፖለቲካዊ ሁኔታ ምን ይመስላል? ለኢትዮጵያና ለአካባቢው አገሮች ያለው እንደምታ ምንድነው? ወዴት አቅጣጫ ሊያመራ ይችላል? የሚለውን በዝርዝርና በመረጃ ላይ በመመሥረት እየተከታተሉ መሆኑን አስረድተዋል:: ‹‹ይህንን መሠረት በማድረግም ዕርምጃችንን እያስተካከልን እንሄዳለን፤ ምክንያቱም ለእኛም የሚተርፍ ነገር

ፎቶ በ

ሪፖርተ

ር/ናሆ

ም ተ

ስፋዬ

አቶ ድሪባ ኩማዝርዝሩን በገጽ 42 ይመልከቱ

አቶ ተፈራ ደርበው አቶ ሲራጅ ፈጌሳ አቶ መኩርያ ኃይሌ አቶ ወርቅነህ ገበየሁ

የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ወሳኝ ፕሮጀክቶች በኃላፊነት እየሠራ ነው አዲሶቹን ባቡሮች መገጣጠምና የማዳበሪያ ፋብሪካ ጥቂቶቹ ናቸው ሰው አልባ አውሮፕላን ገጣጥሞ ታጥቋል

በመከላከያ ዓውደ ርዕይ ላይ ከግራ ወደ ቀኝ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ብርጋዴር ጄኔራል ክንፈ ዳኘው፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም፣ የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ካሳ ተክለ ብርሃን፣ ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹም ጄኔራል ሳሞራ የኑስና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደኅንነት አማካሪ አቶ ፀጋዬ በርኼ ተገኝተው ነበር

Page 2: Reporter Issue 1334

ገጽ 2 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005

በጳጉሜን 6 1987 ተጀመረ በሳምንት ሁለት ጊዜ የሚታተም አድራሻ፡- ከቦሌ መድኃኒዓለም ወደ ብራስ ሆስፒታል በሚወስደው መንገድ ከቦሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል አጠገብ ስልክ 0910-885206/ 011-661 61 79/85/87/011-8614339 ፋክስ: 011-661 61 89

አድራሻ፡- ቦሌ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 03 የቤት ቁጥር 2347 ፖስታ 7023 አ.አ ኢትዮጵያ

ማስታወቂያ ሽያጭና ስርጭት 0910 885206/ 011 6 61 61 79/ 85

[email protected] E-mail: [email protected]

Website: www.ethiopianreporter.com

ዋና ሥራ አስኪያጅ፡ አማረ አረጋዊማኔጂንግ ኤዲተር፡ መላኩ ደምሴዋና አዘጋጅ፡ ዘካሪያስ ስንታየሁየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09/11/12 የቤት ቁ. 217

ከፍተኛ አዘጋጅ፡ ዳዊት ታዬ አዘጋጆች፡ ሔኖክ ያሬድ ጌታቸው ንጋቱ

ምሕረት ሞገስ ኃይሌ ሙሉ

ረዳት አዘጋጆች፡ ታደሰ ገ/ማርያም ምሕረት አስቻለው ታምሩ ጽጌ የማነ ናግሽ

ዋና ግራፊክ ዲዛይነር፡ ይበቃል ጌታሁንከፍተኛ ግራፊክ ዲዛይነር፡ ቴዎድሮስ ክብካብግራፊክ ዲዛይነሮች፡ ፀሐይ ታደሰ ፋሲካ ባልቻ እንዳለ ሰሎሞን ስሜነህ ሲሳይ ቢኒያም ግርማ ነፃነት ያዕቆብ ቤዛዬ ቴዎድሮስ

ዋና ፎቶ ግራፈር ናሆም ተሰፋዬፎቶ ግራፈሮች፡ ታምራት ጌታቸው መስፍን ሰሎሞን

ካርቱኒስት፡ ኤልያስ አረዳ

በሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር (ኤም.ሲ.ሲ) ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር

እየታተመ የሚወጣ ጋዜጣ

ከፍተኛ ሪፖርተሮች፡ ደረጀ ጠገናው ብርሃኑ ፈቃደ ውድነህ ዘነበ፣ ሰለሞን ጎሹሪፖርተር፡ ምዕራፍ ብርሃኔማርኬቲንግ ማናጀር፡ እንዳልካቸው ይማምሴልስ፡ ቤዛዊት ፀጋዬ' Hና Ó`T' w\¡ S<K<Ñ@�' IK=ና ከuደ፣ ብሩክ ቸርነትማስታወቂያ ፕሩፍሪደር፡መሳይ ሰይፉ፤ ኤፍሬም ገ/መስቀል፤ ዳዊት ወርቁኮምፒውተር ጽሑፍ፡ ብርቱካን አባተ፣ ሄለን ይታየው፣ ፍሬሕይወት ተሰማ፣ ማስታወቂያ ፅሁፍ እስከዳር ደጀኔ፣ መሠረት ወንድሙ፣ ራሔል ሻወልሕትመት ክትትል፡ ተስፋዬ መንገሻ፣ የየሱስወርቅ ማሞ፣ ገዛኸኝ ማንደፍሮዌብ ሳይት፡ ቤዛዊት ተስፋዬ፣ ቢኒያም ሐይሉ

ርእሰ አንቀጽ

እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005

ማስታ

ወቂያ

የመከላከያ ሠራዊታችን ሕገ መንግሥታዊ ታማኝነትና ሕዝባዊ

ባህርይ እንደተጠበቀ ይኑር!ሰሞኑን የኢፌዲሪ የመከላከያ ሠራዊት ቀን እየተከበረ ነው:: የበዓሉ ዋነኛ መሪ ቃል መልዕክትና

መግለጫም ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ታማኝነታችንና ሕዝባዊ ባህሪያችን እንደተጠበቀ ይኖራል!›› የሚል ነው:: መሆን ያለበት መልዕክትና መግለጫም በዋነኛነት እሱ ብቻ በመሆኑ፣ እኛም የመከላከያ ሠራዊታችን ሕገ መንግሥታዊ ታማኝነትና ሕዝባዊ ባህርይ እንደተጠበቀ ይኑር እንላለን::

እንደ ኢትዮጵያዊነት በግልጽና በሀቅ እንነጋገር ከተባለ ኢትዮጵያ ካሉዋት አስተማማኝ ተቋማት አንዱ የመከላከያው ተቋም ነው:: የመከላከያ ሠራዊት ነው:: ይህ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳንሆን፣ አፍሪካዊያን ብቻ ሳይሆኑ፣ ዓለምም በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) በኩል ይተማመንበታል:: በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሥነ ምግባርና አቅም እምነት እንዳለው በተደጋጋሚ ገልጿል::

በአፍሪካ ሰላም የማስከበር ተልዕኮ ሲኖር ቅድሚያ የሚሰጠው ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ነው:: በሱዳን፣ በላይቤሪያ፣ በሩዋንዳና በብሩንዲ ለሰላም ማስከበር የተመረጠው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ነው::

ሌላው ቀርቶ ደቡብ ሱዳንና ሱዳን ጦርነት ውስጥ ገብተው እንኳ ለአስታራቂነት አገር ምረጡ ሲባሉ በኢትዮጵያ አስታራቂነት ነው የተስማሙት:: ሰላም አስከባሪ ኃይል ይላክ ሲባልም ሁለቱም ተፋላሚ አገሮች የተቀበሉት የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትን ነው:: በሁለት ተፋላሚ አገሮች ታማኝነትን ማግኘት እጅግ ከባድ ነው:: ሠራዊታችን ግን አግኝቷል::

የሰላም አስከባሪ ኃይሎች ተብለው ወደ ተለያዩ አገሮች የሚሰማሩ የተለያዩ አገሮች የመከላከያ ሠራዊት አባላት በርካታ ስህተቶችና ወንጀሎች በመፈጸምና የሥነ ምግባር ጉድለቶችን በማሳየት ሲከሰሱ ይደመጣል:: የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት ግን ሰላም ለማስከበር በሄዱበት አገር ሰረቁ፣ ዘረፉ፣ አመፁ፣ ደፈሩ፣ ጨፈጨፉ፣ ወዘተ በመባል ሲወቀሱና ሲከሰሱ አልተሰማም:: ፈጽሞ አልተደረገምና:: ሕዝባዊ ባህርይ ሲባልም ይህ ማለት ነው::

የመከላከያ ሠራዊት ሲቋቋም የውጭ ወራሪን ለመከላከልና ሉዓላዊነትን ለማስከበር ነው:: ግን ይህ ብቻ በቂ አይደለም:: ሕገ መንግሥትን ለማስከበርና ለሕገ መንግሥት ታማኝነት ያለው ተግባር ለመፈጸምም ነው:: የመከላከያ ሠራዊቱ በዚህም የሚያኮራ ሥራ እየሠራ ነው:: በብዙ የአፍሪካ አገሮች በመከላከያ ሠራዊት አማካይነት አገር ሲታመስ የኢትዮጵያ ግን የማረጋጋት ሚና እየተጫወተ ይገኛል:: የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ መለስ ዜናዊ በሕመም ላይ በነበሩበት ጊዜና በሕልፈታቸውም ጊዜ የሚተካቸው ጠቅላይ ሚኒስትር በፓርላማ እስኪሰየም ድረስ ምንም ረብሻና ሁከት ያልነበረው፣ መከላከያ ሠራዊታችን ለሕገ መንግሥቱ ታማኝነቱን ለሕዝቡ ደግሞ ሕዝባዊ ባህርይ በማሳየቱ ነው::

ይህ ሕዝባዊ ባህርይና ሕገ መንግሥታዊ ታማኝነት ይበልጥ እየተጠናከረ መምጣት ይገባዋል:: በትጥቅ ትግሉ ጊዜ የነበረ ሕዝባዊ ባህርይ ይቀጥላል ተብሎ በመዝናናትና በመኩራራት ከመቀመጥ ይልቅ፣ በተተኪው ኃይልና አዲስ በሚቀላቀለው የመከላከያ ሠራዊት ዘንድ ማስቀጠል ተገቢ ነው:: ምንጊዜም ሕገ መንግሥታዊ ተገዥነትና ታማኝነት ከሕዝባዊ ባህርይና አገልጋይነት ጋር ተያይዞና ተቀናጅቶ እንዲቀጥል፣ ተከታታይ ሥልጠናና ትምህርት ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል:: ከፖለቲካ ድርጅት ጋር ተያይዞ የመጣውን የረዥም ጊዜ ተዋፅኦም ሙሉ በሙሉ በተመጣጠነ መንገድ ለማስኬድ፣ ልዩ ትኩረት እየሰጡ መጓዝ የግድ ይላል:: ምንጊዜም ሕገ መንግሥታዊ ታማኝነትና ሕዝባዊ ባህርይ ቋሚ ሆኖ እየተጠናከረ መቀጠል አለበት::

የመከላከያ ሠራዊታችን የምንኮራበት ሌላ ገጽታ አለው:: ሕገ መንግሥታዊ ታማኝነቱና ህዝባዊ ባህርይው እንዳለ ሆኖ የሚሊተሪ ዶክትሪን፣ ሳይንስ፣ ስትራቴጂውና ታክቲኩም በእጅጉ የሚደነቅ ነው:: በሶማሊያ በተካሄደው ውጊያ ወቅት ያሳየው አቅምና ያገኘው ድል፣ በሻዕቢያ ላይ ቀደም ብሎ ያስመዘገበው አሸናፊነት፣ በቅርቡ በሻዕቢያ ተተናኳሽ ኃይል ላይ የወሰደው ቅፅበታዊ ዕርምጃና ውጤት የሚደነቅ ነው:: ይህ ተግባር ሲታይ መከላከያ ሠራዊታችን የታማኝነትና የሕዝባዊነት ብቻ ሳይሆን፣ የጥበብና የሳይንስ አቅሙም እጅግ የሚደነቅና በዓለም ደረጃ ከፍተኛ ሥፍራ ሊሰጠው የሚገባ መሆኑን ነው:: በዚህም እንኮራለን::

የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ሌላ ታሪካዊ ገጽታም እያሳየ ነው:: ወደ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ እየገሰገሰ ያለ ሠራዊት ነው:: የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ወደ መሠረታዊ ቴክኖሎጂ እየገባ ነው:: ለራሱ ለመከላከያው ሠራዊት የሚጠቅም መሣሪያ እየሠራና መለዋወጫ እያመረተ ነው:: በአውቶሞቢል መገጣጠሚያና ተያያዥነት ባለው ቴክኖሎጂ ላይም እንቅስቃሴ እያደረገ ነው:: በእንደዚህ ዓይነት ጉዞው ከቀጠለ ለመከላከያ ሠራዊቱ የሚያስፈልገውን የውጊያ ቁሳቁስ ራሱ በብዛት ሊያመርት ይችላል:: ካላስፈላጊ ጥገኝነትም ሊላቀቅ ይችላል::

የመከላከያና የቴክኖሎጂ ተያያዥነት የታየው በኢትዮጵያ ብቻ አይደለም:: በሌሎች የበለፀጉ አገሮችም በስፋት ይታያል:: በአሁኑ ጊዜ ኢንተርኔት የሲቪል ኩባንያዎች ሥራ ሆነ እንጂ፣ ኢንተርኔት የተጀመረው በመከላከያ ሠራዊት አካላት በአሜሪካ ውስጥ ነው:: ጥቅሙ እየጎላ ሲሄድ ነው ወደ ግሉ ዘርፍ የተዛመተው::

አሁንም በቴክኖሎጂና በሳይንስ ምርምሩ ይቀጥል፣ ይበርታ፣ ይበረታታ እንላለን:: እግረ መንገዳችንን ደግሞ ወደ ቴክኖሎጂ ሲገባ ‹‹ቢዝነስም›› አብሮ ሊመጣ ስለሚችል የመከላከያ ሠራዊታችን ሕገ መንግሥታዊ ታማኝነትና ሕዝባዊ ባህርይን የሚሸረሸሩ የቢዝነስ አሉታዊ ባህርያት እንዳይከሰቱም ጥንቃቄ ያድርግ እንላለን::

ከቴክኖሎጂው ጋር ተያይዘው በሚመጡ የቢዝነስ ባህርያት ምክንያት የግል ዘርፉን ማዳከም፣ ሙስናና ሕዝባዊ ባህርይን ማጣትና ሕግን መጋፋት እንዳይከሰቱ፣ ጥንቃቄ እየተደረገና ክትትል እየተደረገበት የሚሄድ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ዕድገት ጉዞ ይሁን እንላለን:: ኋላ ከመማቀቅ ከወዲሁ መጠንቀቅ እንላለን::

የመከላከያ ሠራዊት ሕዝባዊ ባህርይውን የሚያንፀባርቀው ውጊያ ሲኖር ብቻ አይደለም:: የተፈጥሮ አደጋ ማለትም ጎርፍ፣ ረሃብ፣ ድርቅና ሌሎች ችግሮች ሲከሰቱ የመከላከያ ሠራዊት ሕዝባዊ ወገናዊነቱን ያንፀባርቃል፣ ያስመሰክራል:: የመከላከያ ሠራዊታችንም እንዲህ ዓይነት አደጋዎች ሲኖሩ ከወገኑ ጋር ይቆማል:: የመከላከያ ሠራዊታችን በአደጋ ጊዜ ከሕዝብ ጋር ሲቆም ታይቷል፣ ተስተውሏል:: ይህም በደረጀ ሁኔታ ይቀጥል እንላለን::

አዎንታዊ ባህርያትን ስንገልጽ አብረን ለመግለጽ የምንወደው ነገርም አለ:: አዎንታዊ ባህርያት እንዳይሸረሸሩ እንጠንቀቅ እንላለን:: ሕገ መንግሥታዊ ታማኝነትና ሕዝባዊ ባህርይ እንዳይሸረሸር መንግሥትም እንደ መንግሥት፣ መከላከያ ኃይልም እንደ ተቋም ልዩ ትኩረት ሰጥተው ይንቀሳቀሱ እንላለን:: ያለንበት ዓለም ፈተናው ከባድ ነው:: ባለንበት አካባቢ ያለው የጠላት ፈተና እጅግ ከባድ ነው:: ፈተናው ከባድ በመሆኑ ታማኝነትና ሕዝባዊነት ምንጊዜም ይጠናከር ይቀጥል::

መልካም የመከላከያ ሠራዊት ቀን! እንኳን አደረሳችሁ!

Invitation for BidBid Ref No: AFDA-02/2013

Supply of HDPE Pipes

1. Action For Development (AFD), an Ethiopian Residents Charity, invites interested bidders to Supply HDPE Pipes for its project activity: Achi Algone Rural Water Supply Scheme, in Hamer Woreda, South Omo Zone, SNNPR as part of the project entitled “Recovery and Resilience Building in Hamer Woreda“ which is currently under implementation in partnership with Christian Aid/DEC.

2. Financing by: Christian Aid/ DEC3. Diameter & Quantity of HDPE Pipes: Pipe diameter - 90mm & Length - 5,100m of PN 6 & Pipe

diameter - 75mm & Length - 1,300m of PN 10;4. Eligible bidders are invited to take part in the bid upon submission of copies of renewed trade

license, Vat registration & tax payer’s identification certificates. 5. Bidding will be conducted through open local tender procedure.6. The bid document shall be collected from Action For Development, P.O.Box 19859, Tel 011 662

59 76, during office hours, as of the date of this notice.7. Interested bidders may obtain further information from Administration and Finance Department

of Action For Development, Tel 011 662 59 76/011 618 26 65, Fax 011 662 55 63.8. All bids must be accompanied by a bid bond amounting 1% of the total bid amount including

15% VAT, in the form of C.P.O or certified cheque. Bid bond in any other form shall not be acceptable.

9. All bids must be submitted to Action For Development, P. O. Box 19859, Tel 011 662 59 76 one original marked “ORIGINAL” and one copy signed in the same way as the original and marked “COPY” by stating the contract title - Supply of HDPE Pipes and Bid Ref. no. AFDA-02/2013, with wax-sealed envelope at or before 12:30 P.M. (noon) local time on 20th February, 2013. The technical and financial offer must be placed together in a sealed envelope.

10. Bids will be opened in the presence of bidders and/or their official representatives who wish to attend, on 20th February, 2013 local time.

11. Failure to comply with any of the conditions indicated above will result in automatic rejection.12. The Organization reserves the right to accept or reject any or all bids.

Action For Development

Page 3: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 3 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታ

ወቂያ

ወደ ክፍል-1 ገጽ 44 ዞሯል ወደ ክፍል-1 ገጽ 44 ዞሯል

ወደ ክፍል-1 ገጽ 44 ዞሯል

በዳዊት ታዬ

በኢትዮጵያ የፋይናንስ ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የግል ባንኮች ለተበዳሪዎች ከሚሰጡት ከእያንዳንዱ ብድር ለብሔራዊ ባንክ ቦንድ ግዥ ያዋሉት ገንዘብ 15 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተጠቆመ::

የሪፖርተር ምንጮች እንደገለጹት፣ ካለፈው ሁለት ዓመት ተኩል ወዲህ እያንዳንዱ ባንክ በሚያበድረው የብድር መጠን ልክ 27 በመቶ ለቦንድ ግዥው የሚያውለው ገንዘብ እየጨመረ ነው::

እስከ 2005 ዓ.ም. ግማሽ የበጀት ዓመት ድረስ የተሰባሰቡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት፣ ባንኮቹ ለቦንድ ግዥ ያዋሉትን ገንዘብ ማበደር ቢችሉ ኖሮ ከአንድ ቢሊዮን ብር ያላነሰ ትርፍ

ያገኙበት እንደነበር ጠቁመዋል::

እስካሁን ባለው መረጃ 27 በመቶው የቦንድ ግዥ ተግባራዊ ከተደረገ በኋላ፣ ከፍተኛውን የቦንድ ግዥ የፈጸመው አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ ነው:: እስከ በጀት ዓመቱ አጋማሽ ድረስ አዋሽ ባንክ 2.8 ቢሊዮን ብር የቦንድ ግዥ ፈጽሟል:: ከአዋሽ ቀጥሎም ዳሸን ባንክ በሁለተኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን መረጃዎች ያመለክታሉ::

የ27 በመቶ የቦንድ ግዥ የባንኮችን የማበደር አቅም እየገታ ነው ቢባልም፣ የባንኮች የብድር መጠን እየጨመረ ነው:: የ2005 ዓ.ም. የስድስት ወራት እንቅስቃሴያቸውን የሚያስረዳው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት፣ ሁሉም ባንኮች አትራፊ መሆናቸውና ተቀማጭ ገንዘባቸውን

የባንኮች የቦንድ ግዥ 15 ቢሊዮን ብር ደረሰ

የስድስት ወር አፈጻጸማቸው ዕድገት አሳይቷል

በጋዜጣው ሪፖርተር

የተለያዩ የሕክምና አገልግሎቶችን በመፈለግ ደረጃቸውን ወዳልጠበቁ የህንድ ሆስፒታሎች የሚያቀኑ ኢትዮጵያውያንን መንግሥት አስጠነቀቀ፡፡

ህንድ በርካታ ታዋቂ የሕክምና አገልግሎት መስጫ ተቋማት ቢኖራትም፣ አገሪቷ በጣም ትልቅ ከመሆኗ አንፃር በርካታ አነስተኛ የአገልግሎት መስጫ ተቋማትም ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም እነዚህ ደረጃቸው የማይታወቁና የሕክምና ጥራታቸውም

እምብዛም የሆኑት ተቋማት፣ የአፍሪካን ገበያን ለመቆጣጠር በሚል ደላሎችን ወደተለያዩ የአፍሪካ አገሮች እንደሚልኩ መንግሥት አስታውቋል፡፡

አብዛኛዎቹ ሆስፒታሎች በዋጋ ርካሽነት የሚመረጡ፣ ደረጃቸውን ያልጠበቁና ከዋና ከተሞች ርቀው የሚገኙ ሲሆኑ፣ ታካሚዎች ሕክምናቸውን በወቅቱ አግኝተው ያለመመለስና ተገቢውን ሕክምና ያለማግኘት ችግሮች እንደሚገጥማቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል፡፡

በኒውዴልሂ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሚኒስትር ካውንስለር አቶ መታሰቢያ ታደሰ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በህንድ ሕክምና የሚያገኙ ኢትዮጵያውያን ሁኔታ ጥሩ ነበር፡፡ አሁን አሁን ግን በርካታ ደረጃቸውን ያልጠበቁ ሆስፒታሎች በሚልኳቸው ደላሎች በኩል የሚመጡ ኢትዮጵያውያን እየተጉላሉ ይገኛሉ፡፡ አብዛኛዎቹ ታካሚዎች በኢትዮጵያ የማይሰጡ እንደኩላሊትና የጉልበት ማስቀየር

መንግሥት ወደ ህንድ ለሕክምና የሚሄዱ ዜጐችን አስጠነቀቀ

በውድነህ ዘነበ

የኢትዮጵያውያን ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) በኢሕአዴግ ተፅዕኖ ተገፍቶ እንደማይወጣ ለማሳየት ቀጣዩን የሚያዝያ ምርጫ አንድ ዕጩ ተወዳዳሪ ብቻ በማቅረብ እንደሚሳተፍ አስታወቀ::

ኢዴፓ ዓርብ የካቲት 1 ቀን 2005 ዓ.ም. በራስ ሆቴል በሰጠው መግለጫ፣ ኢሕአዴግ በምርጫው ላይ የተቃዋሚውን ጎራ ሚና ትርጉም አልባ ቢያደርገውም፣ ኢዴፓ በኢሕአዴግ ተፅዕኖ ከምርጫ ሥርዓቱ ተገፍቶ እንደማይወጣ ለማረጋገጥ ሲል በመርህ ደረጃ በምርጫ ተሳታፊ ለመሆን መወሰኑን አስታውቋል::

ብቸኛው የኢዴፓ ዕጩ አቶ ወንድወሰን ተሾመ ሲሆኑ፣ አቶ ወንድወሰን ለአዲስ አበባ ምክር ቤት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ይወዳደራሉ:: ‹‹ይኼ ለእኔ ታሪክ ነው፤›› ሲሉ የኢዴፓው ብቸኛ ዕጩ ተወዳዳሪ የሆኑት የፈጠረባቸውን ስሜት ገልጸዋል::

ከተመሠረተ 12 ዓመታትን ያስቆጠረውና

ኢዴፓ በአንድ ዕጩ ብቻ በምርጫው ተሳታፊ እሆናለሁ አለ

በኢትዮጵያ የተቃውሞ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ስም ያለው ኢዴፓ፣ በሚያዝያ 2005 ዓ.ም. በሚካሄደው የአካባቢና የማሟያ ምርጫ በሙሉ አቅሙ መወዳደር ያልቻለበትን አሥር ነጥቦች ይዘረዝራል:: ከእነዚህ ነጥቦች መካከል አንዱ በመራጩ ሕዝብና በተመራጭ ፓርቲዎች መካከል ድልድይ ሆነው የሚያገናኙት የመገናኛ ብዙኅን የማይተካ ሚና እንዳላቸው ይታወቃል ይላል:: ነገር ግን ጉዳዩ በጋራ ምክር ቤት ቀርቦ መፍትሔ እንዲያገኝ የተደረገው ጥረት በተለያዩ ምክንያቶች ተደናቅፏል ይላል ኢዴፓ::

በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ነጥብ በሕገ መንግሥቱና የፖለቲካ ፓርቲዎችን ምዝገባ ሕግ መሠረት አድርጎ በምርጫ ቦርድ የወጣው ደንብ አዲስ አበባ የፌዴራል መንግሥት አባል ሆኖ፣ በአገራዊ የምርጫ ሒደት ውስጥ በተደጋጋሚ የምርጫ ፋይናንስና ድጋፍ እንደተሰጠው ቢታወቅም ለዚህ ምርጫ ድጋፍ እንዳይኖር ተደርጓል የሚል ነው::

በሦስተኛ ደረጃ ኢዴፓ ያስቀመጠው ነጥብ ኢሕአዴግ በመንግሥት ወጪና አወቃቀር ያደራጃቸው ‹‹የልማት ሠራዊቶች›› ወደ ምርጫ ሠራዊትነት በመለወጥ በዕጩዎች፣ በመራጩ ሕዝብና በደጋፊዎች ላይ ከፍተኛ ወከባ ማካሄዳቸውን መታዘቡን ይገልጻል::

ኢዴፓ ማብራርያውን ሲቀጥል በተደጋጋሚ በምርጫ ሒደት ችግር ፈጥረዋል የተባሉ የምርጫ አስፈጻሚዎች ገለልተኝነታቸውና የሁሉንም ተቃዋሚ ፓርቲዎች ይሁንታ ባገኙ አስፈጻሚዎች እንዲተኩ የቀረቡ በርካታ ጥያቄዎች ቢኖሩም ምርጫ ቦርድ እስካሁን ምላሽ አልሰጠም::

የኢዴፓ የወቅቱ ፕሬዚዳንት አቶ ሙሼ ሰሙ፣ አንድ ዕጩ ለምርጫ የሚያስፈልገው ድጋፍ ባለመኖሩ በቂ ፖስተርና በራሪ ወረቀቶች ሳይኖሩ፣ ፍላየርስ፣ የተሽከርካሪ ቅስቀሳ ሳያደርግ፣ በመገናኛ ብዙኅን የፖለቲካና የኢኮኖሚ ፍልስፍናውን ሳያቀርብ፣ በቂ ታዛቢ ማሰመራት ሳይቻል ምርጫው ሚዛናዊና ውድድር ያለበት ነው

Page 4: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 4 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ወደ ክፍል-1 ገጽ 43 ዞሯል

ወደ ክፍል-1 ገጽ 43 ዞሯል

በዮሐንስ አንበርብር

ከሁለት ዓመት በፊት በአምባሳደርነትና በምክትል አምባሳደርነት ማዕረጐች ተሹመው በተለያዩ አገሮች ከተመደቡ የቀድሞ ከፍተኛ ባለሥልጣናት መካከል አሥራ ስምንት የሚሆኑት ወደ አገር እንዲመለሱ ተደረገ:: ሁለቱ በድጋሚ ሹመት ወደሌሎች አገሮች ሲመደቡ የተቀሩት ግን በአገር እንዲቀሩ ተደርጓል::

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት

አምባሳደሮቹ የተመለሱት ለምንድን ነው? ተልዕኮአቸውን ጨርሰው ነው ወይ? የሚል ጥያቄ ባለፈው ሐሙስ በምክር ቤቱ ለተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም አቅርበዋል:: የተመለሱት አምባሳደሮች በአሁኑ ወቅት ያለ ሥራ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥርያ ቤት ተቀምጠው እንደሚገኙና አስተዳደራዊ ችግር እንዳለባቸውም እየገለጹ በመሆኑ፣ በዚህ ላይ ዝርዝር ማብራሪያ እንዲሰጣቸው የምክር ቤቱ አባላት ሚኒስትሩን ጠይቀዋል::

‹‹በአንድ አገር ሁለት አምባሳደር ሊኖር አይችልም:: ሊኖር የሚችልበት ምክንያት በሚመደቡበት አገር እንደ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያሉ ተቋማት የሚገኙ ከሆነና በመንግሥት በኩል እንደነዚህ ያሉ ተቋማት በአምባሳደሮች እንዲወከሉ ከተፈለገ ነው፤›› በማለት ምላሽ መስጠት የጀመሩት ሚኒስትሩ፣ ሹመቱ የተሰጠው ግን በዚህ

በአምባሳደርነት ከተሾሙ ከፍተኛ ባለሥልጣናት 16 እንዲመለሱ ተደረገ‹‹ለበጐ ዓላማ የተሰጠ ሹመት ቢሆንም ስህተት በመሆኑ ተጠርተዋል›› የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

ወደ ክፍል-1 ገጽ 43 ዞሯል

በሔኖክ ያሬድ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስድስተኛው ፓትርያርክ የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም. እንደምትመርጥና 800 መራጮች ድምፅ እንደሚሰጡ አስታወቀች::

ቅዱስ ሲኖዶስ ያቋቋመው የአስመራጭ ኮሚቴ ሰብሳቢ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ የጅማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. በመንበረ ፓትርያርክ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፣ የካቲት 21 ቀን ለሚፈጸመው የፓትርያርክ ምርጫ የሚቀርቡት አምስት ዕጩ ፓትርያርኮች የካቲት 18 ቀን ለሕዝብ ይፋ ይሆናሉ::

ስድስተኛውን ፓትርያርክ የሚመርጡት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት መምርያ ኃላፊዎች፣ ጥንታውያን ገዳማትና አድባራት፣ ካህናት፣ ምዕመናን የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችና የማኅበረ ቅዱሳን

ለስድስተኛው ፓትርያርክ ምርጫ 800 መራጮች ድምፅ ይሰጣሉ

ምርጫው የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም. ይፈጸማል

ወደ ክፍል-1 ገጽ 43 ዞሯል

ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ (በግራ) ከብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ የጅማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የአስመራጭ ኮሚቴ

ሰብሳቢ ጋር በመግለጫው ወቅት

በምሕረት ሞገስ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይተችበት የነበረውን የትምህርት ጥራት መጓደልና የደረጃ መውረድ ለማረም በዩኒቨርሲቲው ፕሮግራሞች ላይ ክለሳና ግምገማ እያካሄደ ነው::

በፕሮግራሞች ላይ የሚደረገውን የግምገማ ሒደት አስመልክቶ ከየፕሮግራምና ከየትምህርት ክፍሉ ከተውጣጡ ምሁራን ጋር ለመምከር ዩኒቨርሲቲው ባዘጋጀው ዓውደ ጥናት ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጄሉ ኡመር እንደተናገሩት፣ የዩኒቨርሲቲውን አጠቃላይ ጥራትና ደረጃ ለማስጠበቅ በፕሮግራሞቹ ላይ ክለሳውን ማካሄድ ወሳኝ ሆኖ ተገኝቷል::

በዩኒቨርሲቲው ጥራት ለማምጣት፣ ፕሮግራሞችን ለማሻሻል፣ ገበያውን ያማከለ ፕሮግራም ለመክፈት፣ ተወዳዳሪ ለመሆንና የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ የሚፈልገውን የተማረ ኃይል ለማብቃት ዩኒቨርሲቲው በፕሮግራሞቹ ላይ ስትራቴጂካዊ ለውጥ ማድረግ ይጠበቅበታል ብለዋል::

ከየትምህርት ክፍሎች ኃላፊዎችና

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጥራት መጓደልን ለማረም የፕሮግራሞች ክለሳ እያደረገ ነው

ወደ ክፍል-1 ገጽ 43 ዞሯል

በሔኖክ ያሬድ

በኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ ታሪክ ሁነኛ ስፍራ ያላቸው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥነ ጽሑፍ ተባባሪ ፕሮፌሰር የነበሩት ዶክተር ዮናስ አድማሱ ባለፈው ዓርብ በ69 ዓመታቸው ድንገት አረፉ::

በ1936 ዓ.ም የተወለዱት ዶክተር ዮናስ ከቄስ ተማሪ ቤት በኋላ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በኮከበ ጽባሕ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ትምህርት ቤት ያጠናቀቁ ሲሆን፣ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲም (የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ ጽሑፍ ክፍለ ትምህርት በ1959 ዓ.ም. የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በማዕርግ ካገኙ በኋላ፣ ዩኒቨርሲቲውን በአስተማሪነት አገልግለዋል:: ከአሜሪካ ካሊፎርንያ ዩኒቨርሲቲ እንግሊዝኛ እንደ ሁለተኛ ቋንቋ በሚል ዘርፍ የማስተርስ ዲግሪ አግኝተው በመመለስ ዩኒቨርሲቲውን ያገለገሉት ዶክተር ዮናስ፣ በ1970 ዓ.ም. በስደት ወደ አሜሪካ በማቅናት በአፍሪካ ጥናት ሌላ ሁለተኛ ዲግሪ አግኝተዋል:: ለማስተርስ ዲግሪያቸው ያዘጋጁት የመመረቂያ ድርሳን ‹‹Narrating Ethiopia- A Panorama of the National Imaginary›› የሚል ሲሆን፣ በዚያው ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ያገኙት ደግሞ በአንፃራዊ ሥነ ጽሑፍ (Comparative Literature) ነው::

ዕውቁ የሥነ ጽሑፍ ባለሙያ ዶክተር ዮናስ አድማሱ አረፉ

ሐኪም ማሞም አርፈዋል

ዶክተር ዮናስ አድማሱ

በአዲስ አበባና በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲዎች በተለያየ ደረጃ ያስተማሩት ዶክተር ዮናስ በጠሊቅ ጥናትና ምርምሮቻቸው ታዋቂ የነበሩና

በዳዊት ታዬ

ከአዋጅ ውጪ ተወርሶ በመርህ ደረጃ እንዲመለስ ውሳኔ ተሰጥቶበት የነበረው የድሬዳዋ ንግድ ምክር ቤት ባለአራት ፎቅ ሕንፃ ሳይመለስ 10 ዓመታትን ማስቆጠሩ ተገለጸ::

ከ30 ዓመታት በፊት የተገነባውንና ድሬዳዋ ከተማ ቀበሌ 04 ክልል ውስጥ የሚገኘውን ይህንን ሕንፃ ለማስመለስ ለዓመታት የተደረገው ጥረት አዎንታዊ ምላሽ ሳያገኝ ቢቆይም፣ አሁን ግን ሕንፃውን ለማግኘት የሚያስችለን ደረጃ ላይ ደርሰናል ሲል የድሬዳዋ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ገልጿል::

በድሬዳዋ ንግድ ምክር ቤትና በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ የኢትዮጵያ የጫት፣ የእርሻና የእርባታ ውጤቶች ላኪና አስመጪ አክሲዮን ማኅበር በጋራ የተገነባ ነው የተባለውን ይህ ሕንፃ፣ በአሁኑ ወቅት እየተጠቀመበት የሚገኘው የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ነው::

ለሕንፃው አለመመለስ ዋናው ምክንያትም ከአስተዳደሩ ጋር በአመላለሱ ዙሪያ መግባባት

የድሬዳዋ የንግድ ኅብረተሰብ የተወረሰ ሕንፃችን ይመለስ እያሉ ነው

ሕንፃው እንዲመለስ ከተወሰነ 10 ዓመት በላይ ቢሆንም መረከብ አልቻለም

በሰለሞን ጎሹ

በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ ምሁራንን ያፈራው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት 50ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ መጻሕፍትንና የምርምር ሥራዎችን ለሕትመት ሊያበቃ ነው::

አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት 50ኛ ዓመቱን ለማክበር ዝግጅቱን አጠናቋል:: የሕግና ገቨርናንስ ስተዲስ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ታደሰ ካሳ የበዓል አከባበር ኮሚቴ መዋቀሩን ለሪፖርተር ገልጸዋል::

በ1956 ዓ.ም. የተቋቋመው የሕግ ትምህርት ቤት 50ኛ ዓመቱን የሚያከብረው በ2006 ዓ.ም. ሲሆን ኮሚቴው በቀሩት ወራት የቀድሞ ተመራቂዎችን በማፈላለግ፣ ገንዘብ በማሰባሰብ፣ የሴሚናርና የምርምር ሥራዎች እንዲዘጋጁ ሁኔታዎችን የማመቻቸትና ልዩ የሕትመት ሥራዎችን እንደሚያዘጋጅ ዶ/ር ታደሰ ገልጸዋል::

በኢትዮጵያ የሕግ መጽሔትና በሕግ ትምህርት ቤት የቀድሞ ባልደረቦች የተጻፉ ሥራዎች፣ የአገሪቱን የተለያዩ እንቅስቃሴዎች በመመዝገብ እንደ ታሪክ ሰነዶች የሚያገለግሉ በመሆናቸው የተወሰኑ ሥራዎች በድጋሚ ታትመው በበዓሉ ላይ ለሽያጭ እንደሚቀርቡም ዶ/ር ታደሰ አመልክተዋል::

ተጨማሪ የሕትመት ሥራዎችን ከማዘጋጀት ጎን ለጎን የኢትዮጵያ የሕግ መጽሔት ሥራዎችን በሶፍት (ኤሌክትሮኒክ) ኮፒ የማዘጋጀት ሥራም መጀመሩን ዶ/ር ታደሰ ጠቁመዋል:: በበዓሉ

የሕግ ትምህርት ቤት 50ኛ ዓመቱን ሊያከብር ነው

ወደ ክፍል-1 ገጽ 44 ዞሯል

Page 5: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 5 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታ

ወቂያ

በታምሩ ጽጌ

በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የፍርድ ቤቶች፣ የፖሊስ የዓቃቤ ሕግ፣ የፀጥታና የማረሚያ ቤቶች አመራሮች፣ ከእሑድ የካቲት 3 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ ለአሥር ቀናት ግምገማዊ ሥልጠና መግባታቸውን ምንጮች ገለጹ::

ከፍተኛ አመራሮቹ ግምገማዊ ሥልጠናውን እስከ የካቲት 12 ቀን 2005 ዓ.ም. እንደሚያካሂዱ የገለጹት ምንጮቹ፣ ግምገማዊ ሥልጠና ይባል እንጂ ዋናው አጀንዳ ግምገማ እንደሚሆን ጠቁመዋል::

በሌሎቹ ተቋማት ላይ ያሉ አመራሮች ግምገማም ሆነ ሥልጠና መስጠቱ የተለመደ መሆኑን የሚናገሩት ምንጮቹ፣ ከማንኛውም ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ነፃ ሆኖ መሥራት እንዳለበት የሚታመነው የዳኝነት አካል በሥልጠናው እንዲታደም መደረጉ፣ ገለልተኛ ሆኖ የመሥራቱ ጉዳይ ላይ ጥያቄ ሊያስነሳ ይችላል የሚል ግምታቸውን ተናግረዋል::

ግምገማዊ ሥልጠናውን የሚሰጡት የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ዓለማየሁ አቶምሳ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አቶ ኩማ ደመቅሳና የኦሕዴድ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ አስቴር ማሞ ሊሆኑ እንደሚችሉ የገመቱት ምንጮቹ፣ የተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳ እንዲያሠለጥኑ ተጠይቀው በሥራ ብዛት እንደማይችሉ ምላሽ መስጠታቸውን ተናግረዋል::

ግምገማዊ ሥልጠናው የሚሰጠው በአዳማ ከተማ ሲሆን፣ በመጀመሪያው ቀን ለግምገማዊ ሥልጠናው መነሻ ሐሳብ ጽሑፍ ከቀረበ በኋላ በቡድን በቡድን ተከፋፍለው ግምገማው እንደሚካሄድ ምንጮቹ ጠቁመዋል::

በቡድን ተከፋፍለው በመሠረቱት ኮሚቴ

አማካይነት በተለይ በፍርድ ቤቶች አመራሮች ላይ ሊደረግ የሚችለው ግምገማዊ ሥልጠና፣ በተለያዩ ጉዳዮች ክስ በሚመሠረትባቸው ዜጎች ላይ ስለሚሰጠው የዋስትና ፈቃድና የቅጣት ውሳኔ ላይ ትኩረት ሊደረግ እንደሚችል ምንጮች ግምታቸውን ተናግረዋል:: አክለውም በተለይ ዳኞች ሥልጠናም ሆነ ግምገማ ሊሰጣቸው የሚችልበት ራሱን የቻለ አሠራር ስላለው፣ በዚያ በኩል ቢሆን የተሻለ ሊሆን ይችል እንደነበረም ገልጸዋል:: ዳኝነትና ፖለቲካ ግልጽ ባለ ሁኔታ መገናኘት ከጀመሩ፣ የክልሉ የፍትሕ ሥርዓት ጥያቄ ውስጥ ሊገባ ስለሚችል ሊታሰብበት እንደሚገባም ምንጮቹ ጠቁመዋል::

ከፍተኛ አመራሮቹ ለአሥር ቀናት በአዳማ ከትመው ስለሚያካሂዱት ግምገማዊ ሥልጠና ማብሪራያ ለማግኘት የኦሮሚያ ክልል የኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ባለሙያዎችን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት ባይሳካም፣ አንድ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የቢሮው ባልደረባ፣ ግምገማዊ ሥልጠናው እንደሚካሄድ አረጋግጠው ዝርዝር አጀንዳውን እንደማያውቁት ተናግረዋል::

ሌላው ምንጮች የገለጹት የኦሮሚያ ክልል በ2005 በጀት ዓመት ላለፉት ስድስት ወራት ያከናወነውን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በሥራ አስፈጻሚው አማካይነት የካቲት 1 እና 2 ቀን 2005 ዓ.ም. ለምክር ቤቱ ማቅረቡን ነው:: ምንጮቹ ዝርዝር ማብራሪያ ማግኘት እንዳልቻሉ ቢናገሩም፣ በዘንድሮው የበጀት ዓመት በኦሮሚያ ክልል እየተካሄደ የሚገኘው የሥራ ሒደት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር ዝቅተኛ መሆኑንና በርካታ መሠራት የነበረባቸው ተግባራት በአግባቡ ሊፈጸሙ አለመቻላቸውና በተለያየ መንገድ ሊገነዘቡ መቻላቸውን አሳውቀዋል:: የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርቱ እንዳበቃም ወደ ግምገማዊ ሥልጠናው የሚመለከታቸው አካላት መሄዳቸውንም አክለዋል::

የኦሮሚያ ክልል ዳኞችና የሌሎች ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ግምገማዊ ሥልጠና ገቡ

የክልሉ የስድስት ወራት ሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቧል

በውድነህ ዘነበ

የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር በተደጋጋሚ በበጀት ዓመት ግማሽ ዓመት ተጨማሪ የበጀት ጥያቄ እንደማይቀበል ቢገልጽም፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በቅርቡ ለተቋቋመው የኢኮኖሚና የፋይናንስ ክላስተር ማስተባበሪያ የተጨማሪ በጀት ጥያቄውን ሊያቀርብ ነው::

ክላስተሩን የሚያስተባብሩት በምክትል ጠቅላይ ማኒስትር ማዕረግ የክላስተሩ አስተባባሪና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል ናቸው::

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ስድስት ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ይፈልጋል:: የባለሥልጣኑ ምንጮች እንደሚገልጹት፣ ከዚህ ገንዘብ ውስጥ ቢያንስ ቢያንስ ሦስት ቢሊዮን ብር ያስፈልገዋል::

በገንዘብ ሚኒስቴር ተስፋ የቆረጠው መንገዶች ባለሥልጣን የበጀት ጥያቄውን ለፋይናንስ

ማስተባበሪያ ሊያቀርብ ነው

ወደ ክፍል-1 ገጽ 42 ዞሯል

በውድነህ ዘነበ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከወረዳ በታች ሦስት አዳዲስ መዋቅሮችን ለመክፈት ዝግጅት ማጠናቀቁን ምንጮች ገለጹ:: ቀደም ሲል ቀበሌ ይባል የነበረው መዋቅር ወረዳ ከተባለ በኋላ ወረዳ የመጨረሻው የከተማው መዋቅር መሆኑ ይታወቃል:: መንግሥት ከወረዳ በታች ‹‹ቀጣና››፣ ‹‹ሠፈር›› ‹‹ጎጥ›› ወይም ‹‹ብሎክ›› የተሰኙ ሦስት መዋቅሮችን ለማቋቅም ዝግጅቱ ተጠናቋል::

ምንጮች እንደገለጹት፣ ‹‹ቀጣና›› በሚሰኘው መዋቅር ‹‹ሠፈር›› በተሰኘው መዋቅር የተወከሉ ሰዎች ምክር ቤት ያቋቁማሉ:: ምክር ቤቱ የራሱ ሥራ አስፈጻሚ፣ ብሎም ዋና ሥራ አስኪያጅና ረዳት ሥራ አስኪያጅ ይኖሩታል:: ‹‹ሠፈር›› ከ18 ዓመት በላይ የሆኑ ወጣቶችና ጎልማሶች ምክር ቤት አቋቁመው መንደራቸውን ለማልማት ይሠራሉ:: ‹‹ብሎክ›› ወይም ‹‹ጎጥ›› ተመሳሳይ ሥራ የሚሠሩበት ይሆናል ተብሏል::

አንድ የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣን ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ አዲስ አበባ ላይ ትልቁ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ አገልግሎት እየሰጠ ያለው ወረዳ ነው:: መንግሥት ከወረዳ በታች በጥልቀት ወደታች የሚወርዱ ሦስት መዋቅሮች

እንዲቋቋሙ ውሳኔ አሳልፏል:: በእነዚህ ሦስት መዋቅሮች ኅብረተሰቡ አካባቢውን ማልማት የሚችልበት ሁኔታ ይበልጥ ይፈጠራል:: የአካባቢዎቹ ነዋሪዎች በኅብረት ሥራ ማኅበር እየተደራጁ መኖርያ ቤት የሚገነቡበትና አካባቢያቸውንም የሚያለሙበት ሁኔታ ይፈጥራሉ ይላሉ ባለሥልጣኑ::

በአዲስ አበባ አሥር ክፍላተ ከተሞችና 116 ወረዳዎች ይገኛሉ:: በእነዚህ ወረዳዎች ሥር ነው ሦስቱ አዳዲስ መዋቅሮች የሚከፈቱት:: ነገር ግን በአንድ ወረዳ ሦስቱ መዋቅሮች ምን ያህል ቁጥር እንደሚኖራቸው አልታወቀም:: ይሁንና የትኛውም አካባቢ ከእነዚህ መዋቅሮች ውጭ እንደማይሆን እየተገለጸ ነው::

‹‹ቀጣና›› የሚለው ቃል ለአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ባይሆንም፣ ‹‹ጎጥ›› ወይም ‹‹ብሎክ›› በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ራሱን የቻለ መዋቅር ሆኖ የቆየ ይሁን እንጂ በአዲስ አበባ የተለመደ አይደለም:: ‹‹ቀጣና›› ከወታደራዊው መንግሥት መውደቅ ጋር ተያይዞ የጠፋ ቢሆንም፣ በአዲስ አበባ በድጋሚ ጥቅም ላይ እንዲውል ሁኔታዎች ተመቻችተውለታል ተብሏል:: ‹‹ጎጥ›› የሚለው ስያሜ ከሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል መጥቶ በአዲስ አበባ ለመጀመርያ ጊዜ ጥቅም ላይ እንደሚውል ይጠበቃል::

በአዲስ አበባ ከወረዳ በታች ሦስት አዳዲስ መዋቅሮች ሊመሠረቱ ነው

Page 6: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 6 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ማስታ

ወቂያ

ማስታ

ወቂያ

ፖ ለ ቲ ካ

በሰለሞን ጎሹ

ግብፅ ደኅንነቷ፣ ማኅበራዊ መረጋጋቷና ኢኮኖሚዋ ተበጥብጧል:: ብጥብጥ ነግሦባታል:: ባለፈው ሰኔ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት ሙሐመድ ሙርሲና ፓርቲያቸው የሙስሊም ወንድማማቾች ከሌሎች የፖለቲካ ተዋንያን ጋር አብረው መሥራት ተስኗቸዋል:: ተቃዋሚዎች፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ፣ ፍርድ ቤቶችና ወታደሩ በሙርሲ ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችን እያነሱ ነው:: የሁሉም ጥያቄዎች መነሻ የሕገ መንግሥት ማርቀቅ ሒደቱና በቅርቡ የፀደቀው ሕገ መንግሥት የሸሪአ ተፅዕኖ አለበት መባሉ ነው:: የፖርትሳይዱ ብጥብጥ እዚህ ላይ ነው የተጨመረው::

በፖሊስና ለተቃውሞ በሚወጣው ሕዝብ መካከል ያለው አለመግባባት ያልተጠበቀ የብጥብጥ አቅጣጫ ይዟል:: በማዕከላዊ የደኅንነት ኃይሎችና በጦር ኃይሎች ውስጥ መንግሥት እየወሰደ ባለው ዕርምጃ ላይ አለመግባባት መኖሩን ዘገባዎች እያመለከቱ ነው:: የፖለቲካ አለመረጋጋቱ ቀድሞም ቢሆን ታማሚ የነበረውን የግብፅን ኢኮኖሚ ወደ አዘቅት ውስጥ እየከተተው ነው::

ሙርሲ 51.7 በመቶ የመራጮችን ድምፅ አግኝተው ፕሬዚዳንት ሲሆኑ ባደረጉት ንግግር ግብፅ የሁሉም ፖለቲካ ተዋንያን የጋራ ጉዳይ መሆኗን ተናግረው ነበር:: የሙስሊም ወንድማማቾች ያራምዱታል ከሚባለው አክራሪ የእስልምና አስተሳሰብ አንፃር ንግግራቸው ተስፋ ሰንቆ ነበር:: አሜሪካ፣ እስራኤል፣ ፍልስጤምና አብዛኛው የዓረብ አገሮች መሪዎች ሙርሲን በአድናቆት ነበር የተቀበሏቸው:: በተለይ ደግሞ እስራኤልና ሐማስ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያደርጉ የተጫወቱት ስኬታማ የአደራዳሪነት ሚና፣ ከደቡብ ካሮላይና ዩኒቨርሲቲ በማቴሪያል ሳይንስ በፒኤችዲ ለተመረቁት የቀድሞው የዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር ሙርሲ ተጨማሪ ተቀባይነትን አስገኝቶላቸው ነበር::

ሥልጣን ከያዙ በኋላ የወሰዷቸው ዕርምጃዎች ያልተመቻቸው በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ግን በጥቅምት ወር 2005 ዓ.ም. ወደ ታሪካዊው የተቃውሞ አደባባይ ታህሪር በማምራት ተቃውሞአቸውን ሲያሰሙ ‹‹ፈላጭ ቆራጭ›› ብለዋቸዋል:: ተቃውሞውንና የፍርድ ቤቱን አንዳንድ ውሳኔዎች በመቃወም ፕሬዚዳንቱ በጥቅምት ወር ያወጁት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለሚወስዱት ማንኛውም ዕርምጃ ፍርድ ቤቶች ጉዳዩን አስመልክተው ጥያቄ እንዳያነሱ የሚከለክል ነበር:: አዋጁን

የግብፅ ብጥብጥና ኢትዮጵያተከትሎ የኖቬል የሰላም አሸናፊ የሆኑት የቀድሞው የዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዳይሬክተር ሙሐመድ አልባራዳይ ሙርሲን ‹‹አዲሱ ፈርኦን›› ሲሉ አምባገነንነታቸውን ገልጸዋል::

ባለፈው ሐሙስ ከግብፅ የተሰማው ሌላ ዜና ደግሞ አገሪቷ ያለችበት ሁኔታ እየተወሳሰበ መምጣቱን የሚያሳይ ነው:: ረቡዕ ዕለት የቱኒዝያ እስላማዊ መንግሥትን በመተቸት የሚታወቁት ሾክሪ በላይድ ተገድለዋል:: በላይድ እንዲገደሉ አክራሪው የሃይማኖት መሪ ማህሙድ ሻባን ጥሪ ማድረጋቸው የተዘገበው ሐሙስ ዕለት ነው:: ፕሬዚዳንት ሙርሲ የሻባንን ጥሪ በመቃወም መግለጫ ያወጡ ሲሆን፣ ‹‹ሃይማኖትን በመጠቀም የጥላቻ ፖለቲካን የሚያራምዱትን እንቃወማለን:: ሃይማኖት ንፁህ ነው:: ብሔራዊ የፖለቲካ ኃይሎች፣ የሃይማኖት ተቋማትና ታዋቂ ምሁራን ይህን ተቀባይነት የሌለው ማነሳሳት ለመቃወም የተባበረ ግንባር እንዲፈጥሩ ጥሪ አደርጋለሁ፤›› ያሉት ሙርሲ፣ የተቃዋሚ ፖለቲከኞችን ደኅንነት ለመጠበቅ የተጠናከረ ኃይል እንደሚጨመር አረጋግጠዋል::

ፕሬዚዳንቱ በሙስሊም ወንድማማቾችና በአክራሪ የሰለፊ ቡድኖች ቢደገፉም ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ ዳኞች፣ ክርስቲያኖች፣ ከሃይማኖት ውጭ ያሉ ዜጎች፣ ሚድያውና በመንግሥት ደካማ አገልግሎቶች የተማረሩ ዜጎች ሙርሲን በአክራሪነት ይከሳሉ:: በታኅሳስ ወር ከታይም መጽሔት ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት ፕሬዚዳንት ሙርሲ ሙስሊም ወንድማማቾች ዲሞክራሲያዊ ሊሆን ስለመቻሉ ሲጠየቁ፣ ‹‹መልሴ ትልቅ አዎ ነው:: የዜጎች ነፃነት፣ የእምነት ነፃነት፣ ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት፣ እኩልነት፣ መረጋጋትና ሰብዓዊ መብት ከእስልምና እምነት ይመነጫሉ:: ከሌላኛው እምነታችን ከዲሞክራሲም ይመነጫሉ:: ሙስሊም ወንድማማቾች ሁሌም የሚጥረው በግብፅ ተቋማዊና ሕገ መንግሥታዊ አገር ለመገንባት ነው፤›› ብለዋል::

ሙስሊም ወንድማማቾችእ.ኤ.አ. በ1923 ዓ.ም. ሐሰን አልባና የተሰኘ ወጣት

የግብፅን ዋና ከተማ ለመጎብኘት ወደ ካይሮ ካቀና በኋላ በከተማ ያየው የማያምኑ ሰዎች እንቅስቃሴና ፀረ ሞራል አኗኗርን ለመቀየር፣ ከሚያስተምርበት ዳር አልኡሉም ኮሌጅና ከአልሐዛር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አደራጅቶ ማስተማር ጀመረ:: የአልባና የግል ማስታወሻ እንደሚያመለክተው፣ ሠራተኞች ተማሪዎችን መቀላቀል ሲጀምሩ እ.ኤ.አ. በ1920ዎቹ መጨረሻ ላይ የሙስሊም

ወንድማማቾች ሶሳይቲን መሠረተ:: የሶሳይቲው መነሻ ዓላማ አባላቱን ትክከለኛ የእስልምና ግንዛቤ እንዲኖራቸው ማስቻል ነበር::

አልባና የሶሳይቲው ዓላማ መቀየሩን የጠቆመ ንግግር እ.ኤ.አ. በ1938 አደረገ:: ‹‹እስልምና አምልኮና መንፈሳዊነት ብቻ እንደሆነ የሚያስቡ ተሳስተዋል:: እስልምና እምነትና አምልኮን፣ አገርና ዜግነትን፣ ሃይማኖትና መንግሥትን፣ ድርጊትና መንፈሳዊነትን፣ ቁርዓንና ሰይፍን አንድ ላይ የያዘ ነው፤›› ይል ነበር:: የሙስሊም ወንድማማቾች እንቅስቃሴ ከግብፅ መንግሥት ጋር እየተጋጨ በመሄዱ እ.ኤ.አ. በየካቲት 1949 አልባና ተገደለ::

የፓርቲው ርዕዮተ ዓለም በመላው ዓረብ አገሮች ድጋፍ በማግኘቱ ዛሬ በብዙ አገሮች የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ ይገኛል:: ይሁንና በግብፅ በይፋ በሙርሲ በኩል ወደ ሥልጣን የመጣው ሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ ከአልባና መሞት በኋላ ለ63 ዓመታት ያህል ብዙ ውጣ ውረዶችን አይቷል:: ጫና ሲበዛበት መልኩን እየቀያየረ የግብፅን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የሕግ፣ የሃይማኖትና የባህል ማዕቀፍ በበላይነት ለመምራት ጥረት አድርጓል::

እ.ኤ.አ. በ1964 የፓርቲው መሪ ሰይድ ቁጥብ ‹‹Signposts on the Road/Ma’alim fi’l-Tariq›› በተሰኘው ሥራቸው ከሸሪአ ወይም ከዓለማዊ መንግሥት (ጃህሊያ) ውጪ ሦስተኛ አማራጭ እንደሌለ በመግለጽ፣ የእስልምና እንቅስቃሴውን በማክረር አንድ እርከን ጨምረዋል::

እ.ኤ.አ. በ1970ዎቹ የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ ለሁለት ለመሰንጠቅ በቅቷል:: አንዳንዶቹ የቁጥብን ሐሳብ በመከተል ወታደራዊ ቡድን ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ ለዘብተኛ ስትራቴጂ መከተልን መርጠው ነበር:: ፓርቲው ከፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ ጋር ያለው ግንኙነት በውጥረት የተሞላ በመሆኑ እ.ኤ.አ. በ1990ዎቹ ፓርቲው በሕገወጥነት ተፈርጆ ነበር:: የፓርቲው ወታደራዊ ክንፍም በመንግሥት የደኅንነት ኃይሎች፣ በኮፕቲክ ክርስቲያኖች፣ በለዘብተኛ የሙስሊም ምሁራንና በቱሪስቶች ላይ ጥቃት መፈጸሙ በመንግሥት ይገለጽ ነበር:: በአዲስ አበባ የቀድሞውን የግብፅ ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክን ለመግደል የተደረገውን ሙከራ ፓርቲው ቢያወግዝም፣ መንግሥት ግን የሙስሊም ወንድማማቾች እጅ እንዳለበት ይከስ ነበር::

የሙስሊም ወንድማማቾች በዘመነ ሙባረክ ውስጥ ለውስጥ የንግድ ማኅበራትን፣ የሙያ ማኅበራትን፣ የተማሪዎች ኅብረትንና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን

እንዲሁም ሲቪል ማኅበራትን በመቆጣጠር ህልውናቸውን ጠብቀዋል:: አወቃቀሩ፣ ማኅበራዊ መሠረቱና ቅርፅና ባህሪውን ከሁኔታ ሁኔታ የመቀያየር ችሎታው ከመጥፋት ራሱን ለመታደግ ጠቅሞታል:: ሃይማኖታዊ ንቅናቄ ሆኖ ቢጀመርም በግብፅ ፖለቲካ ዋነኛ ሚና ያለው የፖለቲካ ኃይል ሆኖ ጥንካሬን አግኝቷል::

የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ ለስምንት አሥርት ዓመታት በተቃዋሚነት ከቆየ በኋላ አሁን በሥልጣን ላይ ይገኛል:: በተራው ደግሞ ከተለያዩ አቅጣጫዎች በተለያዩ ምክንያቶች የሚቃወሙት አካላት ከበውታል:: ተንታኞች ፓርቲው በድጋፍና በተቃውሞ መሀል መንሳፈፉን በመጠቆም፣ ግብፅ አሁን ካለችበት ብጥብጥ ለመውጣት ብትችል እንኳን የተረጋጋ የፖለቲካ ሥርዓት ለመገንባት እንደሚያዳግታት ያስረዳሉ::

የናይል/ዓባይ ፖለቲካየግብፅ ብጥብጥ ለኢትዮጵያ ምኗ ነው? ብሎ

የሚጠይቅ ሁሉ ትኩረቱ የዓባይ ፖለቲካ ላይ ነው:: ሁለቱ አገሮች በሃይማኖትና በዓባይ ጉዳይ የተነሳ የሰላም ጊዜ ድርሻቸው በአለመግባባትና በጥርጣሬ የተያዩበት ጊዜን አይስተካከልም:: እ.ኤ.አ. ከ1991 ጀምሮ የዓባይን ፖለቲካ ለመቀየርና ባለበት ለማስቀጠል የተደረገውን ግብግብ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊና የግብፅ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ መርተውታል::

መለስና ሙባረክ በራሳቸው አዲስ አጀንዳ ለመነጋገር ብዙም ዕድል አላገኙም:: በ20ኛው ክፍለ ዘመን ግብፅ ከተለያዩ አገሮች ጋር በዋነኝነት በቅኝ ገዥዋ እንግሊዝ አማካይነት የተፈራረመቻቸው ስምምነቶች በዓባይ ውኃ የመጠቀም መብትን ለግብፅ የሚያጎናጽፉ፣ ከሱዳን በስተቀር በዓባይ ተፋሰስ ውስጥ የሚገኙትን እንደ ኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ኮንጎ፣ ሩዋንዳና ብሩንዲ የመሳሰሉ አገሮችን ጨምሮ ለኢትዮጵያ መብት ቦታ ያልሰጡ ስምምነቶች ናቸው::

ኢትዮጵያ ከዓባይ ውኃ ውስጥ 85 በመቶ የሚሆነውን የምታመነጭ አገር ናት:: ዓባይ ካለው 84 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውኃ ውስጥ ግብፅና ሱዳን 70 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር እንዲጠቀሙ ስምምነቶቹ ይደነግጋሉ:: ኢትዮጵያ የምትመራው የላይኛው የዓባይ ተፋሰስ አገሮች ስምምነቶቹ የአገራቱን ብሔራዊ ጥቅም ስለሚነካ እንዲሻሻል ይፈልጋሉ:: የሕዝብ ቁጥራቸው በከፍተኛ

ወደ ክፍል-1 ገጽ 20 ዞሯል

Page 7: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 7 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታ

ወቂያ

ማስታ

ወቂያ

ፖ ለ ቲ ካፖ ለ ቲ ካበየማነ ናግሽ

ተመስገን ደረጀ በ20ዎቹ ዕድሜ ውስጥ የሚገኝ በአዲስ አበባ የሚኖር ወጣት ነው:: ከአምስት ያህል ጓደኞቹ ጋር ተሰባስበው በአንድ መዝናኛ ክበብ ምሳቸውን ሲበሉ እንደሌላ ጊዜ በሳቅና በጨዋታ ሳይሆን በከፍተኛ ጭቅጭቅ ውስጥ ነበሩ:: በአካባቢያቸው የነበሩ ሰዎች በጉዳዩ ላይ እየተነጋገሩ ባይመስሉም በዚሁ ቡድን ክርክርና ጭቅጭቅ ግን ቀልባቸው የተገዛ ይመስላል:: የሚጨቃጨቁት ደግሞ በፖለቲካ አቋም ወይም በእምነት ምክንያት አይደለም:: ሰሞኑን ከሦስት ጊዜ በላይ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ‹‹ጅሃዳዊ ሐረካት›› በሚል በተላለፈው ዘጋቢ ፊልም ላይ ነበር::

የታፈነ ድምፅ ለመተንፈስሕዝቡን በስፋት እያነጋገረ ያለው ይኼው ዘጋቢ ፊልም

ከአተራረኩ ጀምሮ የተመረጠበት ጊዜና ከሌሎች ዓለም አቀፍ የሽብር ተግባራት ጋር እንዲተሳሰር የተደረገበት ምክንያት ‹‹እውነት ነው››፣ ‹‹ውሸት ነው›› በሚል በሁለት ጎራ እያከራከረ ነው:: አብዛኛዎቹ አስተያየት ሰጪዎች የዘጋቢ ፊልሙ እውነትነት ወይም ድራማ መሆን የሚመዘነው ከቀረበው መሠረታዊ እውነት መሆንና አለመሆን ላይ ሳይሆን፣ ግለሰቦች በመንግሥት ላይ ካላቸው አመለካከት ወይም አቋም እየተለካ ይመስላል::

ይህ ዓይነቱ አቋም የተሰማት አንድ ወጣት ሴት ጋዜጠኛ፣ ‹‹አንዳንድ ሰው ፊልሙን በኢቲቪ በመተላለፉ ብቻ በጭፍን እየተቃወመ ይመስለኛል:: እውነት ነው አይደለም አልልም:: በአብዛኛው ድራማ ነው፣ የመንግሥት ፈጠራ ነው የሚሉ ሰዎች የሚያቀርቡት ምክንያት አሳፋሪ ነው:: ድራማ ነው እያሉ ያሉ ሰዎች ለጉዳዩ ትልቅ ትኩረት ሰጥተው ፊልሙን በሥርዓት ተመልክተው የቱ ጋ ‘ፌክ’ እንደሆነ አውቀው አይመስለኝም፤›› ትላለች:: ምናልባት በሌላ ዓለም አቀፍ ሚዲያ ቀርቦ ቢሆን ሊቀበሉት ይችሉ ነበር በማለት:: የጋዜጠኛዋ አስተያየት ሰዎች ዘጋቢ ፊልሙን እውነት ነው ውሸት ነው ብለው ለመቀበልና ላለመቀበል ለመንግሥት ካላቸው ጥላቻ ወይም ፍቅር ጋር መያያዝ የለበትም የሚል ይመስላል::

ተመስገን ያለበት ቡድን አባላትም ጋዜጠኛዋ ያለችውን ነገር የሚያረጋግጡ ይመስላሉ:: ከጥቂቶቹ በስተቀር ዘጋቢ ፊልሙ ለመደገፍና ለመቃወም የሚያቀርቡት ምክንያት ‹‹የኢትዮጵያ መንግሥት እኮ ነው››፣ ‹‹ኢቲቪ ነው እኮ››፣ ወዘተ በሚል ይመስላል:: ያም ሆነ ይህ ዘጋቢ ፊልሙ ድራማ ከሆነባቸው ሁለቱ ሰዎች መካከል አንደኛው በፊልሙ የቀረቡት ተጠርጣሪዎች ተገደው የሚያነቡ የመሰለው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ሰዎቹ ከምር አሸባሪ ቢሆኑ ኖሮ የፈለገው ስቃይና ምርመራ ቢደርስባቸው ቃላቸውን

‹‹ጅሃዳዊ ሐረካት››በጥርጣሬና በጥያቄ መሀልአይሰጡም ይላል:: በአሜሪካ ጓንታናሞ እንኳን በተመሳሳይ ወንጀል የተከሰሱ አሸባሪዎች ነፍሳቸው እስክታልፍ አንዳች ቃል ትንፍሽ አይሉም በሚል መከራከርያ ነጥብ::

የሁለቱም አቋም መንግሥት የሙስሊሙን ማኅበረሰብ ጥያቄ መመለስ ስላቃተው የፈጠረው ልብ ወለድ ነው የሚል ነው:: ‹‹በኢትዮጵያ ውስጥ እንዲህ ዓይነት ተግባር ፈጽሞ አይታሰብም:: መንግሥት ራሱ ሽብር እየፈጠረ ነው፤›› የሚሉ ሲሆን፣ አንድ ቦታ የተፈጸመ አንድ የሽብር ተግባርን መንግሥት በተጨባጭ አለማሳየቱም ሌላው መከራከርያ ነጥባቸውን የሚያጠናክሩበት ነው::

‹‹ጅሃዳዊ ሐረካት›› ጅሃዳዊ ሐረካት ባለፈው ዓመት ‹‹አኬልዳማ›› በሚል

ርዕስ አንዳንድ መንግሥትን በኃይል ለመጣል ከሚንቀሳቀሱ ነፍጥ ያነገቡ (እንደ ኦነግ፣ ኦብነግና ግንቦት 7 የመሳሰሉ) ቡድኖች፣ ከአልሸባብና ከሻዕቢያ ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ሳይፈጸም ስለከሸፈው የሽብር ተግባር ከሚተርከው ዘጋቢ ፊልም ጋር ተመሳሳይ ይዘት ያለው ዘጋቢ ፊልም ነው:: የቀረበውም በኢትዮጵያ መረጃና ደኅንነትና የፌዴራል ፖሊስ ፀረ ሽብር ግብረ ኃይል ነበር::

በዚሁ ፊልም ከቀረበው ተጠርጣሪ አሸባሪ የቡድን መሪ ተብሎ የቀረበው አማን አሰፋ (አማን እስማኤል) እንደሚለው፣ የቡድኑ የመጨረሻ ዓላማ በኢትዮጵያ እስላማዊ መንግሥት (Islamic State) መመሥረት ሲሆን፣ የሽብር መረቡ ከኬንያ (ዳሩ ቢላል) በሞቃዲሾ በኩል ወደ ኢትዮጵያ የተዘረጋ ነው:: አቶ አማን አሰፋ እንደሚለው፣ በአጠቃላይ ለሽብር አፈጻጸሙ ለውጊያ አመቺ ቦታ መምረጥ፣ የጦር መሣርያ ማከማቸትና የምሽግ አቆፋፈር ጭምር በአልሸባብ አባላትና በሌሎች አሸባሪዎች ሥልጠና ተሰጥቷቸዋል::

የምሥራቅ አፍሪካ የአልቃይዳ ዩኒት በተለያዩ አካባቢዎች ያልተማከለ የሽብር ጥቃት የመፈጸም አዲስ ዕቅድ አካል መሆኑን የሚተርከው ይኼው ዘጋቢ ፊልም፣ በናይጄሪያ የንፁሐን ዜጎችን ደም እየፈሰሰ ካለው ቦኮ ሃራምና በማሊ ታሪካዊ ቅርሶችን እያፈራረሰ ካለው አሸባሪ ቡድን ጋር ለማመሳሰል የተደረገ ጥረትም አለ:: ባለፈው

ዓመት በአወልያ ትምህርት ቤት የተነሳውን አመፅ፣ በግብፅ ካለው አመፅ ጋር ለማገናኘትም ተሞክሯል:: በናይሮቢና በዳሬሰላም በሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲዎች የተፈጸሙ የሽብር ተግባራት ምስልም ተካተውበታል:: በከሚሴ የመጀመርያ ጥቃቱን ለመፈጸም በዝግጅት ሳለ ቡድኑ በቁጥጥሩ መዋሉን የሚዘግበው ጅሃዳዊ ሐረካት፣ ከግንቦት ሰባት አባላትና ከኤርትራ መንግሥት ጋር ለማገናኘትም ሙከራ አድርጓል:: ኢትዮጵያ ከፍተኛ የሽብር ማዕከላት ከሆኑት አፍጋኒስታን፣ የመንና ፓኪስታን መካከል መመረጧንም በዘጋቢ ፊልሙ ከተጠርጣሪዎች አንደበት ተሰምቷል::

የፍርድ ቤት ወይስ የሚዲያ ውሳኔ? ‹‹ጅሃዳዊ ሐረካት›› በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን

እንደሚተላለፍ መተዋወቁን ተከትሎ፣ የተጠርጣሪዎች ጠበቆች ባቀረቡት የይታገድልን አቤቱታ መሠረት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አራተኛ ወንጀል ችሎት ዳኛ የእገዳ ትዕዛዝ መጻፋቸው ተሰምቷል:: ሆኖም ዓቃቤ ሕግ ይህንን እግድ በመቃወም ባቀረበው የይግባኝ አቤቱታ መሠረት የከፍተኛው ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወዲያውኑ እግዱን በማንሳታቸው ምክንያት በተያዘለት ጊዜ ዘጋቢ ፊልሙ መተላለፍ ችሏል::

የተጠርጣሪዎች ጠበቆች አቤቱታ ጉዳዩ በፍርድ ሒደት ላይ መሆኑንና ዘጋቢ ፊልሙ እንዲቀርብ መደረጉ በዳኞችና በአጠቃላይ በኅብረተሰቡ ላይ የሚያሳድረው ጫና ደንበኞቻቸው ራሳቸውን የመከላከል መብት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራል የሚል ነው:: ቀደም ሲል በተመሳሳይ እንዲተላለፍ የተደረገው ‹‹አኬልዳማ›› ዘጋቢ ፊልምን ጨምሮ፣ በፍርድ ቤት የተያዙ የሽብር ወንጀሎች በዘጋቢ ፊልም ሲቀርቡ የመጀመርያ አይደለም:: ከዚህም በተጨማሪ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት በመታየት ላይ ያሉ ግለሰቦችን አስመልክቶ በፓርላማ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፣ ‹‹ወንጀለኞች መሆናቸውን አረጋግጠናል›› የሚል አስተያየት መስጠታቸው የሚታወስ ነው:: አስፈጻሚው የመንግሥት አካል በሕግ ተርጓሚው (ፍርድ

ቤት) ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ ተደጋግሞ የተተቸ ጉዳይ ነው:: ባለፉት ተመሳሳይ ጉዳዮች ላይ በርካታ ትችቶችን ያስተናገደው መንግሥት አሁንም ‹‹ጅሃዳዊ ሐረካት›› ዘጋቢ ፊልምን በኢቴቪ ያስተላለፈው፣ የተጠርጣሪዎቹን ምስል እያሳየና በአንደበታቸው እንዲናገሩ በማድረግ ሲሆን፣ ይኼም አንዱ የፊልሙ አነጋጋሪ ጉዳይ መሆኑ ይወሳል::

ከተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች መካከል አቶ ተማም አባቡልጉ ለሪፖርተር እንዳስረዱት፣ በዘጋቢ ፊልሙ ከቀረቡት መካከል አብዛኞቹ በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ክስ ተመሥርቶባቸው ምስክር በመሰማት ላይ በመሆኑ ነበር በፍርድ ቤት አሳግደውት የነበረው:: ሆኖም ጠቅላይ ፍርድ ቤት እግዱን ውድቅ አድርጎ ሊቀርብ መቻሉ እሳቸው እንደሚሉት፣ የክስ ሒደቱን በእጅጉ ይጋፋል:: ተጠርጣሪዎቹ ፖሊስ አስገድዶ አንብቡ እያላቸው ጭምር እንዲቀርብ ተደርጓል ይላሉ::

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ሰሞኑን ባወጣው መግለጫ፣ በዚሁ ዘጋቢ ፊልም የሙስሊሙን ማኅበረተሰብ ጥያቄ ለማፈን ሙከራ እየተደረገ ነው ይላል:: በፍርድ ቤት የታገደ ፊልም ያለምንም ይግባኝ በሌላ ፍርድ ቤት ውድቅ እንዲደረግ በመደረጉም ፓርቲው ተቃውሞውን አሰምቷል:: ይህንን አስመልክተን ያነጋገርናቸው የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ፣ ዘጋቢ ፊልሙ ሙስሊሞች ያቀረቡትን ግልጽ የሆነ ጥያቄን ለማፈን ሆን ተብሎ የቀረበ መሆኑን ይናገራሉ፤ የመንግሥት ኃላፊነት የጎደለው ተግባር በማለት:: ትረካው ሚዛናዊነትን ያልጠበቀ፣ ሕዝቡ በፍርድ ቤት ላይ ያለውን እምነት የሚያሳጣ መሆኑንም አስረድተዋል::

የኢትዮጵያውያን ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ፕሬዚዳንት አቶ ሙሼ ሰሙ በበኩላቸው፣ ዜጎች የመንግሥት ጥበቃ ያስፈልጋቸዋል በማለት አሁን በተደረገው ግን የፋይናንስም ሆነ የቴክኖሎጂ አቅም ያለው መንግሥት በተጠርጣሪዎች ላይ ጫና ይፈጥራል ይላሉ:: ሕጉ ቢፈቅድም ባይፈቅድም፣ ተጠርጣሪዎች በፍርድ ቤት ወንጀለኛ እስካልተባሉ ድረስ ንፁህ መሆናቸው

ወደ ክፍል-1 ገጽ 21 ዞሯል

Page 8: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 8 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ማስታወቂያ

Page 9: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 9 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታወቂያ

Page 10: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 10 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

በዳዊት ታዬ

ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ የጀመረውና የውኃ፣ የመብራትና የስልክ አገልግሎት ክፍያን በአንድ መስኮት የሚያስተናግደው ዘመናዊ የክፍያ ሥርዓት ደንበኞችን ከቀድሞ የባሰ እንግልት ውስጥ ከተተን እያሉ ነው::

ይህ ዘመናዊ የክፍያ ሥርዓት ይፋ ከሆነበት ማግስት ጀምሮ በአዲሱ አሠራር ክፍያቸውን ለመፈጸም ወደተዘጋጁት የክፍያ ማዕከሎች የሄዱ ደንበኞች ፈጣን አገልግሎት ማግኘት አለመቻላቸውንም ገልጸዋል:: የክፍያ ሥርዓቱን የሚያስፈጽመው መሥርያ ቤት ግን ችግሩ የተፈጠረው ከዚህ አገልግሎት መጀመር ጋር ተያይዞ መሥሪያ ቤቶቹ ክፍያ ባለመሰብሰባቸው ደንበኞች አገልግሎቱ ይቋረጥብናል በሚል በተፈጠረ ሥጋት ነው ይላል::

በዚሁ የክፍያ ሥርዓት ለመገልገል ወደክፍያ ማዕከሎቹ የሄዱ ደንበኞች ከዚህ ቀደም በነበረው አሠራር ከገጠማቸው ሰልፍ በላይ እንዳጋጠመችው አምርረው ተናግረዋል::

በአንዳንድ የክፍያ ማዕከሎች ተዘዋውረን እንደተመለከትነውም በመቶዎች የሚቆጠሩ ደንበኞች ረዥም ሰልፍ ይዘው ወረፋ በመጠበቅ ለሰዓታት መቆማቸውን መታዘብ ተችሏል:: ለሁሉ የሚል መጠሪያ የተሰጠው ይህ ዘመናዊ የክፍያ አገልግሎት የሦስቱን አገልግሎት ክፍያ በአንድ ላይ ማድረጉ ተመራጭ ቢሆንም፣ ደንበኞች በፈጣን አገልግሎት መስተናገድ አለመቻላቸውንና ጭርሱኑ የባሰ ሁኔታ መመልከታቸው ቅሬታ ፈጥሮባቸዋል::

ለሁሉ ዘመናዊ የክፍያ አገልግሎትን ተግባራዊ ለማድረግ ለዓመታት ሲሠራበት የቆየው የፕሮጀክት አንዱ ዓላማ ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት መሆኑ ይጠቀሳል:: ሆኖም ካሳለፈነው ሰኞ ጀምሮ በየክፍያ ማዕከሎቹ የታዩት ረዣዥም ሰልፎች በደንበኞች ዘንድ የተሻለ ጠብቀው የባሰ ማጋጠሙ ግራ አጋብቷቸዋል:: በሳሪስ የክፍያ ማዕከል ረዥም ሰልፍ ላይ የነበሩ ተገልጋይ የገጠማቸውን ነገር ‹‹ትሻልን ትቼ ትብስን አገባሁ›› በማለት ገልጸውታል::

በዚህ የክፍያ ሥርዓት አንድ ደንበኛ በሦስት ደቂቃዎች ተስተናግዶ መሄድ የሚቻለበት አሠራር የተቀረፀ ቢሆንም፣ በአገልግሎቱ መጀመር ከተበሰረ የመጀመሪያው ሳምንት ላይ የታየው መጨናነቅ የተፈጠረበት የራሱ ምክንያት አለው ተብሏል::

ከዚህም ሌላ አገልግሎቱን ለማግኘት የግድ ደንበኛው ራሱ መገኘት አለበት መባሉ አግባብ እንዳልሆነ የጠቀሱ ተገልጋይም፣ ‹‹የቀበሌ መታወቂያ የሌለው ደንበኛ አለ፤›› ያሉ አንድ አስተያየት ሰጪ፣ የተጠቀምንበትን ለመክፈል የተጠየቅነው ቅድመ ሁኔታ የበለጠ እንድንጉላላ አድርጐናል ብለዋል::

መታወቂያ ለማውጣት እንኳን ምቹ ሁኔታ የለም ያሉት አስተያየት ሰጪው፣ አሠራሩ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት እንዲህ ያሉ ሁኔታዎች ሊታዩ ይገባ ነበር ሲሉ ተችተዋል::

በሌላም በኩል አንድ ደንበኛ ራሱ ካልመጣ

የሚለው ጥያቄ እንዳሳሰባቸው የገለጹት እኒሁ አስተያየት ሰጪ፣ ‹‹እኔ የመስክ ሥራ እወጣለሁ:: ለዚህ ጊዜ የግድ ባለቤት ካልመጣ ከተባለ እኔ ሥራዬን ትቼ ልመጣ ነው?›› በማለት እንዲህ ዓይነቱ አሠራር ሊስተካከል ይገባል ብለዋል::

ሌላ አስተያየት ሰጪ ደግሞ መንግሥት ይህንን አሠራር ተግባራዊ ከማድረጉ በፊት ለተጠቃሚዎች በቂ ግንዛቤ ማስጨበጥ ነበረበት ይላሉ::

አሁን የተመለከቱት ሰልፍ ፈጣን አገልግሎት እየተሰጠ አለመሆኑን የሚያሳይና ደንበኛው እንዲሰላች መደረጉ ተገቢ አለመሆኑን ገልጸው፣ ሁልጊዜ አዲስ አገልግሎት ሲጀመር የተወሰነ ችግር ሊኖር እንደሚችል ግን ተናግረዋል:: እኒሁ አስተያየት ሰጪ ሰሞኑን የተመለከቱት ሰልፍ ግን ከቀድሞው የባሰ ይሆናል ብለው እንዳልጠበቁም ተናግረዋል::

አንዲት ወይዘሮ እንደገለጹት ደግሞ ሰልፉ በጣም አሰልች እንደሆነና ሰኞ ዕለት ጠዋት የውኃ ሊከፍሉ ሄደው በአዲሱ አሠራር መሠረት መታወቂያ፣ የውኃ፣ የመብራትና የስልክ ውል ፎቶ ኮፒ እንደሚያስፈልግ ተነግሯቸው ተመልሰዋል:: ከሰዓት በኋላ ደግሞ የተጠየቁትን ፎቶ ኮፒ አድርገው ሲመለሱ፣ ‹‹አሁን አንሠራም ለዛሬ በቃ እስከ ሐሙስ ድረስ መክፈል ትችላላችሁ፤›› መባላቸውን ተናግረዋል:: ረቡዕ ዕለት ሲሄዱ ደግሞ ሰልፉ በጣም አሰልች ቢሆንም፣ ወረፋቸውን ጠብቀው ወደ መሃል አካባቢ ሲደርሱ እስከ የካቲት 30 ቀን 2005 ዓ.ም. ድረስ መክፈል ስለምትችሉ አትጨናነቁ ተብለው መመለሳቸውን ይገልጻሉ::

ወይዘሮዋ በዚህ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ አሁንም ሥጋት እንዳለባቸው ይናገራሉ:: ‹‹የውኃ መክፈያ ጊዜው አልፏል፤ ስለዚህ ውኃው እንዳይቆረጥ እሰጋለሁ:: የመብራት ተራችን ደግሞ ወር በገባ ከ1 እስከ 5 ነው:: ስለዚህ እንዴት ነው የምናደርገው? እኔ እንደ መፍትሔ የማስበው ሁሉንም ሰው አሁን እናስተናግዳለን ከማለት ይልቅ፣ ሁሉም በፊት በሚከፍልበት ቀን ተራውን ጠብቆ መክፈል የሚችልበትን አሠራር ቢዘረጉ መጨናነቁን ሊያረግበው ይችላል፤›› የሚል አስተያየታቸውን ሰጥተውናል::

ይህንን ፕሮጀክት ተግባራዊ በማድረግና የክፍያ ሥርዓቱን እያስፈጸመ ያለው የጂሲኤስ የተባለው ኩባንያ፣ አዲስ ሥራ ሲጀመር አንዳንድ ችግር ሊያጋጥም ቢችልም አሁን የተፈጠረው መጨናነቅ ግን የራሱ የሆነ ክስተት አለው ብሏል:: የችግሩ አንዱና ዋናው ምክንያት ይህ አገልግሎት እንደሚጀመር ሲታወቅ ሦስቱም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ቀደም ብለው ይሰበስቡ የነበረውን ክፍያ በማቆማቸው ነው ብሏል ኩባንያው:: ይህም በመሆኑ የሦስቱም መሥርያ ቤቶች ተገልጋዮች የምንከፍልበት ቀን የሚያልፍ ከሆነ አገልግሎቱ ይቋረጥብናል በማለት አብዛኛው ተገልጋይ ወደክፍያ ማዕከሉ በመምጣቱ የተፈጠረ ጭንቅንቅ መሆኑን ኩባንያው ገልጿል::

ይህንን የተፈጠረውን ችግር በመረዳትም ደንበኞች ተረጋግተው እንዲከፍሉ በተለይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽንና የውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ለደንበኞቻቸው ሰጥተውት የነበረውን የመጨረሻ የክፍያ ጊዜ

ከጅማሮው ፈተና የገጠመው አዲሱ የቢል ክፍያ ሥርዓት

ለአሥር ቀናት አንዲራዘም አድርገዋል::

ይህም ዕርምጃ ደንበኞች ያለፈው ወር ሒሳባቸውን ተረጋግተው እንዲከፍሉ ስለሚያደርግ አሁን የታየው መጨናነቅ ይቀንሳል የሚል እምነት አላቸው::

ችግሩን ለማቃለል በተለይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሥልጣን ከ26 እስከ 30 ባለው ጊዜ ይከፍሉ የነበሩ እስከ የካቲት 10፣ ከ1 እስከ 5 ይከፍሉ የነበሩ እስከ የካቲት 15፣ ከ5

በአንዳንድ የክፍያ ማዕከሎች ተዘዋውረን በመቶዎች የሚቆጠሩ ደንበኞች ረዥም ሰልፍ ይዘው ወረፋ በመጠበቅ ለሰዓታት መቆማቸውን መታዘብ ተችሏል

እስከ 10 ይከፍሉ ለነበሩ እስከ የካቲት 20፣ ከ11 እስከ 15 ይከፍሉ ለነበሩ ደግሞ እስከ የካቲት 25 ቀን 2005 ዓ.ም. እንዲከፍሉ የጊዜ ማራዘሚያ አድርጓል::

ከዚህ በኋላ በየክፍያ ማዕከላቱ የሚስተናገዱ ደንበኞች ቀድሞ ይገለገሉበት በነበረው የክፍያ ጊዜ ጠብቀው መሆን እንደሚኖርበትም አሳስቧል::

በዚህም መሠረት የክፍያ ጊዜያቸውን ጠብቀው የሚመጡ ደንበኞች ብቻ የሚስተናገዱ መሆኑን ያሳሰበው ኮርፖሬሽኑ፣ የኤሌክትሪክ ቅድሚያ ክፍያ ካርድ ተጠቃሚዎች ግን በቀድሞዎቹ የኮርፖሬሽኑ የክፍያ ማዕከላት እንደሚስተናገዱ ገልጿል:: በተመሳሳይም የአዲስ አበባ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ያለፈውን ወር የአገልግሎት ክፍያ በአሥር ቀናት ማራዘሙን አስታውቋል::

ወደ ክፍል-1 ገጽ 20 ዞሯል

በዳዊት ታዬ

በኢትዮጵያ የወጪ ንግድ እንቅስቃሴ ዙሪያ የሚታዩ ክፍተቶች ስለመኖራቸው በተደጋጋሚ ሲጠቀስ ቆይቷል:: በወጪ ንግድ የተሰማሩ ኩባንያዎችም የሚፈልጉትን ያህል ለመሥራት የተለያዩ መሰናክሎች አሉብን በማለት የሚያቀርቧቸው በርካታ ምክንያቶች አሉ::

ከወጪ ንግድ መገኘት የሚገባውን ያህል ገቢ ያለመገኘቱ ደግሞ በዘርፉ የተሰማሩ ኩባንያዎችን ስለማሳሰቡ በተለያዩ አጋጣሚዎች ተገልጿል:: አሁንም በዚህ ዘርፍ አሉ የሚባሉ ክፍተቶችን ለመቅረፍ ካልተቻለ ችግሩ ሊቀጥል እንደሚችል እየተነገረ ነው:: ከዚህ ስሜት በመነሳት ባሳለፍነው ማክሰኞ በኢትዮጵያ የወጪ ንግድ እንቅስቃሴ ዙሪያ አንድ የዳሰሳ ጥናት ቀርቦ ነበር:: የዳሰሳ ጥናቱ የተካሄደው በኢትዮጵያ የንግድ ምክር ቤትና በመንግሥትና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረክ ጽሕፈት ቤት በኩል ነው:: ይኸው የዳሰሳ ጥናት በ3ኛው የቻምበር ፎረም ላይ ቀርቧል:: ዘርፉን ለማሳደግ መንግሥት የወሰዳቸውን የተለያዩ ዕርምጃዎች በተለያዩ የንግድ ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል:: ሆኖም በግሉ ዘርፍ በኩል ያሉ ችግሮች አሁንም ያለመፈታታቸውን የዳሰሳ ጥናቱ አመልክቷል::

ኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት እንዲሁም በወጪ ንግድ ፈጣን የሆነ ዕድገትን እያስመዝገበች መሆኑን የተለያዩ መረጃዎች እንደሚያመለክቱ በመጥቀስ የሚጀምረው

የዳሰሳ ጥናቱ፣ መንግሥትም ከኤክስፖርት ዘርፍ የሚያገኘውን ገቢ በየዓመቱ እየጨመረ እንዲሄድ ብቻ ሳይሆን የሚላከው ምርትም በዓይነቱና በብዛቱ እየጨመረ እንዲሄድ መፈለጉንም አያይዞ ገልጿል::

ከግብርና ግብይት ስትራቴጂውም ሆነ ከወጪ ንግድ ገቢ አስገኚ ምርቶች ውስጥ ትልቁን ድርሻ የተሰጣቸውና በመንግሥት የቅርብ ክትትል የሚደረግባቸው እንደ ቡና፣ ቅባት እህሎችና ጥራጥሬ፣ ቆዳና የቁም እንስሳት ቀዳሚ እንደሚሆኑ አመልክቷል::

እነዚህን ምርቶች የወጪ ንግዱ ደጀን ያደረገው መንግሥት፣ ለአብነት ከቡና ብቻ በ2007 ዓ.ም. ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ እንደሚጠብቅ አስታውሷል:: ከቡና የወጪ ንግድ በ2006 ዓ.ም. 1.5 ቢሊዮን ዶላር፣ በ2005 ዓ.ም. ደግሞ 1.2 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ይጠብቃል:: ኢትዮጵያ ወደ ውጭ የምትልካቸው የምርት ዓይነቶች በብዛትም በዓይነትም እየጨመሩ መሆናቸው የማያከራክር መሆኑን የሚጠቅሰው ይኸው ጥናት፣ ቀደም ሲል ቡና እስከ 75 በመቶ የሚደርሰውን ድርሻ ይይዝ የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ግዜ ግን ይህ የድርሻ መጠን በእጅጉ ቀንሷል ብሏል:: ይልቁንም የቆዳ ምርቶች፣ የቁም ከብት፣ የአበባ ምርት እንዲሁም ሰሊጥ በተለያየ መጠን ወደ ውጭ በመላክ ላይ የሚገኙ መሆኑን የዳሰሳ ጥናቱ አመላክቷል::

እንደ ዶላሩ ሁሉ የሚላከውም የምርት

የኢንቨስትመንትና የወጪ ንግዱ አሁንም ችግር ውስጥ ነው

የንግድ ኅብረተሰቡ መፍትሔ ሐሳቦች አቅርቧል

Page 11: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 11 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታ

ወቂያ

በብርሃኑ ፈቃደ

መንግሥት የአገሪቱን ጠቅላላ ኢኮኖሚ የሚለካበትን፣ ብሔራዊ ኢኮኖሚ አካውንት ቀመር መነሻ ዘመን ዱሮ ከነበረበት 1992 ዓ.ም. ወደ 2003 ዓ.ም. ማምጣቱን ተከትሎ የስታቲስቲክስ ለውጥ ለማድረግ ተገድዷል:: በዚህ መሠረት የ2004 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ያድጋል ከተባለው የ11 በመቶ ዕድገት ወደ 8.5 በመቶ ዝቅ ብሏል::

እውነታው ያድጋል የተባለበት የግመታ ቁጥር መጋነን እንጂ ኢኮኖሚው አሁም ፈጣን ዕድገት ውስጥ እንደሚገኝ መንግሥት አስታውቋል:: ይህን ቢልም ቅሉ፣ አገሪቱ ያስመዘገበችው ጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት ዕድገት የአንድ በመቶ ቅናሽ በማሳየቱ ‹‹በመጪዎቹ ሦስት ዓመታት አሰልሰን በመሥራት ጉድለቱን እናካከስሳለን›› ማለቱ ግን መንግሥትን አስተችቶታል::

‹‹ጉድለቱ የታየው በቁጥር ነው:: የቀድሞው ስታቲስቲክስ ከፍ ያለ ነበር:: አዲስ በተሠራው ሥሌት ደግሞ ለእውነት የቀረበ አሃዝ በመገኘቱ ትንበያውን ዝቅ አደረገው:: ይህ ማለት ግን አገሪቱ በወቅቱ ያመረተችው ምርት በአንድ በመቶ ቀንሶ ነበር ማለት አይደለም፤›› በማለት መንግሥትን የሚሞግቱ ማብራርያዎችን ሪፖርተር ያነጋገራቸው ባለሙያዎች ጣል ያደርጋሉ::

መከራከርያው ምን ይሁን መንግሥት ለኢኮኖሚው ትንበያ የሚውሉ አሃዞች ወይም ስታቲስቲካዊ መረጃዎች እውነታውን በተዓማኒነት ያሳዩለት ዘንድ ከዚህ ቀደም ለኢኮኖሚ ትንበያ የሚጠቀምበት መነሻ ዓመት ወይም ቋሚ ዓመት መቀየሩን አስታውቋል:: ቋሚ ዓመት (Base year) ለኢኮኖሚ አካውንት መረጃዎች ወሳኝ ነው:: ለውጡም እንዲሁ አስፈላጊ ነበር:: ቢያንስ በየአምስት ዓመቱ የብሔራዊ ኢኮኖሚ መረጃዎች የተንተራሱበት ቋሚ ዓመት ሊለወጥ እንደሚገባው ቢታመንም መንግሥት ከ11 ዓመት በኋላ ቀይሮታል::

ብሔራዊ የኢኮኖሚ አካውንት ሥርዓት በኢትዮጵያ የአራት አሠርት ዕድሜ እንዳለው ይታመናል:: በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት

ሚኒስቴር፣ የብሔራዊ ኢኮኖሚ አካውንት ዳሬክተሩ አቶ ልዑልሰገድ ደቻሳ እንደሚገልጹት፣ የዚህ ሥርዓት መኖር ከዋና ዋና ዓላማዎቹ ውስጥ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን በቅርበት ለመከታተል ማስቻሉ፣ የማክሮ ኢኮኖሚያዊ ትንታኔዎችን

ለመስጠት ማብቃቱ፣ ኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን ለመቅረፅና ውሳኔ ለመስጠት ከማስቻሉ በላይ ዓለም አቀፋዊ ንጽጽሮችን ለማድረግ ማገዙ እንደሚገኙበት አስረድተዋል::

ለብሔራዊ ኢኮኖሚ አካውንት መረጃዎች ምሰሶ የሆነውን ቋሚ ዓመት መለወጥ ‹‹በኢኮኖሚው ውስጥ የሚታየውን ትክክለኛ ወይም እውነተኛ የምርትና አገልግሎት መጠን፣ የአወቃቀር ለውጥ እንዲሁም ዕድገት የሚያሳዩ ዋና ዋና ኢኮኖሚ አመላካቾች የሚሰሉበትን ማነጻጸርያ መነሻ (ቋሚ) ዓመት በአዲስና ቅርብ በሆነ ዓመት መቀየር ነው፤›› የሚለው የሚኒስቴሩ መረጃ፣ የተባበሩት መንግሥታትን የብሔራዊ ኢኮኖሚ አካውንት ሥርዓትን መሠረት በማድረግ፣ የዓለም ገንዘብ ድርጅት፣ መንግሥት ራሱ በቀጠራቸው የውጭ ቴክኒክ አማካሪዎችና በየወቅቱ በሚመጡ ባለሙያዎች እገዛ አዲሱን ዓመት 2003 እንዲሆን ማድረጉን ያስታወቀው ባለፈው ጥር 27 ቀን 2005 ዓ.ም. ነበር::

የመነሻ ዓመቱን ለውጥ ተከትሎ ከ2004 ይልቅ 2003 የተሻለ ኢኮኖሚያዊ አሃዝ ያስመዘገበ ነበር:: ባለፉት ስምንት ዓመታት ከተመዘገበው የኢኮኖሚ ዕድገት አኳያም የ2004 ዓ.ም. ኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት በዚህ ግመታ ሳቢያ ዝቅተኛው ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን፣ በአማካይ 11 በመቶ ዕድገት ሲመዘገብ መቆየቱን መንግሥት አስታውቆ በ2004 ግን ወደ 8.5 በመቶ መውረዱን አማካዩም 10 በመቶ በመሆኑን ይፋ አድርጓል::

መንግሥት የግብርና ዘርፉ በአማካይ በ9.6 በመቶ እያደገ መምጣቱን ቢያስታውቅም፣ በግመታው መሠረት የግብርናው ኢኮኖሚ ያደገው ግን በ4.9 በመቶ እንደነበርም ገልጿል:: ኢንዱስትሪ በ13.6 በመቶ ሲያድግ፣ አገልግሎት በ11 በመቶ አድጓል:: በዚህም ኢንዱስትሪ ከሁሉም ልቆ ተገኝቷል:: ምንም እንኳ ግብርና ከዋና ዋና ክፍለ ኢኮኖሚ ያነሰ ዕድገት ቢያሳይ፣ አሁንም ድርሻው ግን 44 በመቶ ነበር:: ከ2003 ዓ.ም. አኳያ የአንድ በመቶ ቅናሽ አለው:: ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት አኳያ፣ የአገሪቱ አጠቃላይ ፍጆታ (የመንግሥት ሰባት በመቶ፣ የግል 76.5

የኢኮኖሚያችን ጉዞ ከአምናው ሀቻምናበመቶ) 83.5 በመቶ ሲያስመዘግብ፣ በ2003 የተመዘገበው ደግሞ 87 በመቶ ነበር፤ ይህም ግን መነሻ ዓመቱ ከመከለሱ በፊት 91 በመቶ እንደሚሆን ታስቦ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ::

ኢትዮጵያ በ2004 ዓ.ም. ያስመዘገበችው ዝቅተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት ሲታይ ለዝቅተኛነቱ ምክንያት ከተደረጉት ውስጥ ግብርና ዋናው ሆኗል:: ‹‹በግብርና ኢኮኖሚው በሰብል ምርትና ምርታማነት ላይ የታየው አነስተኛ አፈጻጸም በዋናነኛነት የሚጠቀስ ሆኗል፤›› ያለው ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር፣ ከአጠቃላይ የሰብል ምርት የሚገኘው ተጨማሪ እሴት ከጠቅላላው አገር ውስጥ ምርት በአማካይ እስከ 30 በመቶውን የሚሸፍን በመሆኑ ነው ይላል:: በ2003 ዓ.ም. የተገኘው ጠቅላላ የሰብል ምርት (በበልግና በመኸር ወራት ከተዘራው) 221.82 ሚሊዮን ኩንታል ነበር:: ይህ ምርት በ2004 በምን ያህል መጠን እንደቀነሰ የሚያመላክቱ መረጃዎች ገና እየወጡ ቢሆንም፣ በግብርና ዘርፍ ይገኛል ተብሎ ይጠበቅ የነበረው 9.6 በመቶ ዕድገት ወደ 4.9 በመቶ መውረዱ ምክንያት ተደርጓል ማለት ነው:: የባለሙያዎቹ መከራከርያ ግን ቋሚ ዓመቱ በመቀየሩ ምክንያት ምርት ቀንሷል ሊባል አይችልም፣ ምክንያቱም የተለያየ የትንበያ መንገድ ተጠቅመናልና የሚል ነው::

ይህም ቢባል ግን መንግሥት የቋሚ ዓመቱን መቀየሩ ግን የኢኮኖሚው ዕድገት ከታሰበው ዝቅ እንዲል ማድረጉ አያጨቃጭቅም:: ሌላው መንግሥት በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ ላይ ያሰፈራቸው አሃዞች ላይ ለውጥ የማያደርግ መሆኑን ማሳወቁ ነው:: በዝቅተኛና በከፍተኛ የዕድገት ማዕቀፍ ውስጥ እንዳስቀመጠው ኢትዮጵያ በየዓመቱ ዝቅ ሲል 11 በመቶ ከፍ ሲል 14 በመቶ ታድጋለች:: ከቋሚ ዓመቱ ለውጥ ጋር ተያይዞ ወደ 8.5 በመቶ ዝቅ ያለ የዕድገት መጠን በአገሪቱ እንደተመዘገበ አመላክቷል:: ዝቅተኛውም ከፍተኛውም ባሉበት መጠን ይቀጥላሉ (11 እና 14 በመቶ ሆነው) እንጂ አልቀንስም ያለው መንግሥት፣ እንዲያውም የቀነሰብኝን አንድ በመቶ አካክሳለሁ ባይ ነው::

በአጠቃላይ ግን በ2003 ዓ.ም. መነሻነት የተቃኘው ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በ2004 ከተመዘገበው በአብዛኛው የተሻለ ሆኖ እንዳለፈ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር መረጃዎች ይጠቁማሉ::

የመነሻ ዓመቱን ለውጥ ተከትሎ ከ2004 ይልቅ 2003 የተሻለ ኢኮኖሚያዊ አሃዝ ያስመዘገበ ነበር:: ባለፉት ስምንት ዓመታት ከተመዘገበው የኢኮኖሚ ዕድገት አኳያም የ2004 ዓ.ም. ኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት በዚህ ግመታ ሳቢያ ዝቅተኛው ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን፣ በአማካይ 11 በመቶ ዕድገት ሲመዘገብ መቆየቱን መንግሥት አስታውቆ በ2004 ግን ወደ 8.5 በመቶ መውረዱን አማካዩም 10 በመቶ በመሆኑን ይፋ አድርጓል::

Page 12: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 12 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

በብርሃኑ ፈቃደ

ጁልፋር ግዙፍ የፋርማሲቱካል ኢንዱስትሪስ ግሩፕ (ገልፍ ፋርማሲቱካል ኢንዱስትሪስ) ካካተታቸው አንዱ ለመሆን የበቃውና አዲስ አበባ የከተመው ጁልፋር ፋርማሲቱካል የግል ኩባንያ ነው:: በ40 ሺሕ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ገርጂ አካባቢ የሰፈረው ጁልፋር በዩናይትድ ዓረብ ኤምሬትስ ንጉሣውያን ቤተሰቦችና በኢትዮጵያዊው ባለሀብት የጋራ ኢንቨስትመንት የተገነባ ነው::

ጁልፋር ኢትዮጵያ በንጉሣውያኑ የ55 በመቶ እንዲሁም በሜዲቴክ አትዮጵያ የ45 በመቶ ደርሻ፣ 170 ሚሊዮን ብር ኢንቨስት ተደርጎበት በአንድ ዓመት ውስጥ መጠናቀቁ ታውቋል:: ጁልፋር መድኃኒትና የሕክምና መገልገያዎችን አምራች ኩባንያ እንደመሆኑ፣ በኢትዮጵያ በሦስት ዓይነት መንገድ መድኃኒት ለማምረት የመጀመርያውን ምዕራፍ አጠናቅቋል:: 25 ሚሊዮን የብልቃጥ ሽሮፕ፣ 500 ሚሊዮን ክኒኖችና 200 ሚሊዮን ካፕሱል መድኃኒቶችን ለማምረት አቅም ያለው ይህ ፋብሪካ፣ ከሰባቱ የአንዱ ኤምሬት፣ ራስ አል ኬይማህ ገዥና የጁልፋር የቦርድ ሊቀመንበር፣ ሼክ ሳቅር ቢን ሞሐመድ አል ቃሲሚና የውጭ ንግድ ሚኒስቴሯ ባለቤታቸው ሼክ አሉብና አልቃሲሚ፣ ሌሎችም ልዑካን ከቤተ መንግሥት እስከ ፋብሪካው ቅጥር ግቢ ቆይታ አድገው ነበር::

ባለፈው ማክሰኞ ምሽት ፕሬዚዳንት ግርማ በቤተ መንግሥት ባደረጉላቸው ግብዣ ወቅት አብረዋቸው የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖምን ጨምሮ ሌሎች ባለሥልጣናትም ታድመው ነበር:: በዩናትድ ዓረብ ኤምሬትስ የኢትዮጵያ ቆንጽላ ጄኔራል አቶ ምስጋኑ አረጋም ተገኝተዋል:: ዶክተር ቴድሮስ ንጉሣውያኑን ፈገግ ያሰኘ፣ ባለብዙ አፉን (ቋንቋ ተናጋሪውን) ፕሬዚዳንት ግርማን ያስደሰተ የዓረብኛ መግቢያና መውጫውን ያደረገ የግብዣ ንግግር በቤተ መንግሥት አድርገው ለእንግዶቹ ምቾት ሰጥተው ነበር:: ‹‹አሰላም አሌይኩም፣ ራህማቱላሂ ወበረካቱ፣›› በማለት የጀመሩት ዶክተር ቴድሮስ ‹‹ካለስ ማይ አራቢክ››ን አስከትለው የአረብኛ ንግግራቸው እስከዚያች መሆኗን ጠቁመው ባደረጉት ንግግር፣ ንጉሣውያኑ በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ መፈለጋቸውን በሰሙ ጊዜ ለመቀበል ያልቻሉ መሆናቸውን ገልጸው፣ ነገር ግን እውነት ሲሆን ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጨምር የማሳያ ኢንቨስትመንት መሆኑን በማረጋገጥ መናገራቸውን ዶክተር ቴድሮስ አስታውቀዋል:: እንዲያም ሆኖ ጁልፋር እዚህ ያቆመው ፋብሪካ የዓለም የጤና ድርጅትን

መስፈሮቶች አሟልቶ እንዲገኝ ሲሉም ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል:: በመዝጊያቸውም ‹‹ቪቫ፣ ሹክረል›› የሚሉ ቃላትን ጣል ሲደርጉ ሞቅ ያለ ጭብጨባ ተለግሷቸዋል::

ሼክ ሳቅር ቢን ሞሐመድ አል ቃሲሚ ሲናገሩ ጁልፋር ኢትዮጵያ እዚህ የተቋቋመው ኢትዮጵያን የአፍሪካ ማዕከል ለማድረግ በማሰብና፣ በመላ አፍሪካ ያለውን የገበያ ድርሻ በዚሁ በጁልፋር ኢትዮጵያ በኩል ለማዳረስ ሲሆን፣ ከዚያ ባሻገር አገራቸው ኤምሬትስ ለኢትዮጵያ ተምሳሌት መሆን የምትችልባቸው መስኮችም እንዳሉ ጠቅሰዋል:: በኤርፖርቶች፣ በወደቦች፣ በሎጂስቲክስ፣ በቴሌኮሙዩኒኬሽን፣ በማኑፋክቸሪንግና በንግድ ዘርፍ ያላት ስኬታማ ታሪክ ለኢትዮጵያ አብነት ያለው እንደሆነ

ንጉሣውያኑ ኤምሬቶች ጁልፋርን ወደ አዲስ አበባ አመጡ

ለማስፋፍያ 20 ሚሊዮን ዶላር ተይዞለታል

ጁልፋር ኢትዮጵያ በንጉሣውያኑ የ55 በመቶ እንዲሁም በሜዲቴክ አትዮጵያ የ45 በመቶ ደርሻ፣ 170 ሚሊዮን ብር ኢንቨስት ተደርጎበት በአንድ ዓመት ውስጥ መጠናቀቁ ታውቋል

ፎቶ በ

ሪፖርተ

ር/ናሆ

ም ተ

ስፋዬ

ተናግረዋል:: በትልቅነቱና በዘመናዊነቱ የሚታወቀውን

ጁልፋር መድኃኒት ፋብሪካን ንጉሣውያኑ እዚህ ሲያቆሙ በአፍሪካ የመጀመርያቸው ነው ያሉት አቶ ምስጋኑ፣ ጁልፋር ፋብሪካውን ከመክፈቱም ቀድሞ የኢትዮጵያን የመድኃኒትና የሕክምና መሣርያ ገበያ ያውቀው እንደነበርና ለሌሎች ኩባንያዎች መምጣት በር የሚከፍት እንደሆነ በመግለጽ ነው::

የጁልፋር ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አይማን ሳህሊ ለጋዜጠኞች ሲናገሩ፣ ምንም እንኳ መድኃኒቶቹ እዚህ በመመረታቸው ወጪ የሚቀንሱና ለተጠቃሚውም ዋጋቸው ተስማሚ እንደሚሆን ቢጠበቅም፣ የዋጋ ተመኑን የሚያወጣው ጤና ጥበቃ በመሆኑ መሸጫ ዋጋውን እሱ እስኪያወጣ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል:: ለመድኃኒቶቹ የሚሆን ጥሬ ዕቃ ከውጭ የሚገባ ሲሆን፣ በአቅርቦት ረገድ ምንም ችግር እንደማይኖር አስታውቀዋል::

የሜድቴክ ኢትዮጵያ ዋና ኃላፊና የጁልፋር ኢትዮጵያ ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሞሐመድ ኑሪ፣ ከጁልፋር ጋር በጋራ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከመግባታቸው በፊት በየዓመቱ እስከ 12 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ መድኃኒቶችን ያስመጡ እንደነበር ገልጸዋል:: እስካሁን 170 ሚሊዮን ብር ኢንቨስት የተደረገበት ጁልፋር ኢትዮጵያ፣ አሁን ከሚያመርታቸው ውጭ የሆኑትንና ለውጭ ገበያ ትኩረት የሚያደርግበትን የማስፋፍያ ፕሮጀክት ለማካሄድ ከአዲስ አበባ አስተዳደር የ25 ሺሕ ካሬ ሜትር ቦታ እስኪሰጠው እየተጠባበቀ ሲሆን፣ መሬቱ ሲገኝም በሁለት ዓመት ውስጥ በ20 ሚሊዮን ዶላር ወይም በ350 ሚሊዮን ብር ገደማ ፋብሪካውን እንደሚገነባ አስታውቀዋል::

ከአንድ ወር በኋላ ለገበያ የሚቀርቡት የመድኃኒት ዓይነቶች 60 ያህል ጠቅላላ አንቲባዮቲክስ ላይ ያተኮሩና ከፍተኛ እጥረት አለባቸው ተብለው የሚታሰቡ ሲሆኑ፣ ማስፋፊያው ሲገነባ ቀድሞ በሜድቴክ ይመጡ ከነበሩ ከ243 መድኃኒቶች ውስጥ ከ80 እስከ 90 በመቶ በላይ እንደሚያመርት ይጠበቃል:: አብዛኛውን ለውጭ ገበያ የሚያተኩረው የሁለተኛው ምዕራፍ ፕሮጀክት ጁልፋር አብዛኛው ገበያው አፍሪካ በመሆኑ ከዱባይ ከመላክ ይልቅ ኢትዮጵያን ማዕከል አድርጎ እንደኬንያ፣ ታንዛንያ፣ ናይጄርያ ያሉትን እንደሚያዳርስ ይጠበቃል:: አይቪ ፍሉድ፣ ሄሞዲያሊሲስ፣ ኢንጄክቴብልስ፣ ስሞል ቮልዩም ፓረንታራልስና ሌሎች እስካሁን እዚህ የማይመረቱ መድኃኒቶች ለማምረት መዘጋጀቱን ዶክተር ሞሐመድ ተናግረዋል::

ኤምሬቶች ለሚያካሂዱት የንግድና የኢንቨስትመንት ሥራ መንግሥት ተደራራቢ ቀረጥን ከማስቀረትና የኢንቨስትመንት ዋስትና ከመስጠት ባሻገር ለፋብሪካው የሚያገለግሉ ከ90 በላይ ልዩ ልዩ ማሽነሪዎች ከቀረጥ ነፃ ዕድል ሰጥቷል:: ይህ ሁሉ ግን አሁን ኢንቨስት የተደረገው

በሌሎች የግል ኩባንያዎች ኢንቨስት ከተደረገው የበለጠ ሆኖ ሳይሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት ‹‹ማሳያ›› በመሆኑ ነው:: ይኸውም በመንግሥት ደረጃ ንጉሣውያኑ ባለሀብቶች ኢንቨስት ያደረጉበት ፕሮጀክት ኢትዮጵያን ለማስተዋወቅ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታው ከሁሉም ስለሚልቅ ነው:: በተደራራቢ ቀረጥና በኢንቨስትመንት ዋስትና ረገድ በቅርቡ ስምምነት ተደርጎባቸው ለፊርማ እንደሚበቁ አቶ ምስጋኑ አስታውቀዋል::

ሌላኛው የኢንቨስትመንት ማሳያ በመስቀል አደባባይ እየተገነባ የሚገኘው የአኮር ካራፊ ሆቴል ግንባታ ሲሆን የዩናይትድ ዓረብ ኤምሬትስ ባለሀብት እየተሠራ ያለ፣ ባለአምስት ኮከብ ደረጃ እንዲኖረውም ለማስፋፋት እየሠራ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ ምስጋኑ፣ ኢንቨስተሩ በሆቴል ዘርፍ ትልቅ ከሚባሉ ኤምሬቶች መካከል የሚመደብ እንደሆነም ገልጸዋል::

ጁልፋር በአፍሪካ እዚህ ሲክፍት የመጀመርያው ሲሆን፣ በመካከለኛው ምሥራቅ 12 ያህል የመድኃኒት ፋብሪካዎች ሲኖሩት፣ የመድኃኒት ጥሬ ዕቃዎች በማምረትም በኤምሬትስ ብቸኛው ነው:: እ.ኤ.አ. በ1980 የተመሠረተው ጁልፋር፣ በ2011 ከአንድ ቢሊዮን በላይ ሽያጭ ያስመዘገበና ከ800 በላይ መድኃኒቶችን የሚያመርት ኩባንያ ነው:: በዩናይትድ ኤምሬትስ ያሉትን 12 ያህል ፋብሪካዎች ጨምሮ በኢትዮጵያ፣ በሳኡዲ ዓረቢያና በአልጄሪያ ፋብሪካዎችን ለመገንባት ዕቅድ ይዞ በአፍሪካ የኢትዮጵያውን ጁልፋር ቀዳሚ አድርጎታል::

በተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ በሚገኘው ጁልፋር ከተባለ ኩባንያ ጋር በሽርክና የተገነባው ፋብሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በተገኙበት ጥር 29 ቀን 2005 ዓ.ም. ተመርቋል

Page 13: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 13 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታወቂያማስታወቂያማስታወቂያ

በናታን ዳዊት

በኢትዮጵያ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ደንበኞች ካላቸው አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ውስጥ ኢትዮ ቴሌኮምን የሚስተካከል ያለ አይመስለኝም:: እንደውም የለም ማለቱ ይሻላል:: ቴሌ በደንበኞች ብዛት ሰቃይ የተባለበቱ ምክንያት በዘርፉ ብቸኛ አገልግሎት ሰጪ በመሆኑ ብቻ ሳይሆን የቴሌን አገልግሎት መጠቀም ጊዜው የሚጠይቀው ወሳኝ ጉዳይ በመሆኑ ነው:: ከዚህ እሳቤ አንፃር የደንበኞቹ ቁጥር ከሌሎች ተቋማት በተለየ መበርከቱ ላይገርም ይችላል::

ወቅታዊ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በኢትዮጵያ የሞባይል ደንበኞች ቁጥር 20 ሚሊዮን ደርሷል:: በሌሎች የቴሌ አገልግሎቶች ተጠቃሚ የሆኑ ደንበኞች በሚሊዮን የሚቆጠሩ መሆኑ በኢትዮጵያ ከአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ውስጥ ተወዳዳሪ የሌለው እንዲሆን እያደረገው ነው ወይም ሆኗል:: የዘርፉ ብቸኛ ተዋናይ ሆኖ መገኘቱና በፍጥነት እየበረከቱ የመጡ ደንበኞቹ ቴሌን በየዓመቱ በቢሊዮኖቹ ላይ ቢሊዮን ብር እያስጨመረለት ነው:: ከዚህ በኋላም ይኸው የደንበኞች ቁጥር በእጥፍ እንደሚጨምር ሲታሰብ ደግሞ ቴሌ ገዝፎ ይታየናል:: የቴሌ ደንበኞችም ገቢውም እንዲሁ ከቀጠለ ምናልባት ደንበኞቹን በቅጡ ለማስተናገድ ፈተና ሊሆንበት ይችላል:: አሁን ባለው ደረጃ የሚታዩበት ክፍተቶች ደንበኞቹን ባሳደገ ቁጥር በጥራት የማገልገሉ ነገር ቢያሳስብ ተገቢ ነው::

ቴሌ የደንበኞቹን ቁጥር እንደዛሬ በሚሊዮን ደረጃ ሳያደርስ በመቶ ሺዎች የሚሆኑ ደንበኞች ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበሩበትን ክፍተቶች እናስታውሳለን:: የሞባይል አገልግሎት አንድ ብሎ ከተጀመረበት ጊዜ ወዲህ በአገልግሎት አሰጣጦቹ ላይ ብዙ ትችት ይቀርቡ ነበር:: በተለይ አንድ ደንበኛ የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን አሟላ

የቴሌ ነጥብ ተጋሪነት

በፊት ሲወተወትበት የነበረውን አካሄድ እየቀየረ መጥቷል:: አገልግሎቱን እየቀየረ ስለመሆኑንም ምልክት እያሳየ ሲሆን፣ እኛም እየተመለከትን ነው:: የዘገየ ቢሆንም ካለፈው ዓመት ወዲህ ብዙ የአገልግሎት ማሻሻያዎችን አድርጓል:: በቂ ነው ባይባልም ደንበኛን መሠረት ያደረጉ ለውጦች ታይተዋል:: ለተሻለ ለውጥ እየተንቀሳቀሰ ስለመሆኑም ሰምተናል:: ይህ ይደነቃል::

ከሁሉ በላይ ግን ካለፈው ዓመት ጀምሮ በተለያዩ የአገልግሎቶቹ ላይ ለውጥ ሲያደርግ፣ ከዚህም በኋላም ብዙ እንድንጠብቅ እያደረገን ነው:: በቅርብ ካሻሻላቸው አካሄዶቹ መካከል በጥቂቱ እንኳን ሁለትና ሦስት ሺሕ ብር የሚጠየቅበት ሲም ካርድ ዛሬ በ30 ብር ይገዛል:: ያውም በየሠፈሩ ባሉ መደብሮች ሳይቀር መገኘቱ በራሱ ትልቅ ነገር ነው::

በአጠቃላይ ዘርፉን በሞኖፓል የመያዙ ጉዳይ እንደተጠበቀ ሆኖ ከሲም ካርድ ችርቻሮ መውጣቱ፣ የቅድመ ክፍያ ካርድ ሽያጭን በግል ድርጅቶች በኩል ማካሄዱ፣ የቅድመ ክፍያ ሞባይል አገልግሎትን በቀላሉ ወደ ባለመስመር ስልክ መቀየር እንደሚችል ዕድል መስጠቱ፣ አንዳንድ ታሪፎችን ማስተካከሉ፣ በሞባይል የኢንተርኔት ተጠቃሚ መሆን እንድንችል ማድረጉና ወዘተ. ትልቅ ለውጥ ነው::

ኢቪዲኦ፣ ሲዲኤምኤ፣ የብሮድባንድ አገልግሎት ለማግኘት የነበረውን ቢሮክራሲ ማስቀረቱ፣ ከሞባይል አካውንት ላይ በቀላሉ ለሌላ ማካፈል ማስቻሉ፣ ለድኅረ ክፍያ ተጠቃሚዎች የድምፅ መልዕክት መስጫ አገልግሎት መጀመሩ፣ የቅርብ ጊዜ መልካም ዕርምጃዎቹና ወደ ተሻለ አሠራር እየገባ መሆኑን አመላካች ናቸው::

ሰሞኑንም የቅድመ ክፍያ የሞባይል ካርድ ተጠቃሚዎች በሞሉት የካርድ መጠን ቦነስ እየሰጠሁ ነው ማለቱ፣ ቴሌ ደንበኞችን እየሳበና የደንበኞቹንም ስሜት እያዳመጠ ስለመሆኑ ጠቋሚ ይሆናል:: እንዲህ ዓይነቱ ቦነስ መቀጠል አለበት:: በተለይ ጥሩ ደንበኞቹን ቢያንስ እንዲህ ባለው ነገር መደገፍ ከአንድ አገልግሎት ሰጪ የሚጠበቅ ነውና:: በሌሎች አገልግሎቶችም ላይ በተወሰነ ጊዜ ልዩነት ቦነስ ቢሰጥ አይጐዳም:: ደንበኛው ለቴሌ የሚኖረውም አመለካከት እንዲቀየር ያደርጋል::

በዚህ የሞባይል አገልግሎት ዙሪያ ዓለም የደረሰበትን ቴክኖሎጂ ቴሌ ራሱ በሚለቅልን ድረ ገጽ በቀላሉ የምንመለከተው በመሆኑ፣ አሁንም ለደንበኞች ፍላጎት እርካታ ብዙ መሠራት

ይኖርበታል:: በሚሊዮን የሚቆጠር ደንበኛ ይዞ የሚጓዝና በቢሊዮኖች ገቢ እየሰበሰበ ያለ ተቋም ብዙ ይጠበቅበታል:: በተለይ ጊዜው በቴሌኮም ኢንዱስትሪ በታገዙ ቴክኖሎጂዎች የተሳሰረ እንቅስቃሴ የሚደረግበት መሆኑና ይህ አገልግሎት ለሰከንድ እንኳን ቢስተጓጎል የሚፈጥረውን ቀውስ ከግምት ውስጥ በማስገባት ከመሠረተ ልማት ግንባታው ጐን ለጐን የአገልግሎት ጥራት ቅድሚያ ተሰጥቶት ካልተሠራበት ጉዳት ሊኖረው ይችላል::

የሞባይል አገልግሎት ወሳኝ የሆነበት ደረጃ ላይ ተደርሷል:: የኢንተርኔት አገልግሎት መሠረታዊ የሰው ልጅ ፍላጎት ሆኗል:: ንግድና ኢንቨስትመንት ከእነዚህ ቴክኖሎጂዎች ጋር ተሳስረዋል:: ሌላም ሌላም ሊጠቀስ ይችላልና ቴሌ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተወሰነ የጊዜ ልዩነት በተለያዩ አገልግሎቶች ላይ እያደረገ ያለውን ለውጥ ከዚህም በላይ ሊሄድበት ይገባል::

የደንበኞችንም ፍላጎት በቅርብ በማዳመጥ ለውጡን ፈጣን ማድረግ ተጨማሪ የገቢ ምንጮችን ማስፋፋት ስለመሆኑ ቴሌ ባይጠፋውም፣ ደንበኞቹ በሌሎች ዓለማት የሚገኙ ተገልጋዮች እያገኙ ካሉት አገልግሎት እኩል የሚጓዙበትን አሠራር በርትቶ ሊሠራበት ይገባል::

በዘርፉ ሁለት ሦስት ኩባንያዎች ቢኖሩ ደንበኞች የተሻለ አገልግሎት ያገኙ እንደነበር ቢታሰብም፣ የአገራችን ሁኔታ ግን ይህንን ባለመፍቀዱ ለዘርፉ ዕድገት ተመስጋኝም ተወቃሽም ቴሌ መሆኑን በመረዳት መሥራት ይጠበቅበታል:: ከዚህ አገልግሎት ጋር ተያይዞ የሚታየው የሞባይል ኔትወርክ ችግር ግን ቴሌ እያደረገ ያለውን ጥረት እየደገፈው ነው ማለት ግን አይቻልም:: ከፍተኛ ሊባል የሚችል የኔትወርክ ችግር አለ:: ደንበኞችን እያበዛ በመጣ ቁጥር ደግሞ ይህ የኔትወርክ የጥራት ጉዳይ የበለጠ ፈተና እየሆነ መምጣቱ አይቀርም:: ቴሌ ደንበኞች የማብዛቱን እንቅስቃሴውን በአቅሙ ልክ እስካላደረገ ድረስ ወይም እያሳደጋቸው ያሉትን ደንበኞች የሚያስተናግድ መሠረተ ልማት ማከናወን ካልቻለ፣ የደንበኞች ቁጥር ማብዛቱ ብቻውን ሙሉ ነጥብ አያሰጠውም:: በአንፃሩ ቴሌ እየጣለ የመጣውን ነጥብ እያነሳ፣ ነጥብ እየተጋራበት ያለውን ወቅታዊ እንቅስቃሴውን ግን ምስጋና መንፈግ መልካም ደንበኝነት ወይም ዳኝነት አይደለም::

ይባል የነበረው ቅድመ ሁኔታዎች አስገራሚ ነበሩ:: ካርታ ካልተያዘ የሞባይል መስመር ማግኘት ዘበት የነበረበትን ጊዜ አይተናል:: ሲም ካርድ ለማግኘት በሺዎች የሚቆጠሩ ብሮች ተጠይቀዋል:: በሞባይል ለመገልገል ዋስትና የሚያስፈልግ መሆኑን ጭምር የቀድሞ ተገልጋዮች ትውስታ ነው:: ከዚህም አልፎ ቴሌ ካስመጣሁት የሞባይል ቀፎ ሌላ መጠቀም አይቻልም ብሎ እንደፍላጎታችን የመረጥነውን የሞባይል ቀፎ መያዝ ያልቻልንበትን ወቅት እናስታውሳለን::

ይኼም ሆኖ የሞባይል ኔትወርክ ጉዳይ ያኔም አነጋጋሪ ነበር:: አሁንም አለ:: ቴሌ የሞባይል አገልግሎትን ለመጀመር ደፋ ቀና በሚልበት ወቅት ከዚያም ግልጋሎቱን ከጀመረ ወዲህ ደግሞ አንድ ሞባይል መስመር እንዲኖረው የሚፈልግ ደንበኛ ቴሌ አስቀምጧቸው የነበሩ ቅድመ ሁኔታዎችና የተጋነነው የአገልግሎት ዋጋው የማያስፈልግ መሆኑ በወቅቱ ተገልጾለታል:: አካሄዱንም እንዲያስተካክል ብዙ ውትወታ ነበር:: እንዲውም ከብዙ ትችቶችና ጉትጐታዎች ጐን ለጐን ጥሩ መፍትሔው ቴሌ በሞኖፖል ከያዘው ቢዝነስ ወጥቶ ሥራው በግል ኩባንያዎች ቢሠራ የሚለው ምክር ይታወሳል:: እንደ ዕድል ሆኖ ይህ የማይታሰብ ጉዳይ ነው ተብሏል:: መንግሥት በዚህ ከቆረጠና ቴሌን አላስነካም ካለ፣ አገልግሎቱን በአግባቡና በጥራት ይሰጠን የሚለው ጉዳይ የብዙዎች ስሜት ነው:: በተለይ ሚሊዮኖች የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚዎች ከመሆናችሁ ጋር ተያይዞ የቀድሞ ክፍተቶቹ ዛሬ እንዳይደገሙ ይፈለጋል:: በዚህም ነው ቴሌ ከአገልግሎት አሰጣጡ ጋር ተያይዞ ሲወቀስ የነበረው:: በአንፃሩ ቀድሞ የምንማረርባቸውና ቴሌን የምንተቸችባቸው የነበሩ አንዳንድ የአገልግሎት አሰጣጦች አሁን ተሻሽለዋል::

ቆይቶም ቢሆን ቴሌ እየነቃ ከዓመታት

ማስታ

ወቂያ

Page 14: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 14 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

‹‹ከዚህ በፊት ከነበሩ ሦስት የመኖርያ ቤቶች ግንባታ

ፕሮግራሞች በተጨማሪ ሌሎች አማራጮችን ጨምረናል››

ከንቲባ ኩማ ደመቅሳ የአዲስ አበባ ከተማን ቁልፍ ከተረከቡ ጊዜ ጀምሮ (አምስት ዓመት ሊሆነው ነው) የመሬትና መሬት ነክ ጉዳዮች በማያባራ የለውጥ ሒደት ውስጥ ይገኛሉ:: ለውጡን ሲያቀጣጥሉ የነበሩት የቀድሞው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መኩርያ ኃይሌ ናቸው:: አቶ መኩርያ ከአዲስ አበባ አስተዳደር ወጥተው የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር ሆነው ከተሾሙ በኋላ ይህንን የለውጥ እንቅስቃሴ በአገር አቀፍ ደረጃ አቀጣጥለውታል:: በኢትዮጵያ የመሬትና የመኖርያ ቤት ጉዳዮች ዘወትር አነጋጋሪ እንደመሆናቸው መጠን የለውጥ ሥራዎቹን ኅብረተሰቡ በአንክሮ እየተከታተላቸው ነው:: እየተካሄዱ ያሉትን የመሬትና የመኖርያ ቤት የለውጥ ሒደቶችን በዋነኛነት ቀያሽ የሆኑትን የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትሩን አቶ መኩርያ ኃይሌን ውድነህ ዘነበ አነጋግሯቸዋል::

አቶ መኩርያ ኃይሌ፣ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር ሪፖርተር፡- አዲስ አበባን ጨምሮ በአገር አቀፍ

ደረጃ ምን ያህል የመኖርያ ቤት ፍላጎት አለ? በሌላ አነጋገር ምን ያህል ቤት ፈላጊዎች አሉ?

አቶ መኩርያ፡- የቤት እጥረቱ ሁላችንም እንደምናውቀው ካለፈው ሥርዓት የዞረ ዕዳ ነው:: ያለፈው ሥርዓት መኖርያ ቤቶች በግል ባለሀብትና በራስ ተነሳሽነት እንዲገነቡ የማያበረታታ ስለነበር፣ በቤት አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ችግር ነበር:: በዚህም ምክንያት ብዙ የተከማቸ ፍላጎት ተከምሮ ነው የቆየው:: በየክልሎችና በአዲስ አበባም ከፍተኛ የቤት ፍላጎት እንዳለ መንግሥት ይረዳል:: አሁን ባለንበት ሁኔታ በተለይ ሁለት ነገሮች ተደራርበው እየመጡ ነው ያሉት:: አንደኛው የከተማውና የገጠሩ ኅብረተሰብ በተወሰነ ደረጃ ገቢ እያገኘ የመጣበት ሁኔታ አለ:: ያ ገቢ ከኢኮኖሚውም ጋር የተያያዘ ነው:: በዚህም ምክንያት በተወሰነ ደረጃ እየቆጠበ ቤት ሊገዛ የሚያስችለው አቅም እንዳለው በተለያየ መንገድ ማረጋገጥ ችለናል:: የአቅም ችግር ያለበትም እንዳለ ሁሉ መግዛት የሚችል የኅብረተሰብ ክፍል አለ:: በገጠርም አርሶ አደሩ ቁጠባ እያደረገ ልጆቹን ወደ ከተማ የማስገባት ወይም ወደ አቅራቢያ ትናንሽ ከተሞች የመላክ ፍላጎት እንዳለ የሚያሳይ ሁኔታ አለ:: ሁለተኛው ደግሞ ቅድም እንዳነሳሁት:: ውዝፍ የቤት ፍላጎት አለ:: እነዚህ ተደማምረው ባለንበት ሁኔታ ከአንድ ሚሊዮን የማያንስ የቤት ፍላጎት እንዳለ መንግሥት ይገነዘባል:: የመኖርያ ቤት ችግርን ለመፍታት ፈርጀ ብዙ የሆነ ዕርምጃ ለመውሰድ እየተረባረብን ነው::

ሪፖርተር፡- ከአንድ ሚሊዮን ውስጥ በአዲስ አበባ ያለው ፍላጎት ምን ያህል ነው?

አቶ መኩርያ፡- ከ500 ሺሕ የማያንሰው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ መኖርያ ቤት ፈላጊ ነው ማለት ይቻላል::

ሪፖርተር፡- ውዝፍ ሲባል ለምሳሌ ባለፈው ሥርዓት ብንመለከት የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ ቤት ይገነባ ነበር:: የቁጠባ ቤቶች ነበሩ:: ዜጎች እንደሁኔታው 500 ካሬ ሜትርና 250 ካሬ ሜትር ቦታ እየተሰጣቸው የራሳቸውን ቤት ይሠሩ ነበር:: በአንፃሩ ኢሕአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ ጀምሮ ለ16 ዓመታት ቤት አልገነባም:: ስለዚህ ያለፈው ሥርዓት የፈጠረው ውዝፍ ነው ማለት ይቻላል?

አቶ መኩርያ፡- በደርግ ጊዜ የኪራይ ቤቶች ቤት የሚባሉት አብዛኛዎቹ የሚገኙት አዲስ አበባ ውስጥ ነው:: ቁጥራቸው እስከ 16 ሺሕ ይደርሳል:: እነዚህ ቤቶች አዲስ ግንባታዎች አይደሉም:: አብዛኛዎቹ በአዋጅ ቁጥር 47/67 መሠረት ከግል ባለንብረቶች የተወረሱ ናቸው:: ሁለተኛ የኪራይ ቤቶች የሚባሉት የቀበሌ ቤቶች ናቸው:: ቁጥራቸው 170 ሺሕ ይደርሳል:: እነዚህ ቤቶች ስታያቸው ዛሬ ላይ አነስተኛ ገቢ ያለው የኅብረተሰብ ክፍል በእነዚሁ ቤቶች የመኖርያ አገልግሎት እያገኘ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል:: ነገር ግን ቤቶቹ ለኑሮ የማይመቹ ናቸው:: የመፀዳጃ ቤት አቅርቦት ችግር ያሉባቸው ናቸው:: የፍሳሽ ማስወገጃ የላቸውም:: የእሳት አደጋና ድንገተኛ አደጋ በሚደርስበት ጊዜ አገልግሎት ለማግኘት በጣም ትልቅ ችግር ያለባቸው ናቸው:: የተጎሳቆሉና የተጎዱ ናቸው:: ስለዚህ ደርግ በዜጎች የተገነቡ ቤቶችን መውረስ ካልሆነ በስተቀር በተጨባጭ በቤት አቅርቦት ያደረገው አስተዋጽኦ በጣት የሚቆጠር ነው:: በትልቅ ደረጃ፣ በፕሮግራም ደረጃ ደርግ ቤት የሠራበት ሁኔታ የለም:: ያሉት መረጃዎች ይህንኑ ነው የሚያረጋግጡት:: ኢሕአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ በኋላ በቤቶች የኅብረት ሥራ ማኅበራት አማካይነት ግንባታው ቀጥሏል:: እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የቆመበት ሁኔታ አልነበረም:: ስለዚህ በዚህ ረገድ ኢሕአዴግ ትኩረት አልሰጠም ሊባል አይችልም:: መሬት በሊዝ በስፋት

እየቀረበ የነበረበት ሁኔታ ነበር:: ስለዚህ በምንም መስፈርት ከተወዳደረ ኢሕአዴግ ውዝፍ የቤት አቅርቦት ክምችትን ከተገነዘበ በኋላ አሁን ባሉት የቤቶች የኅብረት ሥራ ማኅበራት፣ በሪል ስቴት አልሚዎች፣ በግል ቤት አልሚዎች ብቻ የቤት ፍላጎቱን መቅረፍ እንደማይችል ተገንዝቦ የተለየ ጣልቃ ገብነት ያስፈልገዋል በሚል፣ ለተወሰነ ጊዜ የሚቆይ የቤት አቅርቦት ፕሮግራም ነድፎ እየተገበረ ነው ያለው:: ስለዚህ ያንን ውዝፍ ለማካካስ በየትኛውም መንገድ ብታወዳድረው በፊት የቤት አቅርቦት የነበረ አሁን ግን የቀነሰ ብሎ መከራከር የሚቻል አይደለም::

ሪፖርተር፡- መንግሥት ውዝፍ ሥራውን ከጨረሰ ከቤት ግንባታ ሊወጣ ይችላል እያሉኝ ነው:: ከወጣስ መቼ ነው የሚወጣው? የተቀመጠ የጊዜ ገደብ አለ?

አቶ መኩርያ፡- የቤት አቅርቦት ችግር ከፍተኛ ነው:: አቅርቦቱ በወሳኝ ደረጃ መፈታት ያለበት ውዝፍ ዕዳ ነው:: አዲስ አበባ ውስጥ 170 ሺሕ አካባቢ የቀበሌ ቤቶች አሉ:: እነዚህ ቤቶች ከሞላ ጎደል የሚፈርሱ ናቸው:: ሁሉም የሚነሱ ናቸው:: እነዚህ ቤቶች ሲነሱ ነዋሪው በትክክለኛው መንገድ መስተናገድ አለበት:: ምክንያቱም ያን አካባቢ ማልማት ማለት አካባቢን ማልማት ማለት ብቻ አይደለም:: እዚያ አካባቢ ማልማት ማለት ሕንፃ መገንባት ማለት ብቻ አይደለም:: ዋና ቁም ነገሩ የዕቅዱ የመጀመሪያና የመጨረሻ የሚሆነው እዚያ ቤት ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ዜጎች ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግና ለኑሮ የተመቸ ሁኔታ ማግኘታቸውን ማረጋገጥ ነው:: ስለዚህ ከዚህ ቀደም የወሰድናቸውን የመልሶ ማልማት ሥራዎች ስታያቸው ከዚህ አንፃር ነው መመዘን ያለባቸው:: በመዋቅራችንም ላይ ችግር ይታያል:: አካባቢውን ማልማት ማለት ሕንፃ መገንባት፣ መሠረተ ልማት መዘርጋት ብቻ መስሎ የሚታየው ሰው ቁጥር ብዙ ነው:: የመንግሥት

ዋና ዓላማ ግን በአንድ አካባቢ በጣም የሚያምሩ ሕንፃዎችን መገንባትና መንገድ መሥራት አይደለም:: ዋና ዓላማው እዚያ አካባቢ ለነበሩ ዜጎች ለኑሮ የተመቸ ሁኔታ መፍጠር ነው:: ዓላማው የኅብረተሰቡን የውኃ፣ የመብራትና የስልክ ችግሮች መፍታት ነው:: ልጆቻቸው የሚጫወቱበት አካባቢ መፍጠርና የኅብረተሰቡን ችግር በዘላቂነት መፍታት ነው:: ስለዚህ ይህ በመዋቅራችን ያለ ችግር በተዋረድ የሚፈታበትን ሁኔታ መፍጠር እንፈልጋለን:: በኅብረተሰቡም ዘንድ ይኸው ሐሳብ ሊታወቅ ይገባል:: ይህ ችግር በግሉ ዘርፍ ሊፈታ አይችልም:: በመንግሥትና በሕዝብ የጋራ ኃላፊነት የሚፈታ ነው:: ስለዚህ ይህ ሥራ አለ:: የመልሶ ማልማት ሥራ አለ:: የቤት አቅርቦት ክፍተት አለ:: እነዚህን ሥራዎች ወደ አንድ ደረጃ ማድረስ ያስፈልጋል:: ስለዚህ እነዚህን ችግሮች ለመፍታት በምናደርገው የአፈጻጸም ብቃት ነው መንግሥት ከግንባታ የሚወጣበት የሚወሰነው:: እነዚህ ችግሮች በግሉ ዘርፍ የሚፈቱበት መንገድ የለም:: እነዚህ ችግሮች ሲፈቱ መንግሥት ከግንባታ ወጥቶ ወደ ቁጥጥር ነው የሚሸጋገረው::

ሪፖርተር፡- ከተያዙት የቤት ልማት ፕሮግራሞች መካከል የ40/60 ቤቶች ፕሮግራም አንዱ ነው:: አሁን በምን ደረጃ ላይ ነው የሚገኘው? በተለይ አዲስ አበባ ላይ?

አቶ መኩርያ፡- የ40/60 ቤቶች ፕሮግራም እናንተ በመገናኛ ብዙኀን በስፋት አጉልታችሁ ስለገለጻችሁት ነው እንጂ በዚያ ደረጃ መገለጽ የነበረበት አይደለም:: ይህ ለሙከራ የምንጀምረው ፕሮግራም ነው:: ከዚያ ውጭ ሌሎች ፕሮግራሞች አሉ:: አንደኛ ሌሎች አነስተኛ ገቢ ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚጠቀሙበት፣ በቤት ግንባታም ቢሆን 35 ሺሕ ቤቶች በግንባታ ላይ ያሉበት ፕሮግራም አለ:: በአብዛኛው

ፎቶ በ

ሪፖርተ

ር/ታምራት ጌ

ታቸው

Page 15: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 15 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታ

ወቂያ

ማስታ

ወቂያ የምዝገባ ጥሪ

ለዳያስፖራ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማኅበር አባላትና ተባባሪ አባላት በተጠናከረ መንገድ

መመዝገብና መሰባሰብ ጀምረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማኅበር በሕጋዊ

መንገድ የተመዘገበ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ዳያስፖራ ኢትዮጵያውያንና

ትውልደ ኢትዮጵያውያንን የሚወክል ብቸኛ ማኅበር ነው፡፡ የኢትዮጵያ

ዳያስፖራ ማኅበር የአባላቱን ፍላጎት ለሟሟላት የተቋቋመ ማኅበር ሆኖ

ኢንቨስተመንትን፣ የዕውቀትንና ክህሎት ሽግግርን፣ ንግድ፣ ቱሪዝም፣

እንዲሁም የአገር ገጽታ ግንባታና የመሳሰሉትን ለማፋጠን የሚረዱ

አገልግሎቶችን ይሰጣል፡፡ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማኅበር ሥራ የሁሉም

የኢትዮጵያውያን ዳያስፖራ ጉዳይ እንደመሆኑ መጠን ኢ.ዳ.ማ ሁሉም

ኢትዮጵያዊያን ዳያስፖራዎች መጥተው እንዲመዘገቡ፣ የበኩላቸውን

እንዲያበረክቱና በማህበሩ ግልጋሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪዎን ያቀርባል፡

፡ እንዲሁም የተመዘገባችሁ አባላት የመታወቂያ ካርድ የተዘጋጀላቸው

በመሆኑ በጽሕፈት ቤቱ መጥታችሁ እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡

አድራሻችን፡ ማራቶን ሕንጻ፣ 3ኛ ፎቅ፣ ቢሮ ቁ. 301

ፖ.ሳ.ቁ. 99/1110/ ስልክ ቁ፡ 251-116 62 75 17

ፋክስ፡ 251 116 18 99 25

ወደ ክፍል-1 ገጽ 18 ዞሯል

የመንግሥት ሠራተኞች ከዚህ ይጠቀማሉ:: ሰፋ ያለ አንድ ክፍል ቤት ነው የሚሆነው:: ባለቤቱ ባለሁለት ክፍል ሊያደርገው ይችላል:: መፀዳጃና ማብሰያ ክፍል ያለው ነው:: መንግሥት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ ከ50 ሺሕ ብር በላይ ድጎማ የተደረገለት ነው:: 28 ሺሕ ብር አካባቢ ብቻ ከፍለው ዜጎች የቤት ባለቤት የሚሆኑበት ሰፊ ፕሮግራም ነው:: አነስተኛ ገቢ ላለው የኅብረተሰብ ክፍል ይጠቅማል ተብሎ የሚታሰብ ፕሮግራም ነው:: ሁለተኛው የኮንዶሚኒየም ቤቶች 20/80 ነው የሚባሉት:: አነስተኛ ገቢ ላለው ኅብረተሰብ ክፍል የምንገነባውን ባለ አንድ ክፍል ቤት 10/90 ነው የምንለው:: ግንባታውን አጠናክረን ነው የምንቀጥለው:: ቀደም ሲል የኮንዶሚኒየም ቤቶች ፕሮግራም በተጨባጭ የሚታወቅ ስላልነበር ሁሉም ዜጋ ተመዝግቧል ማለት አይቻልም:: ሁለት ሦስት ጊዜ የተመዘገቡ አሉ:: በተለያየ ቤተሰብና ትዳር የተመዘገበ አለ:: ይህ በኅብረተሰቡ የሚነሳ ቅሬታ ነው:: ይህ ቅሬታ መወገድ አለበት:: መሬት ለዜጎች የሚደርስበት፣ ቤቶች ለዜጎች የሚደርሱበት አሠራር አለን፤ እኛ የሀብት ድልድል ነው የምንለው:: ያልተገባ ጥቅም የሚያገኘውን ኪራይ ሰብሳቢ ነው የምንለው:: ስለዚህ ኪራይ ሰብሳቢነቱ እንዲቆም ያልተገባ ጥቅም የሚያገኘው በሩ እንዲዘጋበት እናደርጋለን:: ስለዚህ ኮንዶሚኒየም ቤቶቹ ከዚህ አንፃር ትልቅ አስተዋጽኦ የሚኖራቸው ናቸው:: በዚህ ረገድ ያልተገባ ምዝገባ ከተደረገ ቴክኖሎጂው በሚፈቅደው መንገድ እናጠፋለን:: የነበሩ ቅሬታዎችን በሙሉ በሚፈታ መንገድ የኮንዶሚኒየም ምዝገባ በድጋሚ እንዲካሄድ እናደርጋለን:: የ40/60 ቤቶች ፕሮግራም የንግድ ቤቶቹ አራት ሺሕ ይደርሳሉ:: መኖርያ ቤቶቹ 16 ሺሕ ይደርሳሉ:: አጠቃላይ 20 ሺሕ ቤቶች ይገነባሉ:: በዚህ ረገድ የተቀየረ ነገር የለም:: በተጨባጭ ተዟዙሮ መመልከት ይቻላል:: ለገሀር አካባቢ ሦስት አንደር ግራውንዶች እየተቆፈሩ ነው:: ከመሬት በታች ሦስት ወለል ከመሬት

በላይ 12 ወለል በድምሩ 15 ወለል (ፎቅ) ግንባታ ተጀምሯል:: ሁሉም በመገንባት ላይ ነው:: ከዚህ ውጭ የመኖርያ ቤት ፕሮግራም መጀመራችን አይቀርም::

ሪፖርተር፡- የሚጀመሩትን አዳዲስ የቤቶች ፕሮግራሞች ቢገልጹልን?

አቶ መኩርያ፡- ዜጎች መቶ በመቶ ከፍለው የቤት ባለቤት የሚሆኑበትን የቤቶች ፕሮግራም እንጀምራለን:: መሥርያ ቤቶቻቸው ሊገነቡላቸው የሚችሉ ዜጎች በዚህ ሊስተናገዱ ይችላሉ:: የ40/60 ቤቶች ፕሮግራም በስፋት ከተገለጸ በኋላ የወሰድነው ትምህርት አለ:: ዜጎች ለቤት ያላቸውን ፍላጎት ተረድተናል:: ዜጎች መኖርያ ቤት እንዲኖራቸው የነበራቸው ጉጉት ያስተማረን ነገር አለ:: ስለዚህ ከዚህ በፊት ከነበሩ ሦስት የመኖርያ ቤቶች ግንባታ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ሌሎች አማራጮችን ጨምረናል:: ስለዚህ ይህ በቅርብ ጊዜ በመንግሥት ተወስኖ በቅርቡ የተሟላ መግለጫ የምንሰጥበት ይሆናል:: እነዚህን መግለጫዎች አሁን መስጠት ያልፈለግንበት ምክንያት ዜጎች የፖሊሲ አቅጣጫ ማስቀመጥ፣ ሕግ ማውጣት፣ ደንብ ማውጣትና መዋቅር መፍጠር ብዙም ትርጉም አይሰጣቸውም:: ትርጉም የሚሰጣቸው መግለጫ ከተሰጠ በኋላ ሥራ ሲጀመር ነው:: ምዝገባ እንዲጀመር ይፈልጋሉ:: በተጨባጭ ተግባር ውስጥ እንዲገባ ይፈልጋሉ:: እኛም ካለፉ ልምዶች እየተማርን የምንሄድ ስለሆነ ፖሊሲውን የማጠናቀቅ፣ ዝርዝር ማንዋሎችን የመጨረስ፣ ማዕቀፎችን የማዘጋጀት፣ አሠራሩን የማስተካከል ሥራዎች በተሟላ መንገድ እየተጠናቀቁ በመሆናቸው በቅርቡ መግለጫ እንሰጣለን ብለን እናስባለን::

ሪፖርተር፡- ቀደም ባሉት ዓመታት ለኮንዶሚኒየም ቤቶች 453 ሺሕ ሰዎች ተመዝግበዋል:: ከእነዚህ ውስጥ ወደ 80 ሺሕ ሰዎች በተለያዩ መንገዶች የቤት ባለቤት ሆነዋል:: ድጋሚ ምዝገባ ማካሄድ ለምን አስፈለገ? እናጠራለን ማለትስ ምን ማለት ነው?

አቶ መኩርያ፡- ቀደም ሲል የተመዘገቡ ሰዎች መብታቸው ይጠበቅላቸዋል፤ አሁንም ቅድሚያ ያገኛሉ:: ሲያገኙ በፊት እንደነበረው አይሆንም:: በ‹‹ባዮ ሜትሪክስ›› ነው ምዝገባው የሚካሄደው:: ‹‹ባዮ ሜትሪክስ›› በሚሆንበት ጊዜ አንድ ሰው አንድ ጊዜ ከተመዘገበ በኋላ ሌላ ቦታ ቢመዘገብ ቴክኖሎጂው ያገኘዋል:: የመሬትና መሬት ነክ ቋሚ ንብረት ምዝገባ በቅርቡ ስለሚካሄድ ለምዝገባው ጠቀሜታ ይኖረዋል:: በቤተሰቡ፣

በእናት፣ በሚስትና በልጅ የሚደረገው ምዝገባ በግልጽ መሆን አለበት:: የሚወጡ ሕጎች ይኖራሉ:: በዚህ ዓይነት ያልተገባ ጥቅም የሚያገኙ ዜጎች አንዷን ጥቅም እንኳ የሚያጡበት አሠራር እንቀይሳለን:: ስለዚህ ምዝገባው በሚጀመርበት ወቅት ይህንን በግልጽ እናስታውቃለን:: በቀድሞ ምዝገባዎች ወቅት ማስጠንቀቂያዎች አልነበሩም:: ዝም ተብሎ ተመዝገብ ነበር የተባለው:: እነዚህን ነገሮች በተሟላ መንገድ እንገልጻለን:: ያንን የማያደርግ ዜጋ ካለ በራሱ እየፈረደ ነው የሚሄደው:: ምዝገባውን ማካሄድ ያስፈለገው በተለያዩ ዓይነት አደጋዎች የተቀነሱ ዜጎች ሊኖሩ ይችላሉ:: ከአገር የወጡ ዜጎች ሊኖር ይችላሉ:: በሌላ ዕድል ቤት ያገኙ ዜጎች ሊኖሩ ይችላሉ:: በሁለት ሦስት አማራጮች የተመዘገቡ ዜጎች ሊኖሩ ይችላሉ:: ይህንን ማጣራት ስለሚያስፈልግ ነው:: ቀደም ሲል የተመዘገቡት በመጀመርያ ዕድል ተሰጥቷቸው ይመዘገባሉ:: በሚመዘገቡበት ጊዜ ጥርት ያለው መረጃ ይገኛል:: እኛም የምናወራቸው ቁጥሮች መሬት ላይ ያሉ ቁጥሮች ናቸው? ወይስ አይደሉም የሚል ግንዛቤ ይኖረናል:: ስለዚህ ምዝገባው ዳግም ይካሄዳል:: ስለዚህ ዳግም የመመዝገብ ዕደሉ ይኖራቸዋል:: ወረፋው ይጠበቅላቸዋል:: ምዝገባው ግን ዳግም ይደረጋል:: ያን ጊዜ የተመዘገቡበት ካርድና ቁጥራቸውን እያሳዩ ይመዘገባሉ::

ሪፖርተር፡- ከዚህ ቀደም በተለያዩ ስሞች ተመዝግበው ያልተገባ ጥቅም ሁለት ሦስቴ ያገኙ ዜጎች አሉ ይባላል:: በአዲሱ የምዝገባ ስልት ተለይተው ከታወቁ የሚወሰድባቸው ዕርምጃ ይኖራል?

አቶ መኩርያ፡- አጠቃላይ አካሄዳችን የመቅጣት አይደለም:: በአጠቃላይ ስታየው የሊዝ አዋጁን ስናወጣ ሕገወጥ ግንባታ ላይና ውዝፍ ይዞታ ላይ አካሄዳችን የመቅጣት አይደለም:: አካሄዳችን ከችግሩ ሽክርክሪት፣ ከችግሩ አዙሪት የመውጣት (ኤግዚት ስትራቴጂ) ነው እየነደፍን ያለነው:: የመውጫ በር እንከፍትላቸዋለን፤ ያ የተወሰነ ገደብ ይኖረዋል:: በእዚያ ጊዜ መውጣት ይኖርባቸዋል:: በዚያ ጊዜ ካልወጡ ግን ሌሎች ጠንከር ያሉ ቅጣቶች የሚጣሉበትና ተጠያቂ መሆን የሚመጣበት ሥርዓት እንነድፋለን::

ሪፖርተር፡- በየመሥርያ ቤቱ ያሉ ሠራተኞች በማኅበር ተደራጅተው ቤት መገንባት ይፈልጋሉ:: ፕሮቪደንት ፈንድ ያላቸውና ሊጠቀሙበት የሚያስቡም ይኖራሉ:: አንዳንድ ለሠራተኞቻቸው መኖርያ ቤት

Page 16: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 16 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ማስታወቂያ

Page 17: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 17 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታወቂያ

Page 18: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 18 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ለመገንባት ፍላጎት የሚያሳዩ ድርጅቶች አሉ:: እነዚህ አካላት በአዲሱ አሠራር እንዴት ይስተናገዳሉ?

አቶ መኩርያ፡- ይህ ዕድል ይፈጠራል:: ማኅበራቱ ፕሮቪደንት ፈንድ ካላቸው፣ ብድርና ቁጠባም ካላቸው፣ ሌሎችም የገቢ ምንጮች ካሉዋቸው መቶ በመቶ ለቤቱ ግንባታ የሚያስፈልገውን ክፍያ ከፍለው የቤት ባለቤት መሆን ይችላሉ:: ከከፈሉ በኋላ ተደራጅተው በማኅበራቸው ሊሆን ይችላል፣ በኮንትራተር ሊሆን ይችላል፣ ወይም የ40/60 ቤቶችን ለመገንባት በተቋቋመው ኢንተርፕራይዝ ቤቱን ማስገንባት ይችላሉ:: ይህ ዕድል በቅርቡ ይጀመራል::

ሪፖርተር፡- ቤት ለማግኘት በማኅበር የሚደራጁ ሰዎች መሬቱን ተረክበው በራሳቸው መንገድ ግንባታ ማካሄድ የሚችሉበት አሠራር አይፈጠርም? ገንዘቡንም ከባንክ አግኝተው ማካሄድ የሚፈልጉም ይኖራሉ እኮ?

አቶ መኩርያ፡- በማኅበር ከተደራጁና መቶ በመቶ የቤት መሥርያውን ገንዘብ ገቢ የሚያደርጉ ከሆነ ራሳቸው የሚገነቡበትን አሠራር ክፍት ለማድረግ ይቻላል:: መንግሥት የሚያየው ይመስለኛል::

ሪፖርተር፡- ይህን ፕሮግራም ለመጀመር ምን ያህል ጊዜ ይወስዳል?

አቶ መኩርያ፡- በቅርብ ጊዜ ይጀመራል::ሪፖርተር፡- ከመኖርያ ቤት ወጣ ላድርግዎትና አዲስ

አበባን እንመልከት:: የከተማው ማስተር ፕላን 16 ቦታዎችን ለፓርክ አገልግሎት አንዲውሉ ያስቀምጣል:: ነገር ግን ማስተር ፕላኑ ይህንን ቢልም አሥረኛ ዓመቱ ተጠናቆ ከሥራ ውጭ እስከሆነበት ጊዜ ድረስ የፓርኮች ግንባታ እውን አልሆነም:: አዛውንቶች አረፍ የሚሉባቸውና አረንጓዴ ቦታዎች ከተማ ውስጥ እየተናፈቁ ነው:: መንግሥት እነዚህን ጉዳዮች ያስተውላል?

አቶ መኩርያ፡- እንዳነሳኸው የአረንጓዴ ልማትን በተመለከተ በመዋቅራችንም፣ በኅብረተሰቡም በኩል እንደ ሀብት ተወስዶ ለከተማው ኦክስጂን፣ ለዜጎች ደግሞ መናፈሻ፣ በሥራ የተወጠረ አዕምሮ ፈታ የሚልባቸው መሆኑን የግንዛቤ ክፍተት እንዳለ ይታያል:: እንዳስቀመጥከው አተገባበር ላይ ችግር እንዳለ መንግሥት ይገነዘባል:: ያንን ለመፍታት ተጨማሪ ዕርምጃዎች እየተወሰዱ ነው ያሉት:: አንደኛ የመዋቅራዊ ፕላኑ በአሁኑ ወቅት እየተሠራ ነው:: በ2005 ዓ.ም. ለአሥር ዓመት የተተገበረው መዋቅራዊ ፕላን (ማስተር ፕላን) ይጠናቀቃል:: ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ እየተሠራ ያለው አዲስ መዋቅራዊ ፕላን ተግባራዊ ይደረጋል:: በዚህ ረገድ ለአረንጓዴ አካባቢዎች ትኩረት ይሰጣቸዋል:: የተወሰኑ አካባቢዎች በአካባቢ ልማት ፕላን (LDP) መሠረት የተገነቡ አሉ:: ለምሳሌ ካዛንቺስ ኢሲኤ ጀርባ የተገነባው ዓይነት እዚያ አካባቢ የተሠራው [ለአረንጓዴ ቦታዎች ብዙም ትኩረት አልሰጠም]:: በሌላ በኩል የልደታ ቤቶች ልማትን ብትመለከት ፓርክ አለው:: መናፈሻ አለው:: ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ:: አራት ኪሎም በተመሳሳይ መንገድ ይገነባል:: በአዲስ አበባ የረፈደ አይደለም:: ምክንያቱም 80 በመቶ ያህሉ የከተማው ክፍል ፈርሶ የሚሠራ ነው:: ከዚህ በፓርክም፣ በመናፈሻም፣ በአረንጓዴ ቦታም ረፍዷል የምትለው አይደለም:: አዲስ አበባ እንደገና ስትገነባ ደረጃውን የጠበቀ የተሟላ አረንጓዴ ስፍራ የሚኖራት ነው የምትሆነው::

ሪፖርተር፡- ለፓርክና ለአረንጓዴ ልማት ተብለው በተለዩ ቦታዎች ላይ ነዋሪዎች ሰፍረውባቸዋል:: መንግሥት በቅርቡ ያዘጋጀው ደንብ ደግሞ ሕገወጦችን ሕጋዊ ለማድረግ እንደሚሠራ ያትታል:: ሁለቱ እንዴት ይታረቃሉ?

አቶ መኩርያ፡- ሕገወጥ ግንባታዎችና ውዝፍ ይዞታዎችን የምናስተናግደው ስንል ከፓርክና ከአረንጓዴ ቦታዎች ውጭ ያሉትን ነው:: ግንባታው የተካሄደው አረንጓዴ ቦታ ላይ ከሆነ ሕጋዊ አይደረግም:: ስለዚህ እነዚያ ዜጎች የሚስተናገዱበት የራሱ አሠራር ይኖረዋል:: ሕጋዊ የሚደረጉት በመዋቅራዊ ፕላኑ ተቀባይነት የሚያገኙት ብቻ ናቸው:: በአዲስ አበባም ሆነ በክልሎች ይኸው ነው ተፈጻሚ የሚሆነው:: ከዚያ ውጭ በመዋቅራዊ ፕላኑ በአረንጓዴ ቦታዎች ላይ ለሕገወጦች ዕውቅና የሰጠ አካል የሚኖር ከሆነ በእስራትም በገንዘብም የሚጠየቅበት አሠራር በአዋጁ በግልጽ ተቀምጧል:: ስለዚህ እንደዚህ ዓይነት አሠራር አይኖርም::

ሪፖርተር፡- ሕገወጥ የሚባሉትን ሕጋዊ ለማድረግ ሲታቀድ ዓላማው ምንድነው? ሕገወጥ የሚባሉትስ ምን ያህል ይሆናሉ?

አቶ መኩርያ፡- የጊዜ ገደቡ ተቀምጧል:: ይህ አዋጅ የወጣው በ2003 ዓ.ም. ነው:: ሕገወጦችን ሕጋዊ ለማድረግ የአምስት ዓመት ጊዜ ገደብ ሰጥቷል:: በአዋጅ 47/67 መሠረት የይዞታ ማረጋገጫ ሳይሰጣቸው የቆዩ ይዞታዎች አሉ:: እነሱን የመጨረስ፣ በየክልሉ ሕገወጦች ስላሉ ማፍረስ ወይም ዕውቅና መስጠት ያስፈልጋል:: ከዚያ በኋላ ሕገወጥ የሚባል ግንባታ አይኖርም:: ወይ ይፈርሳል ወይ ዕውቅና ይሰጣል:: ከዚያ በኋላ ሕገወጥ ግንባታ ከተካሄደ ሁለቱም አካላት እንዲጠየቁ ነው አዋጅ ያስቀመጠው:: አንደኛ አንድ ከተማ የከተማ ክልል ወሰን ይኖረዋል:: ያንን አካባቢ የሚያስተዳድረው አካል ይጠየቃል:: እሱ በሚያስተዳድርበት ወቅት ሕገወጥ ግንባታ ተገንብቶ ቢገኝ ተጠያቂ የሚሆንበት ሥርዓት ነው የተቀመጠው:: ሕገወጥ ይዞታ የያዘውም ሰው ይጠየቃል:: ያንን ለመቆጣጠር የደንብ ማስጠበቅ ሥራ ይሠራል:: በክህሎቱም፣ በአቅሙም፣ ሕግ በማስፈጸም ረገድ ፖሊሳዊ ቁመና ያለው ደንብ የሚያስከብር ክፍል እንዲደራጅ እናደርጋለን:: በአዲስ አበባም በዚህ እሳቤ እየተሠራ ነው ያለው:: በሌሎችም ክልሎችም ይኸው ይሠራል:: ስለዚህ ሁለቱም አካላት የሚጠየቁበት ሥርዓት ይኖራል:: ከዚህ በተጨማሪም ከኅብረተሰቡ ጋር ውይይት የሚደረግበት ነው::

ሪፖርተር፡- ሕግ ማስከበር ፖሊሳዊ ቁመና ይኖረዋል ሲባል ምን ማለት ነው? ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ የነበረው ደንብ ማስከበር መሥርያ ቤት ምን ይሆናል?

አቶ መኩርያ፡- አዲስ አበባ ላይ ያለው ደንብ ማስከበር እንደገና ተጠናክሮ ይቀጥላል:: እንዲሁም ኮሚዩኒቲ ፖሊሲንግ ከኅብረተሰቡ ጋር ተቀናጅቶ ይሠራል::

ሪፖርተር፡- ሕገወጦችን ሕጋዊ የማድረግ ሒደት ምናልባት ከዚህ ቀደም መሬት ላልወረረ ሰው የሚያስተላልፈው መልዕክት ምንድነው?

አቶ መኩርያ፡- ምንም የሚያስተላልፈው ነገር መኖር የለበትም:: ምክንያቱም በሕገወጥ መንገድ መሬት የያዙ ሰዎች በመንግሥት በኩል ብዙ ተጠቅመዋል የሚል እምነት የለም:: አንደኛ በሕገወጥ መንገድ የያዙትን መሬት የፈለገው ቢሆን በነፃ አያገኙም:: ከፍለው የሚያገኙት ነው የሚሆነው:: ሁለተኛው በቀጥታ ወደሊዝ ሥርዓት ነው የሚገቡት:: በሊዝ ከፍለው ነው የሚያገኙት:: ሦስተኛ የኪራይ ድልድል ባልናቸው ዕድሎች ተጠቃሚ አይሆኑም:: በኮንዶሚኒየም፣ በ40/60፣ በ20/80፣ በ10/90 ተጠቃሚ አይሆኑም:: ስለዚህ ከኅብረተሰቡ ሞራል አንፃር፣ ከማኅበረሰብ እሴት አንፃር፣ ከዜግነትም አንፃር ትክክል አይደለም:: በሞራልም በገንዘብም ተቀጥተው ነው ይህንን መሬት የሚያገኙት:: ያንን ባያገኙ ኖሮ በ10/90 ወይም በ20/80 ወይም በ40/60 አቅም ካላቸው ደግሞ ሙሉውን ከፍለው ሊያገኙ ይችሉ ነበር:: ሕገወጥነት የሞራል ቅጣት አለው:: ሕገወጥነት የሰብዕና መጓደል ነው:: ስለዚህ ሌላ ሰው ቀረብኝ የሚለው አይደለም:: ኃፍረት ነው:: አጥፍቶ ኅብረተሰቡ ይቅርታ እያደረገለት ነው:: መንግሥት ይቅርታ እያደረገለት ነው::

ሪፖርተር፡- የመሬትና መሬት ነክ ቋሚ ንብረት ምዝገባ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል:: የእዚህን አዋጅ አስፈላጊነት ብዙዎች ይጠይቃሉ:: ምክንያታቸውም ቀደም ሲል ካርታ አለን ሌላ ምዝገባ ለምን አስፈለገ የሚል ነው?

አቶ መኩርያ፡- አዋጁ በረቂቅ ደረጃ ነው ያለው:: በተለይ በተለይ የዳበረ የነፃ ገበያ ለመገንባት ስትረባረብ የጀርባ አጥንት የምትለው የመሬትና መሬት ነክ ቋሚ ንብረት ምዝገባ ነው:: የመሬትና መሬት ነክ ምዝገባ ለሁለት አካላት በጣም ወሳኝ ነው የሚሆነው:: ገበያ ኮንትራት ነው:: ገዥ አለ፣ ሻጭ አለ:: በሁለቱ አካላት መካከል የሚደረግ ኮንትራት ነው:: ገዢና ሻጭ የሆነ ቦታ ላይ ተገናኝተው ግብይት ሲፈጽሙ

ግብይት የተፈጸመበት ክስተት መረጃው አስተማማኝ ካልሆነ ግብይቱ ጤነኛ አይሆንም:: ጤነኛ ያልሆነ ሀብት ከአንዱ ወደ ሌላ ሲሄድ ኢኮኖሚው እየተጎዳ ነው የሚሄደው:: ስለዚህ ከዚህ አንፃር የመጀመሪያው ጥቅም በእውነተኛ መረጃ ላይ የተመሠረተ ግብይት እንዲፈጸም ማድረግ ነው:: ይኼ ለኢኮኖሚ ትልቅ ነገር ማለት ነው:: በተለይ ገዥው አስተማማኝ ንብረት ይገዛል ማለት ነው:: የሚጭበረበረው ነገር የለም:: ባንኮችን ውሰዱ፣ ባንኮች አሁን እያበቡ ያሉበት ምዕራፍ ላይ ነው ያለነው:: በዚህ ሒደት በሌሎች አገሮች እንደምንመለከተው ብዙ ጊዜ አደጋ የሚጀምረው ከዋስትና ጋር በተገናኘ ነው:: ስለዚህ ባንኮች ኮላተራል በሚይዙበት ጊዜ ዋጋ ያለው አስተማማኝ መረጃ ይዘው ብድር ሲሰጡ ለኢኮኖሚ ማደግ ትልቅ አቅም ይፈጥራል:: ለኢንሹራንስ ተቋማትና ለባንኮች በግብይት ወቅት አስተማማኝ መረጃ ነው የሚሆነው:: በመጀመርያ ትልቅ አቅም የሚሰጠው ለፖለቲካል ኢኮኖሚያችን ነው:: ዕድገቱ ቀጣይ እንዲሆን ያደርጋል:: ሁለተኛው ጉዳይ ደግሞ መሬት የሕዝብና የመንግሥት ነው:: መሬት የሕዝብና የመንግሥት የሆነበት መሠረታዊ ምክንያት የኢኮኖሚ መሠረተ ልማቶች፣ የማኅበራዊ መሠረተ ልማቶችና የመኖርያ ቤቶች አቅርቦት ዜጎችን በኪራይ ለመደልደልና እኩል ተጠቃሚ ማድረግ ያስችላል ነው:: መሬት ባለቤት ካለው ባለቤቱ ያለውን መሬት ቆጥሮ ማወቅ፣ ቆጥሮ መያዝና መመዝገብ መቻል አለበት:: ስለዚህ የመንግሥትና የሕዝብ የሆነውን መሬት ቆጥረህ የምታስረክብበት ነው:: በሕገ መንግሥቱ የተቀመጠውን ድንጋጌ ለማስፈጸም የተዘጋጀ አዋጅ ነው::

ሪፖርተር፡- የመሬትና መሬት ነክ ቋሚ ንብረት ምዝገባ የሚካሄደው እንዴት ነው? ምዝገባ የሚደረገው ለመሬቱ ነው ወይስ መሬቱ ላይ ላለው ግንባታ?

አቶ መኩርያ፡- የጀመርነው ሥራ ሰፊ ነው:: በእኛ ትውልድ የሚጠናቀቅ አይደለም:: የምንችለውን ነው የምንሠራው:: ሌላው ትውልድ እያስቀጠለ ይሠራዋል:: የእኛ ተልዕኮ መሬቱን መመዝገብ ነው:: ከመሬቱ ምዝገባ በኋላ ሌሎች የሚመጡ ነገሮች ይኖራሉ:: ቀጥሎ የሚመጣው አዲስ አበባ ውስጥ እንደምታየው ከ800 ሺሕ በላይ ቤቶች አሉ:: ከእነዚህ ቤቶች የተወሰኑት የግንባታ ፈቃድ ይኖራቸዋል:: ሁሉም ግን የመጠቀሚያ ፈቃድ የላቸውም:: ይህ ሁሉ ሕንፃ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆኖ የመጠቀሚያ ምስክር ወረቀት ያለው ሕንፃ አንድም የለም:: በሌላ አገር እንደዚህ ዓይነት ነገር የለም:: ኢትዮጵያ ምናልባት ብቸኛዋ አገር ናት:: ስለዚህ ይህ ውዝፍ ከሚባሉት ውስጥ ይጠቀሳል:: በቀጣይ መሥራት ካለበት በመጀመርያ መሬቱን ቀጥሎ በመሬቱ ላይ ያለው ሕንፃ የመጠቀሚያ ፈቃድ እንዲያገኝ መሥራት ነው:: ይህ አሁንም ውዝፍ ሥራ ነው:: አሁን የማስተካከል ሥራ ነው የምንሠራው፤ ሰውን የመቅጣት አይደለም:: ሌላ [ያለፈው] ትውልድ መሥራት የነበረበት ሥራ ነበር:: ኢሕአዴግ ተልዕኮውን ወስዶ ሥራ ውስጥ ገብተናል:: የመጠቀሚያ ፈቃድ መስጠት ስንጀምር ሕንፃው የጎደለው ነገር ካለ እንዲያሟላ በማድረግ ፈቃድ መስጠት ነው:: በቀጣይ የሚመጡት ያንን ሥርዓት ጠብቀው እንዲሄዱ ማድረግ ነው:: ሌላኛው ትልቅ ሥራ አንተ እንዳነሳኸው የመሬት ዋጋ አለ፤ በመሬቱ የመጠቀም ዋጋ ሊዝ ‹‹ቫሊዩ›› ይኖረዋል:: ‹‹ቫሊዩ›› ሁሌም አንድ ዓይነት አይሆንም:: ልደታ ላይ ካየኸው እዚያ አካባቢ በ1999 ዓ.ም. በካሬ ሜትር ዋጋው ስንት ነበር? ዛሬ ደግሞ ስንት ነው? በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ የመሬቱ ዋጋ ጨምሯል::

ሪፖርተር፡- በልደታ ቤቶች ፕሮግራም ተገንብተው ለጨረታ የቀረቡት ሱቆች የተጋነነና ያልተጠበቀ ዋጋ ነበር የቀረበላቸው (በካሬ ሜትር 56 ሺሕ ብር):: ይኼ ትክክል ነው ይላሉ?

አቶ መኩርያ፡- ለእኛ ዓላማችን ሱቆቹ ሳይሆኑ

ቤቶቹ ናቸው:: ሱቆቹ ላይ ፍላጎት የለንም:: ወደፊትም አይኖረንም:: የንግዱ ኅብረተሰብ ፍላጎቶች ናቸው:: አቅም ያለው ይገዛል:: እኛ አነስተኛ ገቢ ላለው የኅብረተሰብ ክፍል ይድረስ ልንል አንችልም::

ሪፖርተር፡- መንግሥት የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የተለያዩ ነገሮችን ያደርጋል:: በዚህ በተጋነነ ዋጋ የሚገዛ ሱቅ ውስጥ የሚሸጡት ሸቀጦች የማይቀመሱ ሊሆኑ ስለሚችሉ ነው ይህን የጠየቅኩዎት::

አቶ መኩርያ፡- እኛ ለእሱ መፍትሔ እናስቀምጣለን:: ይህንን የምንሰብርበትን መንገድ እናውቃለን:: እንዴት እንደምንሰብር እናውቃለን:: ይህንን ገንዘብ ያቀረበው በዚያ ወቅት ምንም ይሁን የሆነ ነገር አስቦ ሊሆን ይችላል:: በእርግጠኝነት የምናውቀው ሱቆቹ እንደሚያስፈልጉ ነው:: እንደዚህ ዓይነት ሱቆችን በስፋት እንሠራለን:: አቅርቦትና ፍላጎት በሚጣረስበት ጊዜ በፍላጎት ልክ፣ አቅርቦት በሚያንስበት ወቅት እኛ ለምን ዋጋ ወጣ ብለን አይደለም የምንጨነቀው:: አቅርቦትን በመጨመር ነው ችግሩን የምንቀርፈው:: ከዚህ በፊት ታስታውሳለህ አዲስ አበባ አስተዳደር እያለሁ አንስተህልኝ ነበር:: ‹‹ለአንድ ካሬ ሜትር ቦታ 22 ሺሕ ብር ቀረበ ከዚህ በላይ ሊወጣ ነው ወይ?›› ብለህ ጠይቀኸኝ ነበር:: ምንድነው የዚያን ጊዜ ያልኩህ እንሰብረዋለን ነበር:: አሁን ስንት ነው በካሬ እየቀረበ ያለው? እየቀነሰ ነው:: ለምን ቀነሰ ቢባል መሬት በብዛት ለጨረታ በማቅረባችን ነው:: ስለዚህ ሱቆች የሚያስፈልጉ ከሆነ በስፋት ገንብተን በማቅረብ ነው ዋጋን የምናረጋጋው:: የግሉ ዘርፍ ሱቅ እየገነባ እያቀረበ አይደለም ማለት ነው:: ክፍተት ስላለ እኛ በስፋት እንገባበታለን::

ሪፖርተር፡- የሊዝ አዋጁ ተግባራዊ ሆኗል:: እርስዎ በቅርቡ ከሌሎች ሕጎች በተሻለ ያለምንም ችግር እየተተገበረ ነው ብለው ነበር:: እርግጠኛ መሆን ይቻላል? ምንም ችግር አልተፈጠረም?

አቶ መኩርያ፡- ሁላችንም እንደምናውቀው በኅብረተሰቡ በኩል ሥጋት ነበር:: ፖሊሲያችንን በሚቃወሙ ተቃዋሚዎችና በራሳችንም አባላት የግንዛቤ ክፍተቶች ነበሩ:: በእኛም በኩል በቂ ማብራሪያ ከመስጠት አንፃር ክፍተቶች ነበሩ:: ለዚያ ነው በመሬትና መሬት ነክ ቋሚ ንብረት ምዝገባ ረቂቅ አዋጅ ላይ ሰፊ ውይይት እያደረግን ያለነው:: ስለዚህ የሊዝ አዋጅ ደንቡ ወጥቷል:: መመርያ ወጥቷል:: እናንተም በተከታታይ ብትሠሩበት ቆንጆ የሚሆነው:: ነባር ይዞታ ያለው ሰው ወደሊዝ ቢገባ ይጎዳል ወይስ ይጠቀማል?

ሪፖርተር፡- እርስዎ ግን እንደሚጠቀም ነው የሚገልጹት::

አቶ መኩርያ፡- አዎ! ለምንድነው የሚጠቀመው መሰለህ የሊዝ መነሻ ዋጋ እንዳይከለስ ወስነናል:: ገደቡ ሊያበቃ አንድ ዓመት ብቻ ቀርቷል:: የሊዝ መነሻ ዋጋ አዲስ አበባ ላይ ሁለት መቶ ብር ወይም ሦስት መቶ ብር ሊሆን ይችላል:: የአንድ ካሬ ሜትር መነሻ ዋጋው ሦስት መቶ ብር ነው ብትል፣ ይህንን ዋጋ ለ99 ዓመት ነው የምታካፍለው:: 300 ብር ለ99 በመቶ ዓመት ብታካፍለው ሦስት ብር አካባቢ ነው:: ይህ ገንዘብ የቅድሚያ ክፍያ የለበትም:: ስለዚህ ለአንድ ካሬ ሜትር ሦስት ብር እየከፈለ ይኖራል:: በዚህ ጊዜ ውስጥ የነበረ ባለይዞታ ሊዝ ቢገባ ይህ ገንዘብ መቼም ጭማሪ አይደረግበትም:: ለ99 ዓመት ይኖርበታል:: ክፍያውን በ40 ዓመት ከፍሎ ይጨርሳል:: 59 ዓመት በነፃ ይኖራል ማለት ነው:: የመሬት ኪራይ ግን ሦስት ብር ሆኖ ይቀጥላል ወይ? ካልክ አይደለም ይቀየራል:: በየዓመቱ ይቀየራል:: ከአምስት ዓመት በኋላ በካሬ ሜትር ስንት እንደሚሆን አይታወቅም:: ኢኮኖሚው ነው የሚወስነው:: ከመንግሥት ጋር ነው የምትዋዋለው:: መንግሥት ቢቀያየርም ገዥ ሆኖ ይቀጥላል:: እኛ አሁን በአዋጅ 47/67 መሠረት እንመራለን:: መንግሥት ያወጣው አዋጅ ነው እስካልተሻረ ትገዛበታለህ:: ያንን ዕድል ሰው ማገናዘብ አለበት::

ሪፖርተር፡- አዲስ አበባ ውስጥ ከሊዝ መሬት ጋር በተያያዘ እኩል ጥፋተኛ የሚባሉ አልሚዎች ላይ የሚወስደው ዕርምጃ የተለያየ ነው:: አንዱ አጠፋህ ተብሎ ዕርምጃ ሲወሰድበት ሌላኛው በዝምታ ይታለፋል:: ይህ ሁኔታ ወጥ የሆነ አሠራር የለም አያስብምልም?

አቶ መኩርያ፡- የሊዝ አዋጁን በዚያ መንፈስ ስታየው የግንባታ ሥራው የሚሰጥበት አሠራር አለ:: ሁሉም ሒደት የጊዜ ስሌት ተቀምጦለታል:: ሆቴል፣ ሆስፒታል፣ ዩኒቨርሲቲም ሆነ ምንም ዓይነት ግንባታ በዚህ ስሌት ይካሄዳል:: ከዚህ በኋላ ያለው መስተንግዶ ወጥ በሆነ መንገድ ይሆናል:: ከዚህ በፊት የነበሩት ደግሞ በሊዝ አዋጁ ላይ የተቀመጠው ምንድነው? በአንዳንድ የከተማ አስተዳደሮች ከባለ ሚናው ጋር የጊዜ ወሰን እያስቀመጡ መጨረስ እንዳለባቸው ተቀምጧል:: በፌዴራል በኩል የሊዝ አዋጁን በማስፈጸም በተለይ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶታል:: በአዋጁ መሠረት ቁጥጥር ለማድረግ ከፍትሕ ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት የሕግ ኦዲት ለመጀመር በዝግጅት ላይ ነው:: የሚጠየቁ ሰዎች ይኖራሉ ማለት ነው::

Page 19: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 19 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታወቂያ

የዮድ አቢሲኒያው ‘የጃንደረባው ጉዞ’ ወደ ቅድስት ሃገር ኢየሩሳሌም የልደት/ገና ጉዞ በታቀደለት መርሃ ግብር በተዋጣለት ሁኔታ

ተጠናቅቆ ሁሉም ተጓዦች በሰላም ወደ ሃገራቸው ተመልሰዋል፡፡

በትንሣኤ በዓል ከሚያዝያ 21 እስከ ግንቦት 5 2005 ዓ.ም. ለ14 ቀናት የሚደረገውም የጉብኝት መርሃ ግብር ምዝገባው ከወዲሁ

በመጠናቀቅ ላይ ሲሆን ቦታ ሳይሞላባችሁ እስከ የካቲት 15 2005 ዓ/ም ድረስ የታደሰ ፓስፖርታችሁን በመያዝ ምዝገባችሁን

እንድትፈጽሙ በዚሁ አጋጣሚ ዮድ አቢሲኒያ ለማስታወስ ይወዳል፡፡

ያስተውሉ! ባለ አምስት ኮከብ ሆቴልና ልዩ የትንሳዔ የምሳ ግብዣ መዘጋጀቱ፣

በታዋቂ የፊልም ድርጅት ጉብኝቱ ተቀርፆ በዲቪዲ እና ፎቶግራፎች ደግሞ በሲዲ በነፃ ለተጓዦች መስጠቱ፣

ስለሚጎበኙ ቦታዎችና ስለጉብኝቱ ፋይዳ ግንዛቤ የሚያስጨብጥ የጉዞ መፅኄት መካተቱ፣

ስለኢየሩሳሌምና አካባቢው የጠለቀ እውቀት ያላቸው ተጋባዥ አባቶችና ታዋቂ የስብከተ ወንጌል መምህራን ከምዕመን ጋር

በመጓዝ ትምህርትና ማብራሪያ መስጠታቸው፣

ሙሉ የጉዞ ኢንሹራንስ መካተቱ ‘የጃንደረባው ጉዞ’ን ለየት ከሚያርጉት ነጥቦች ጥቂቶቹ ናቸው፣

አድራሻችን ቦሌ መድሐኒያለም ቤተክርስቲያን ዝቅ ብሎ፣ ከዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ቅጥር ግቢ፣ ለሚኖርዎ ማንኛውም ጥያቄ ይደውሉልን፡ 0116 614 479 0116 612 154 ኢሜይልም ያድርጉልን: [email protected]

ድህረ ገፃችንንም ይጎብኙ፡ www.yodabyssiniatour.com

የዮድ አቢሲኒያው ‘የጃንደረባው ጉዞ’ ወደ ቅድስት ሃገር ኢየሩሳሌም የልደት/ገና ጉዞ በታቀደለት መርሃ ግብር በተዋጣለት ሁኔታ

ተጠናቅቆ ሁሉም ተጓዦች በሰላም ወደ ሃገራቸው ተመልሰዋል፡፡

በትንሣኤ በዓል ከሚያዝያ 21 እስከ ግንቦት 5 2005 ዓ.ም. ለ14 ቀናት የሚደረገውም የጉብኝት መርሃ ግብር ምዝገባው ከወዲሁ

በመጠናቀቅ ላይ ሲሆን ቦታ ሳይሞላባችሁ እስከ የካቲት 15 2005 ዓ/ም ድረስ የታደሰ ፓስፖርታችሁን በመያዝ ምዝገባችሁን

እንድትፈጽሙ በዚሁ አጋጣሚ ዮድ አቢሲኒያ ለማስታወስ ይወዳል፡፡

ያስተውሉ! ባለ አምስት ኮከብ ሆቴልና ልዩ የትንሳዔ የምሳ ግብዣ መዘጋጀቱ፣

በታዋቂ የፊልም ድርጅት ጉብኝቱ ተቀርፆ በዲቪዲ እና ፎቶግራፎች ደግሞ በሲዲ በነፃ ለተጓዦች መስጠቱ፣

ስለሚጎበኙ ቦታዎችና ስለጉብኝቱ ፋይዳ ግንዛቤ የሚያስጨብጥ የጉዞ መፅኄት መካተቱ፣

ስለኢየሩሳሌምና አካባቢው የጠለቀ እውቀት ያላቸው ተጋባዥ አባቶችና ታዋቂ የስብከተ ወንጌል መምህራን ከምዕመን ጋር በመጓዝ ትምህርትና ማብራሪያ መስጠታቸው፣

ሙሉ የጉዞ ኢንሹራንስ መካተቱ ‘የጃንደረባው ጉዞ’ን ለየት ከሚያርጉት ነጥቦች ጥቂቶቹ ናቸው፣

አድራሻችን ቦሌ መድሐኒያለም ቤተክርስቲያን ዝቅ ብሎ፣ ከዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ

ቅጥር ግቢ፣ ለሚኖርዎ ማንኛውም ጥያቄ ይደውሉልን፡ 0116 614 479 0116 612 154

ኢሜይልም ያድርጉልን: [email protected]

ድህረ ገፃችንንም ይጎብኙ፡ www.yodabyssiniatour.com

Page 20: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 20 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ሁኔታ መጨመሩ ብቻ ሳይሆን የዓባይን ውኃ ጥቅም ላይ የማዋል አቅማቸውም ጨምሯል:: አካባቢው በእርስ በርስ ግጭት ከመታመስ ወጥቶ በአንፃራዊ ሰላም ውስጥ ይገኛል:: ስለዚህ ግብፅ ውጤታማ፣ ፍትሐዊ፣ ትክክለኛና ምክንያታዊ የዓባይ አስተዳደርን የተመለከተ ስምምነት እንድታደርግ ለማግባባት ሞክረዋል::

እ.ኤ.አ. ከ2007 እስከ 2010 ድረስ በዘለቀው የናይል ኢኒሺዬቲቭ የውይይት መድረክ ግብፅ ለመሳተፍ ብትችልም፣ በናይል የትብብር ማዕቀፍ ረቂቅ ስምምነት ላይ በአንቀጽ 14(ለ) ላይ ‹‹በማንኛውም የዓባይ ተፋሰስ አገሮች የውኃ ደኅንነት ላይ መሠረታዊ ጉዳት ማድረስ አይቻልም፤›› የሚለውን ክፍል ግብፅና ሱዳን ለመፈረም አልፈቀዱም:: ግብፅ ከላይ የተገለጸው ክፍል ‹‹በማንኛውም የዓባይ ተፋሰስ አገሮች የውኃ ደኅንነትና የአጠቃቀም ይዞታ ላይ አደገኛ ጉዳት ማድረስ አይቻልም፤›› በሚል እንዲቀየር ሐሳብ አቅርባ ስምምነቱ እንዲፈርስ አድርጋለች::

የላይኛው የዓባይ ተፋሰስ አገሮች ግብፅን ለማሳመን ያደረጉት ጥረት አለመሳካቱን ተከትለው የቀድሞ ስምምነቶችን እንደማይቀበሉ በመግለጽ ግብፅን ያገለለ የራሳቸውን ስምምነት ለማድረግ በሒደት ውስጥ ይገኛሉ:: ግብፅ በኢትዮጵያ የበላይነት የሚደረገውን ይህን ጥረት በወታደራዊ ኃይል በማስፈራራትና አገሮችን በጥቅም በማሰር ኢትዮጵያን እንዳይተባበሩ ለማድረግ ስትጥር መቆየቷ ይታወሳል::

ኢትዮጵያ ከሌሎች የተፋሰሱ አገሮች በተለየ ሁኔታ እ.ኤ.አ. በ1929 እና በ1959 የተደረገጉት ስምምነቶች ሲደረጉ ያልተማከረችና ያልተሳተፈች ስትሆን፣ ግብፅ የህዳሴ ግድብ ዕቅድን ኢትዮጵያ አላማከረችኝም በማለት ግን ትከሳለች::

መጪው ጊዜግብፅ ተሰሚነታቸው ከፍተኛ የነበረውን የቀድሞውን

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ሞት እንደ መልካም አጋጣሚ ልትጠቀምበት እንደምትችል የሚጠቁሙ ዘገባዎች ክረምት ላይ ተሰምተው ነበር:: ዘገባዎቹ ኢትዮጵያ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ የጀመረችው ግብፅ አለመረጋጋት ላይ መሆኗን በመጠቀም መሆኑን ጠቁመው፣ አሁን ተራው የግብፅ ነው በማለት ምክር ቢጤም ጣል አድርገው ነበር::

ይሁንና ኢትዮጵያ በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ አማካይነት የተጀመሩትን ነገሮች ከመቀጠል ውጪ በዓባይ ጉዳይ የተለወጠ ነገር የለም:: በግብፅ በኩል ግን አዲሱ ፕሬዚዳንት ከውጥረት ወደ ውጥረት መሸጋገራቸው ለኢትዮጵያ ሌላ መልካም አጋጣሚ አምጥቷል ብለው ብዙዎች እንዲከራከሩ አድርጓል::

አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ግብፅ የአገር ውስጥ ፖለቲካዋን ለማርገብና የሕዝቡን ትኩረት ለመሳብ ከኢትዮጵያ ጋር ጦርነት ልትመርጥ እንደምትችል ይገምታሉ:: እ.ኤ.አ በ2010 ዊኪሊክስ ባሠራጨው መረጃ መሠረት ግብፅ ከሱዳን ጋር በመተባበር የኢትዮጵያን ግድብ የማጥቃት ዕቅድ እንደነበራት መገለጹ ይህን የሚያጠናክር ነው:: ግብፅ በተደጋጋሚ ግድቡ የውኃውን ፍሰት እንደሚያስተጓጉል መግለጿም ይታወሳል:: በሁለቱ አገሮች መካከል ጦርነት ሊነሳ ይችላል የሚል ሥጋት ያለ ቢሆንም፣ ሁለቱ አገሮች ጦርነት ውስጥ ቢገቡ የሚገጥማቸው ፈተና ከባድ መሆኑን በመጥቀስ ብቸኛው አማራጭ ተስማምተው ልማት ላይ ቢሠሩ እንደሆነ የሚመክሩት በርካቶች ናቸው::

ግብፅ ወደ ጥልቅ አለመረጋጋት መግባቷ ግን ኢትዮጵያ ግድቡን ተረጋግታ ለመሥራት ፋታ እንደሚሰጣት ብዙዎች ይስማማሉ:: ኢትዮጵያ ሌሎቹን የተፋሰስ አገሮች ማለትም ኮንጎ፣ ሱዳንና ደቡብ ሱዳንን ለማስማማትም ሁኔታው አጋጣሚን እንደሚፈጥርለት ተስፋ ያደረጉም አሉ::

ዶ/ር ታደሰ ካሳ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግና ገቨርናንስ ስተዲስ ኮሌጅ ዲን ሲሆኑ በቅርቡ፣ ‹‹International Water Courses Law and the Nile River Basin Three States at a Crossroad: Egypt, Sudan and Ethiopia›› የተሰኘ መጽሐፍ አሳትመዋል:: ዶ/ር ታደሰ የግብፅ ብጥብጥ በናይል ፖለቲካ ላይ ከባድ ተፅዕኖ እንዳለው ያስረዳሉ:: ‹‹ሁሉንም ነገር በሕግ አግባብ የመፍታት ሙከራ ቢኖርም ይህ ሁልጊዜ አይሠራም:: የኢኮኖሚ መነሳሳትና የፖለቲካ መረጋጋት ትልቅ ሚና አላቸው:: የግብፅ አለመረጋጋት ለኢትዮጵያ ዘላቂ መፍትሔ መሆኑ አጠያያቂ ነው:: ይሁንና የአጭር ጊዜ ጥቅሙን ካየን እፎይታ የሚሰጥና መልካም አጋጣሚ የሚፈጥር ነው፤›› ይላሉ::

ዶ/ር ታደሰ ግብፅ በብጥብጥ ውስጥ ተዘፍቃ እንደማትቀር ግን ያስጠነቅቃሉ:: ‹‹አሁን ግብፅ ያለችበት ሁኔታ ኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በፊት የነበረችበት ነው:: የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ግብፅ ከዚህ ሁኔታ ትወጣለች:: ያኔ ግብፅ መልሳ ዓባይን ዋነኛ አጀንዳዋ ማድረጓ አይቀርም:: ምክንያቱም ዓባይ ለግብፅ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ሕግና የማንነት ጉዳይ ስለሆነ፤›› በማለት ያክላሉ::

ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች የኢትዮጵያ ማንኛውም እንቅስቃሴ ግብፆችን በዓባይ ዙሪያ ልዩነትን አቻችለው በአንድነት እንዲሠሩ በማድረግ ተቃዋሚዎችንና መንግሥትን የማስታረቅ ሚና ሊኖረው እንደሚችል በማስጠንቀቅ፣ ኢትዮጵያ አጋጣሚውን በብልህነት እንድትጠቀም ይመክራሉ::

የግብፅ ብጥብጥና... ከክፍል-1 ገጽ 6 የዞረ

መጠን እንዲሁ ከፍተኛ ዕድገት እያሳየ እንደሚቀጥል በሰነዶች ሲረጋገጥ፣ ለምሳሌ በዚህ ዓመት ብቻ 364 ሺሕ 531 ቶን ቡና ለመላክ ታቅዷል:: እንዲሁም በ2006 ዓ.ም. ደግሞ ከ460 ሺሕ በላይ ቶን ለመላክ ዕቅድ መያዙንም ጥናቱ ያስታውሳል::

በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ የመጨረሻ ዓመት (በ2007 ዓ.ም.) አገሪቱ በግብርና ጥገኛ መሆኗ ቀንሶ ወደ ኢንዱስትሪ የምትሸጋገርበት ዕድልን መክፈት የሚችል መሆኑ ጥናቱ አስታውሷል:: ነገር ግን የዕቅድ ዘመኑ ሦስተኛ ዓመት ላይ ቢገኝም፣ ኢንዱስትሪው በተለያዩ ችግሮች ምክንያት የሚፈለገውን ያህል ውጤት እያስገኘ አይደለም በማለት ገልጿል::

መንግሥት ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለመሸጋገር የተለያዩ ማበረታቻዎችን የሚያደርገው የተያዘውን ውጥን ከግብ ለማድረስ ሲሆን፣ ለአምራች ላኪዎችና ቀጥተኛ ላልሆኑ አምራች ላኪዎች እንዲሁም ለላኪዎች ጥሬ ዕቃ አቅራቢዎች የተለያዩ ዓይነት የማበረታቻ ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ የሚያደርግ ሥርዓት መዘርጋቱን ጥናቱ በዝርዝር አስቀምጧል::

በተመሳሳይ መንገድ ለኢንቨስተሮች በተለይም ደግሞ ምርቱን ወይም አገልግሎቱን ወደ ውጭ ለሚልክ ባለሀብት ስለ ኢንቨስትመንት ማበረታቻዎች የወጣው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ የገቢ ግብር ማበረታቻን ሰጥቷል:: እንዲሁም የካፒታልና የግንባታ ዕቃዎችንና ተሽከርካሪዎችን ከጉምሩክ ነፃ በማድረግ ማበረታቻዎችን ዘርግቷል:: ይሁን እንጂ የኢንዱስትሪው ዕድገት የተፈለገው ደረጃ ላይ አለመድረሱን ገልጿል::

ዕድገቱ የተፈለገውን ያህል ያልሆነበትን ምክንያትም የዳሰሳ ጥናቱ ለማሳየት ሞክሯል:: የኢንቨስትመንት በተለይም የወጪ ንግዱ በተለያዩ ተግዳሮቶች ሥር መሆኑን በዘርፉ የሚሳተፉ የንግድ ማኅበረሰብ እንደሚገልጹ በማስታወስ፣ አሉ ካላቸው ችግሮች ውስጥ በመጀመሪያ ደረጃ

ያስቀመጠው የገንዘብ አቅርቦት ችግርን ነው::

በገንዘብ አቅርቦት ችግር ዙሪያ በቀረበ ማብራሪያ የኢትዮጵያ የግል ዘርፍ በአመዛኙ ከሚያጋጥመው ትልልቅ ችግሮች የፋይናንስ አቅርቦት አንዱና ዋነኛው መሆኑን ጥናቶችም እንዲሁም የንግዱ ማኅበረሰብ ይገልጻሉ ይላል:: በዚህም የተነሳ ተርም ሎንም ሆነ የኦቨር ድራፍት ብድር በሚገባው መጠን እንደማይገኝ እንደሚያመለክቱ አትቶ፣ ይህ ችግር መንግሥት ትኩረት በሰጠው በወጪ ንግድ ዘርፍ እየተንፀባረቀ መምጣቱ ትልቅ ክፍተት ሆኗል:: ለዚህም ክስተት የባንኮች የገንዝብ የማበደር አቅም ውስን መሆን እንደ ምክንያት ቀርቧል:: ይህ ችግር ደግሞ በግል ባንኮች ላይ ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል:: ይህን የፋይናንስ አቅርቦት ችግር በተወሰነ ደረጃ ለመፍታት ያግዛሉ ተብለው የሚታመኑ ዕርምጃዎች እንደሚኖሩ ያመለከተው የዳሰሳ ጥናት፣ በዚህ ረገድ እንደመፍትሔ ያስቀመጣቸው ነጥቦችም አሉ:: ወደ ውጭ በመላክ የተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች ለምርት ግብዓት የሚሆን ጥሬ ዕቃ ከውጭ የሚያስመጡበት ሁኔታ ያለ ሲሆን፣ ለዚህ ተግባር የሚሆን የውጭ ምንዛሪ በተፈለገው መጠንና ግዜ የማያገኙበት ሁኔታ መፍትሔ የሚፈልግ ነው ብሏል:: በመሆኑም በዚህ ረገድ ያለው ችግር ስለሚታይ ይህንን ለመቅረፍም ባንኮች ለእነዚህ ኢንዱስትሪዎች ቅድሚያ የሚሰጡበት የአሠራር መመርያ ቢዘጋጅ ጥሩ መፍትሔ መሆኑን አስቀምጧል:: ይህ የመፍትሔ ሐሳብ እንደተጠበቀ ሆኖ ላኪዎች ከባንኮች የሚገዙት የውጭ ምንዛሪ በባንኮች በመሸጫ ዋጋ ሲሆን፣ እነሱ ያስገኙትን የውጭ ምንዛሪ ለባንኮች ሲሸጡ ግን ባንኮች ለማንኛውም አቅራቢ በሚሸጡበት ዋጋ የሚተመን በመሆኑ፣ ይህም ደግሞ ለላኪዎች የሚያበረታታ አሠራር አይደለም ተብሏል:: ይህንንም በመገንዘብ አገሮች በዚህ መልክ የሚገኝን ትረፍ ግማሽ በግማሽ ለላኪዎች የሚሆንበትን አሠራርና ደንብ ነድፈዋል:: ሌሎች ደግሞ ለላኪዎች የተለየ የግዥ ዋጋ በመተመን ላኪዎችን ያበረታታሉ::

ይህን ከግንዛቤ በማስገባት ላኪዎችን ማበረታታት የሚያስችል የግብይት ተመን ቢወሰን፣ አግባብነት እንደሚኖረው የመፍትሔ ሐሳቡ ያስገነዝባል::

የገንዝብ አቅርቦት ችግር ከሚያስከትለው ምክንያት አንዱ በባንኮች የተጣለው በየብደር መጠኑ 27 በመቶ ያህል የብሔራዊ ባንክ የቦንድ ግዥ አሠራር ለወጪ ንግዱ ሌላ እንቅፋት ሆኖ መቀመጡን አመልክቷል:: ይህ የመፈጸም ግዴታ ለአገሪቱ ጠቅላላ ዕድገት የሚያስገኘው ጉልህ ፋይዳ አሌ የማይባል ቢሆንም፣ የውጭ ንግዱን ከማበረታታት አንፃር ግን ይህን መስፈርት ለውጭ ላኪ ተበዳሪዎች የሚቀርበትን ሁኔታ መዘርጋት አግባብነት አለው በማለት የዳሰሳ ጥናቱ አመልክቷል::

ባንኮች የብደር አቅርቦታቸውን ለኢንዱስትሪዎችና ለወጪ ንግድ ተሳታፊዎች ቅድሚያ እንዲሰጡ መንግሥት እያደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም የጥናቱ የመፍትሔ ሐሳብ አመልክቷል:: ለዚህም የተለያዩ የማበረታቻ ዘዴዎች ቢነደፉ የባንኮችን የብድር ትኩረት ወደ ወጪ ንግድ ተሳታፊ ነጋዴዎች እንዲሁም ለኢንዱስትሪዎች እንዲሆን የማድረግ ሚና ይኖረዋል ብሏል::

ከገቢዎችና ጉምሩክ አሠራር ጋር ተያይዘው የሚነሱ ችግሮችም በዚህ የዳሰሳ ጥናት ውስጥ ተካተዋል:: የንግድ ምክር ቤቶች በተለያዩ ፎርሞቻቸው ላይ የጉምሩክ ጉዳይ በተደጋጋሚ ይቀርባል:: በዚህም የዳሰሳ ጥናት ውስጥ ተካትቷል::

የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ከፍተኛ የሚባሉ ለውጦችን ለመዘርጋት ዝግጅቱን እያጠናቀቀ መሆኑ የማይካድ ሃቅ መሆኑን የሚያትተው ይኸው ጥናት፣ በአሁኑ ወቅት ተግባራዊ የሆኑ አሠራሮችና ሕጎች ግን በወጪ ንግዱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያደረሱ ስለመሆኑ በአጽንኦት አስቀምጧል:: የገቢዎችና ጉምሩክ አሠራር በወጪ ንግዱ ላይ አሳደረ ብሎ ካስቀመጣቸው ነጥቦች መካከል፣ ፈጣንና ቀልጣፋ ያልሆነ አሠራር መኖሩ ዋነኛ ምክንያት ሆኖ ቀርቧል::

ወደ ውጭ ለመላክም ሆነ ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት መተግበር ያለባቸው የጉምሩክ ሥነ ሥርዓቶች በተቀላጠፈ አጭርና ወጭ ቆጣቢ በሆነ መልኩ እየተፈጸሙ አይገኝም። ለዚህም የጉምሩክ ውስጣዊ አሠራርም ሆነ ሌሎች የመንግሥትና የግል ዘርፍ ባለድርሻ አካላት አስተዋጽኦ ያደርጋሉ። በእርግጥም የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ድርጅት ከተለያዩ የመንግሥት አስፈጻሚ አካላት ጋር የሚሠራ ተቋም እንደመሆኑ፣ ሌሎች እህት ድርጅቶች ሥራቸውን በተፋጠነ ሁኔታ ያለመፈጸም በጠቅላላ አገልግሎቱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል።

በዚህና ሌሎች የውስጥ ችግሮች የተነሳም የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት አጭርና የተቀላጠፈ መሆኑ ቀርቶ የተንዛዛ ሥርዓት የሚከተል በመሆኑ በወጪ ንግዱ ተወዳዳሪነት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛል በማለት የዳሰሳ ጥናቱ አመልክቷል:: ይህንንም ለመቅረፍ ጉምሩክ በጅምር ላይ ያሉ ማሻሻያዎችን በቶሎ ተግባራዊ ማድረግ ይገባዋል:: በተለይም ጉምሩክ ለፉብሪካ ጥሬ ዕቃዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት ቶሎ እንዲለቀቁ የሚቻልበትን ሥርዓት ማመቻቸት እንደሚኖርበት ጠቅሷል::

የትራንስፖርትና ሎጅስቲክ አገልግሎት በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ አለመቅረብ የኢትዮጵያን የወጪ ንግድ አሉታዊ ተፅዕኖ ከሚያሳድሩ ምክንያቶች መካከል አንዱ መሆኑ ተወስቷል:: በዚህ ዘርፍ የጥራት ችግርና የዋጋ ከፍ ማለት በዘረፉ ተወዳዳሪነት ላይ ጫና እየፈጠረ በመገኘቱ መፍትሔ ያስፈልጋል ተብሏል::

በዚህ ዘርፍ አሉ የሚባሉት ችግሮች ውስጥ አንዱ የመልቲ ሞዳል ትግበራ ያስከተለው ችግር ነውም ይላል:: የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት አገልግሎት በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ወደብ አልባ ለሆኑ አገሮች ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚያስገኝ የብዙ አገሮች ልምድ ቢያሳይም፣ አተገባበሩ ላይ ክፍተት አለ ብሏል:: በዝግጅት ማነስ ትግበራው የታለመትን ያህል ስኬታማ እየሆነ ነው ለማለት ጥናቱ አልደፈረም:: ዕቃዎች ከወደብ በጊዜ አለመነሳት፣ የዕቃዎች መሰወር፣ የመጠቀሚያ ጊዜ ማለፍና መበላሸት፣ ለወደብ ኪራይና ለትራንስፖርት ዋጋ ንረት መዳረግ፣ ለፋብሪካዎች ጥሬ ዕቃ በወቅቱ አለመቅረብን በማስከተሉም ብዙዎች አቤቱታዎችን

እንዲያሰሙ አድርጓቸዋል:: ይህንን ችግር ለመፍታት ከሚያስችሉ ዕርምጃዎች መካከል የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት አገልግሎትን ከመንግሥት ባሻገር በግል ዘርፉ በተሰማሩ የጭነት አስተላላፊዎችና የመርከብ ወኪሎች እንዲተገበር ማድረግ ሲሆን፣ ከዚህ በተጨማሪ ለሥርዓቱ ውጤታማነት የሚያስፈልጉ መሠረተ ልማቶች እንዲሁም የሰው ኃይል ማሟላት የግድ መሆኑን እንደ መፍትሔ አስቀምጧል::

በዚህ ዳሰሳ ጥናት በኢንቨስትመንትና በወጪ ንግድ ትግበራ ዙሪያ ሌሎች በርካታ ክፍተቶች መኖራቸውን በዝርዝር ያስቀመጠ ሲሆን፣ የትራንስፖርት ዋጋ መወደድ ሊታሰብበት ይገባልም ተብሏል:: በዚሁ ጥናት ውስጥ የትራንስፖርት ዋጋ ውድ መሆን በአሁኑ ጊዜ ዕቃን ከጅቡቲ ወደ አዲስ አበባ ከማጓጓዝ ከቻይና ወይም ከህንድ ወደ ጅቡቲ ማጓጓዝ ርካሽና ቀላል እንደሆነ አስመጪዎች እያስረዱ ነው ይላል:: በተመሳሳይ መንገድ አስመጪዎች እንደሚያስረዱት፣ የኢትዮጵያ መርከብ ድርጀት የሚጠይቀው ዋጋ ከዓለም ገበያ ከፍ ያለ በመሆኑ ለኢንቨስትመንት አስቸጋሪ መሆኑን እንደሚያመለክት ጠቅሷል:: የትራንስፖርት ውድነት ደግሞ የአገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎችንም ሆነ ኤክስፖርተሮችን ተወዳደሪነትን እየጎዳ የሚገኝ በመሆኑ፣ መንግሥትም ይህን ከግንዛቤ በማስገባት የኢትዮጵያ መርከብ ድርጅት የሚጠይቀው ዋጋ ሌሎች የመርከብ ደርጅቶች ከሚጠሩት ዋጋ ጋር ተመጣጣኝ እንዲሆን መደረግ አለበት የሚል እምነት ተንፀባርቋል:: በተጨማሪም በአገር ውስጥ የየበስ ትራንስፖርት ውድነት መንስዔ በማጥናት ተገቢውን ዕርምጃ ቢወስድ ለወጪ ንግዱ ተወዳዳሪነትም ሆነ በአገር ወስጥ ላሉ ኢንዱስትሪዎች ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረውም ጥናቱ አመላክቷል::

ከዚሁ ጋር ተያይዞ አገሪቱ በየዓመቱ በብዙ ሚሊዮኖች የሚገመት ገንዘብ ለኮንቴይነር ኪራይ እንደምታወጣ መረጃዎች የሚያመለክቱ ሲሆን፣ ዕቃ ይዞ የመጣ ኮንቴይነር ዕቃው ከተራገፈ በኋላ ባዶውን ሞጆ ደረቅ ወደብ ላይ ይጠራቀማል:: ጉምሩክ ወደ አገር ወስጥ ለሚገቡ ኮንቴይነሮች 8,000 ብር ማስያዣ ስለሚጠይቅ ይህን ብር እንዲለቀቅላቸው አስመጪዎች ባዶውን ለመመለስ ይገደዳሉ:: ተሽከርካሪዎች ደግሞ ባዶ ኮንቴይነር ጭነው ለመሄድ ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ ይጠይቃሉ:: በሌላ በኩል ደግሞ የኤክስፖርት ዕቃዎች በተለያዩ ዕቃዎች ታሽገው ወደ ጅቡቲ ከተላኩ በኋላ ተራግፈው በኮንቴይነር ይጫናሉ:: ይህም አላስፈላጊ ለሆነ ከፍተኛ ወጪ እያዳረጋቸው እንደሆነ ላኪዎች መግለጻቸውን ጥናቱ አስታውሷል:: በተለይ ከቅርብ ግዜ ወዲህ የመርከብ ድርጅቶች ወኪል ሆነው የሚሠሩ ኩባንያዎች ቀደም ብለው በነፃ ሲሰጡ ለነበሩ አገልግሎቶች ክፍያ መጠየቅ መጀመሩ ተገቢ አለመሆኑን ጠቅሷል:: ለዚህም ባቀረበው ምሳሌ ለመርከብ ጭነት ዝርዝር መግለጫ፣ 25 ዶላር ለክራፍት ወረቀት፣ እንደ ሲሚንቶ ወረቀት ያለ ሲሆን አገልግሎቱም ቡና ኮንቴይነር ውስጥ በሚሆንበት ወቅት እርጥበት እንዳይስብ ነው:: 60 ዶላር ለኮንቴይነር ማሸጊያ እንዲሁም ለቁልፍ እስከ ሦስት ዶላር ይከፈልበታል ብሏል::

እነዚህ አገልግሎቶች በሙሉ ከዚህ ቀደም በነፃ የሚሰጡ የነበረ ሲሆን፣ ይህን ችግር ለመፍታት የኤክስፖርት ዕቃዎች ሞጆ ደረቅ ወደብ ላይ በኮንቴይነር ታሽገው ለወጪ ገበያ እንዲቀርቡ ቢደረግ ብዙ ወጪ ማዳን ይቻል እንደነበር አመልክቷል:: ለዚህ ደግሞ አስመጪዎች የሚያመጡበትን ኮንቴይነር ባዶውን እንዳይመለስ የሚያደርግ አሠራር ማመቻቸት እንደሚኖርበት አስገንዝቧል::

ላኪዎችም በተለይም ቡና ላኪዎች የክራፍት ወረቀት በማስመጣት መጠቀም እንዲችሉና ይህንኑ ወረቀት ከቀረጥ ነፃ የሚያስገቡበትን ሥርዓት መዘርጋትም ለወጪ ንግዱ መበረታታት አስተዋጽኦ ይኖረዋል:: ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ግን የኢትዮጵያ የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኮንቴይነር እንዲያመርት ቢደረግ አገሪቱን ከአላስፈላጊ የውጭ ምንዛሪ ወጪ መታደግ የሚቻል መሆኑንም እንደ መፍትሔ አስቀምጧል::

የኢንቨስትመንትና... ከክፍል-1 ገጽ 10 የዞረ

Page 21: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 21 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1

ማስታ

ወቂያየኦዲት ማስታወቂያ

የኪሞዬ ሊንሰን ሮዝስ ጆይንት ቦዲ ማህበር የ2012ን እ.አ.አ. ኦዲት ለማስደረግ ስለሚፈልግ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟላ ኦዲተር ይፈልጋል፡፡

ሀ/ ኦዲተሩ የሙያ ማረጋገጫ ያለው፣

ለ/ የንግድ ፈቃድ ያለው፣

ሐ/ የዘመኑን ግብር ስለመክፈሉ መረጃ ማቅረብ የሚችል፣

መ/ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያለው፣እና

ሠ/ የፌዴራል ወይም የክልል ኦዲተር መስሪያ ቤት ለበጀት ዓመቱ የታደሰ ፈቃድ ያለው መሆን ይኖርበታል፡፡

የተዘረዘሩትን መስፈርት የሚያሟላ ተወዳዳሪ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ፣ በአምስት ተከታታይ ቀናት ውስጥ አስፈላጊውን ማስረጃ ማስገባት ይኖርበታል፡፡

አድራሻ፡ ሊንሰን ሮዝስ ኢትዮጵያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

ከብስራተ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ወረድ እንዳሉ፣ በአዲስ ሆም

ዴፖ 250 ሜ. ወደ ውስጥ

ገባ ብሎ

ስልክ፡- 0113 20 56 68

ኢሜል፡ [email protected]

የፖ.ሳ.ቁ 5750 አ.አ

በሚዲያና ኮሙዩኒኬሽንስ ሴንተር እየታተሙ በሚወጡት የሪፖርተር ጋዜጦች አልፎ አልፎ የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅትን መልካም ስም በሚያጎድፉ ጽሑፎችና ካርቶን ሥዕሎች ለአንባቢ በቅተዋል::

ይህን ደብዳቤ የጻፍነው ለሪፖርተር ጋዜጣ ስለ ሐተታ ጽሑፎች ወይም ስለ ካርቱን ሥዕሎች ለመንገር በመፈለግ ሳይሆን፣ ስለ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት የቀረቡት ጽሑፎችና ካርቶን ሥዕሎች ሙሉ በሙሉ በትክክለኛ መረጃ ላይ ያልተመሠረቱና በመሆናቸው ነው:: ስለሆነም ከእውነት የራቀ ሐሳብን በመጻፍና በማቅረብ አንባቢያንን ለማደናገር መሞከር ፍጹም ተዓማኒነትን የሚያሳጣ ስለሚሆን እውነታውን ማስቀመጥ ያስፈልጋል በሚል ነው::

ከራስ ጠቀሜታ ብቻ በማየት 24 ሰዓት አገልግሎት እየሰጠ ያለውን ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ለማጠየም መሞከር፣ ድርጅቱን ጠንቅቀው ለሚያውቁና ከእውነታው ጋር ለሚያገናዝቡት አንባቢዎችና ደንበኞች የሚዲያ ኮሙዩኒኬሽንስ ሴንተር (ሪፖርተር ጋዜጣ) ያወጣውን ጽሑፍ ግምት ውስጥ የሚጥል ነው::

የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽንስ ሴንተር ስለ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ለመጻፍ ካስፈለገው፣ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት እንኳን ለደንበኛው ለሪፖርተር ጋዜጣ ይቅርና መረጃ ለሚፈልግ ሁሉ በሩ ክፍት ነው::

በአገራችን ውስጥ በየትኛውም ክልል ሕትመት ሲነሳ ብርሃንና ሰላም፤ ብርሃንና ሰላም ሲነሳ ሕትመት ሳይነሳ የቀረበት አጋጣሚ የሌለ መሆኑ በስፋት ይታወቃል:: ምክንያቱም የሕትመት ቴክኖሎጂን ወደ አገር ውስጥ በማስገባት፣ የሕትመት ኢንዱስትሪውን በማጎልበትና ተጠቃሚውን በማገልገል ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት 90 ዓመታትን በጥንካሬ አሳልፏል::

ባሳለፋቸውም ዓመታት ሚስጥራዊ ሕትመቶችን ጨምሮ መጻሕፍትን፣ መጽሔቶችን፣ ጋዜጦችን፣ ደረሰኞችንና ሌሎችንም ሕትመቶች በማተም ለኅብረተሰቡ በአግባቡ አገልግሎት እየሰጠ ያለ ድርጅት

ነው:: አሁንም ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት አገልግሎቱን በማስፋት ደንበኞቹንና ተጠቃሚዎቹን እያስተናገደ እንደሚገኝ ይታወቃል::

አገራችን ድህነትን ለማጥፋት፣ ዕድገትና ልማትን ለማፋጠን በምታደርገው ከፍተኛ ርብርብ የሁሉም ዘርፍ የሥራ ውጤት መሆኑን በመገንዘብ ብርሃንና ሰላምም የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል:: ለዚህም ነው በየዓመቱ አመርቂ ውጤት እያስመዘገብን የምንገኘው::

ሁሉም በተሰማራበት መስክ በየዘርፉ በትጋት በመንቀሳቀስ በትምህርት፣ በጤና፣ በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት፣ በኢንዱስትሪው፣ በግብርናው ወዘተ. ለዕድገትና ለልማት በከፍተኛ ሁኔታ እየሠሩ መሆናቸውን መረጃዎች ይጠቁማሉ:: በእያንዳንዱ ዘርፍ የሚደረገው እንቅስቃሴም ከሕትመት አገልግሎት ጋር የተያያዘ መሆኑ እሙን ነው:: ሁሉም ክልሎች የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት የሕትመት ተጠቃሚዎችና ደንበኞች ናቸው:: ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅትም የተጠቃሚዎቹንና የደንበኞቹን ፍላጎት ለማሟላትና በሥራ ዘርፋቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ዘወትር የላሰለሰ ጥረት በማድረግ የሚሠራ የሕትመት ተቋም ነው::

ለዚህም ራሱ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽንስ ሴንተር ማሳያችንና ምስክር ነው:: ከአንድ ጋዜጣ ሁለት ጋዜጣ ማሳተም (አማርኛና እንግሊዘኛ ጋዜጣ) ደርሷል:: በሳምንት አንድ ጋዜጣ ከማሳተም በሳምንት ሦስት ጋዜጦችን (ሁለት አማርኛና አንድ እንግሊዘኛ ጋዜጦችን) ለአንባቢ አድርሷል:: ከ20 አካባቢ በአማካይ ወደ 160 ገጾች ለመድረስ በቅቷል::

ከ1500 ቅጂ አካባቢ በአማካይ 15,000 ቅጂ አሳድጓል:: ከጥቁርና ነጭ ቀለም የባለቀለም ጋዜጦችን ማሳተም ችሏል:: በጋዜጣው እንደነገረንም የማተሚያ ቤት ሕንፃ መገንባት መቻሉን ገልጿል:: ከጥቂት ሠራተኞች በርካታ ሠራተኞችን ማስተዳደር ወዘተ. የተቻለው ዘወትር በዕድገትና ልማት ጎዳና ላይ ባለው

ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ጋዜጦችን በማሳተም መሆኑን ለሚዲያና ኮሙዩኒኬሽንስ ሴንተር መንገር ማለት ቀባሪውን አረዱት እንደማለት ነው:: ብርሃንና ሰላም እንኳን ለራሱ ለደንበኞቹም ዕድገት በከፍተኛ ደረጃ የሚጥር መሆኑን ሊረዱት ይገባል::

የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽንስ ሴንተርም ከምን ተነሳሁ? ምን ደረጃ ላይስ እገኛለሁ? ለዚህስ ውጤት መብቃት የቻልኩት በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት በመሥራቴና ባለኝ መልካም የሥራ ግንኙነት አይደለም? በሚል ማሰብ ቢቻል ኖሮ፣ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅትን ጠንቅቆ ማወቅ ይቻል ነበር::

ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት እንደ ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽንስ ሴንተር ዓይነት ደንበኞችን ከምንም ተነስተው ዛሬ ለደረሱበት የዕድገት ደረጃ ለማብቃት የበኩሉን ድርሻ በመወጣቱ እጅግ ደስተኛ ነው:: ምክንያቱም ለዕድገት ያደረገው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ስለሚገነዘብ:: ከዚህም በላይም እንዲያድግ የሚጠበቅብንን አገልግሎት ሁሉ ለመስጠት ዘወትር ዝግጁ ነን:: ምክንያቱም ደንበኞቻችን ንጉሦቻችን ናቸውና::

ለዚህም ነው ዛሬም ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ደንበኞቹ ምንግዜም በሕትመት አገልግሎት አሰጣጣችን ደስተኛ ሆነው እንዲስተናገዱ ትልልቅና አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በመቅረፅ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው::

ድርጅቱ እነኚህን በርካታ ተግባራት ሲያከናውን ግን ችግር የለበትም ወይም አልገጠመውም ማለት አይደለም:: ምክንያቱም መቶ በመቶ የሕትመት መሣሪያዎችንና ከ85 በመቶ በላይ የሕትመት ግብዓቶችን ከውጭ አገር በማስገባት የሚጠቀም በመሆኑ በተለያዩ ወቅቶች የውጭ ምንዛሪ እጥረትና የማጓጓዣ ችግሮች ያጋጥሙታል:: ችግሮቹን በራሱ መፍትሔ ፈልጎና አቻችሎ ደንበኞቹን ለማስተናገድ ምንግዜም ደንበኞቻችን ንጉሦቻችን ናቸው የሚለው መርህን በመጠቀም አገልግሎት ይሰጣል:: በሚያጋጥመውም ሁኔታ ላይ በጋራ በመወያየት መንቀሳቀሱ የመልካም አስተዳደርና የግልጽነት አሠራር መሆኑን በማመን ይጠቀምበታል::

ይህም የተለመውን ራዕይ ለማሳካት የሚያደርገው ጉዞ ነው:: ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ለደንበኞቹ የሚያደርገው መልካም ተግባር በቀላል የሚገለጽ ባለመሆኑ ከዓመት ዓመት ከፍተኛ ዕድገት እያስመዘገበ ያለ ማተሚያ ድርጅት ነው::

የሚዲያ ኮሙዩኒኬሽንስ ሴንተርም ይህን በመረዳት ለዚህ ያበቃኝ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ነው ማለቱ የተሻለ ይሆናል::

(ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት)

የዶክተሩ ማብራሪያ እንዲህ ይስተካከልበመጀመሪያ ደረጃውን ለጠበቀ የጋዜጣ አቀራረባችሁ

ያለኝን ምስጋና ለመግለጽ እወዳለሁ:: ጥር 26 ቀን 2005 ዓ.ም. በታተመው የሪፖርተር ጋዜጣ በቆይታ አምዳችሁ ከዶክተር አደም ካሴ አበበ ጋር ያደረጋችሁትን ቃለ መጠይቅ አንብቤአለሁ:: የቃለ መጠይቁ ይዘትና የዶክተሩ ማብራሪያ ጥሩ ሆኖ እያለ ባቀረባችሁት አንድ መሠረታዊ ጥያቄ ላይ ግን መስተካከል ያለበት ጉዳይ ያለ ስለመሰለኝ፣ አስተያየቴን ከማስረጃ ጋር አያይዤ የላክሁላችሁ ስለሆነ ቢታረም የሚል አስተያየት አለኝ::

ሕጎች በነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትመው መውጣታቸው የሚጠበቅ ሆኖ እያለ፣ በነጋሪት ጋዜጣ ሳይታተሙ ሥራ ላይ እየዋሉ ያሉ መመርያዎችና ደንቦች ስለመኖራቸው በመጥቀስ ይህ ከሕግ የበላይነት ጋር እንዴት እንደሚታይ ላቀረባችሁት ጥያቄ ዶክተሩ ሲመልሱ፣ ማንኛውም ሕግ በነጋሪት ጋዜጣ መውጣት አለበት የሚል ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌ የለም ብለው መልስ ሰጥተው ነበር::

ነገር ግን የፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 3/1987 አንቀጽ 2 ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ “ማናቸውም የፌዴራል መንግሥት ሕግ የሚወጣው በፌዴራሉ ነጋሪት ጋዜጣ ይሆናል፤” ብሎ ሲደነግግ፣ አንቀጽ 2 ንዑስ አንቀጽ 3 ላይ ደግሞ “ማናቸውም የፌዴራል ወይም የክልል ሕግ አውጪ፣ አስፈጻሚና ተርጓሚ እንዲሁም ማንኛውም የተፈጥሮ ሰው ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ የሚወጣ ሕግን የመቀበል ግዴታ ይኖርበታል፤” በማለት በነጋሪት ጋዜጣ ለሚወጡ ሕጎች ተፈጻሚነት ትልቅ የሕግ መሠረት ይሰጠዋል::

ስለዚህ የፌዴራል መንግሥትን ሕግ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ የመውጣት አስገዳጅነት ከዚህ አንፃር ታይቶ ቢስተካከል በማለት የፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 3/1987ን አያይዤ የላክሁላችሁ መሆኑን እየገለጽኩ፣ እናንተም በጥሩ የጋዜጠኛ ሥነ ምግባር፣ ምሁራንም በተለመደው የአገር ፍቅር ስሜት አገራችንን በጋራ ለመገንባት እንረባረብ እላለሁ:: አመሰግናለሁ::

(አወቀ አስፋው፣ ከአዲስ አበባ )

እዚህ የደረስኩት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ባሳተምኳቸው ሕትመቶቼ ነው ማለት አይሻልም?

‹‹ጅሃዳዊ ሐረካት››... ከክፍል-1 ገጽ 7 የዞረ

እየተጣሰ ነው ብለዋል:: ፊልሙ ፍርድ ከተሰጠ በኋላ ቢሆን ታማኝነቱ ከፍተኛ ይሆን እንደነበርም ይናገራሉ:: እንዲሁም ደግሞ ፊልሙ አሁን ካለው የሙስሊሞች ጥያቄ ጋር ቀጥታ ግንኙነት እንደሌለው ምልከታቸውን ገልጸዋል::

በተጨማሪም ይተላለፍ ከተባለ እንኳን ተጠርጣሪዎቹ በቀጥታ በአንደበታቸው ከሚናገሩት ውጪ፣ ምንም ግንኙነት የሌለው የሆሊውድና ሌሎች ቪዲዮዎች ተቀናብረው መቅረባቸው ጉዳዩን የበለጠ ለማግዘፍ እንደሆነ ያምናሉ::

ጉዳዩን አስመልክተን ጥያቄ ያቀርብንላቸው የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሽመልስ ከማል ግን፣ የሽብር ተግባር አደገኛና በሕዝብ ላይ የሚያስከትለው ጉዳትም ከፍተኛ በመሆኑ መንግሥት ምን እያደረገ እንደሆነ የማሳወቅ ግዴታ አለበት ይላሉ:: በዘጋቢ ፊልሙ የቀረበው ጉዳይ ገና በፍርድ ቤት ያልተያዘ መሆኑንም ይናገራሉ::

አንዳንድ በሌላ የሽብር ተግባር የተከሰሱ ተጠርጣሪዎች ያሉበት መሆኑን ግን ተናግረዋል:: የፀጥታ ኃይሎች ተከታትለው ገና ከመፈጸሙ በፊት በማክሸፍ በቁጥጥር ሥር የዋለ ሴራ መሆኑን ገልጸው አንድም ሕዝቡ እንዲያውቅ፣ ሁለትም ከዚህ ጋር በተያያዘ ሕዝቡ ለፀጥታ ኃይሎች ተባባሪ ሆኖ በዚህ ተግባር ላይ የተሰማሩ ሰዎች ካሉ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት እንዲያደርግ ማስጠንቀቂያ ነው ይላሉ:: ያለ ሕዝብ ትብብር ውጤታማ መሆን አይቻልም በማለት:: ጉዳዩ ግልጽ የሆነ ማስረጃ የተያዘበት መሆኑን ተናግረው፣ በማንም የፍርድ ቤት አካል ላይ ተፅዕኖ ለመፍጠር መንግሥት ዓላማ እንደሌለውም አስረድተዋል::

ተያያዥነት የሌላቸው ጉዳዮች በፊልሙ መካተታቸውን በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ በማሊና በናይጄሪያ እየሆነ ያለው በኢትዮጵያ የማይሆንበት ምክንያት የለም ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል:: በቁጥጥር ሥር ካልዋለ ወደዚያ ማምራቱ አይቀርም ነበር በማለት ‹‹ማስጠንቀቂያ ነው፤›› ብለዋል::

በኢጋድ የፀረ ሽብርተኝነት አቅም ግንባታ ኃላፊ ኮማንደር አበበ ሙሉነህ፣ እንዲህ ዓይነት ጥቃት የአልቃይዳ አዲሱ ስትራቴጂ መሆኑን ይናገራሉ:: ቀደም ሲል እንዲህ ዓይነት የሽብርተኝነት መናኸርያ የነበሩት አፍጋኒስታን፣ ኢራንና ሱዳን የነበሩ መሆናቸውን ጠቁመው፣ አሁን በግብፅ የሙስሊም ወንድማማቾች ወደ ሥልጣን መምጣት በምሥራቅ አፍሪካ የሽብርተኝነት ገጽታ ሊቀየር እንደሚችልም ያስረዳሉ:: ተጠርጣሪዎቹ

ከአልሸባብና ከሌሎች የአልቃይዳ መሪዎች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው መሆኑን በመጠቆም፣ በሌሎች አገሮች የሚታዩ ጥቃቶች በኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይፈጸሙ ከፍተኛ ሥጋት እንዳለ ያምናሉ::

ጅሃዳዊ ሐረካት - ልብ ወለድ ወይስ እውነት?

ፌስቡክን ጨምሮ በተለያዩ ማኅበራዊ ድረ ገጾች በርዕሰ ጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ክርክር እየተደረገ ሲሆን፣ ‹‹መንግሥት የፈበረከው ውሸት ነው›› ከሚለው ጀምሮ የተጠርጣሪው ቡድን ዓላማ ነው ከሚባለው፣ ‹‹በኢትዮጵያ እስላማዊ መንግሥት ማቋቋም›› ምን ክፋት አለው እስከማለት የደረሱ አስተያየቶች እየተሰጡ ነው:: በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ መሆናቸውን በግልጽ አስቀምጧል:: ይህንን አንስተው ለሚከራከሩም ቀደም ሲል ኢትዮጵያ ውስጥ ክርስቲያናዊ መንግሥት ለዘመናት አልነበረም ወይ የሚል ምላሽ የሚሰጡ አሉ:: ‹‹አንዱ ስህተት በሌላ ስህተት አይተስካከልም›› በሚል ሐሳባቸውን የሚያቀርቡ አስተያየት ሰጪዎች ቢበዙም፣ ‹‹የሕዝቡ ፈቃድ ከሆነ እስላማዊ መንግሥት በሰላማዊ መንገድ መመሥረት ምን ክፋት አለው?›› የሚሉ አስተያየት ሰጪዎችም ይደመጣሉ::

በድረ ገጾችም ሆነ በሕዝቡ ውስጥ ተጠርጣሪዎች የፍርድ ውሳኔ ከማግኘታቸው በፊት በሚዲያ መቅረቡ አግባብነት የለውም የሚሉ በርካታ አስተያየቶች ይሰጣሉ:: ፊልሙን የሙስሊሙን ማኅበረሰብ ለአንድ ዓመት የዘለቀ ተቃውሞ የተቀላቀለበት ጥያቄ ለማክሸፍ መንግሥት የፈበረከው ነው የሚሉም አልታጡም::

ጋዜጠኛዋ እንዳለችው፣ በአብዛኛው ዘጋቢ ፊልሙን የሚያጥላላና የሚያጣጥል የኅብረተሰብ ክፍል በመንግሥት ላይ ያለውን የፖለቲካ ጥላቻና ተቃውሞ መሠረት ያደረገ ይመስላል:: በኢቴቪ በመተላለፉ ብቻ እውነት ነው ብለው የማይቀበሉ ሰዎችም አሉ:: በመንግሥት ላይ ተቃውሞ ማሰማት የሚፈልግ የኅብረተሰብ ክፍል የሙስሊሙ ማኅበረሰብ አመፅ እንዲቀጣጠልም ፍላጎት ያለው ይመስላል፤ ተቃውሞውን በሌላ አቅጣጫ ለመግለጽ:: መንግሥት ደግሞ እየታዩ ያሉ የሽብር እንቅስቃሴዎች በአጭሩ ካልተቀጩ መዘዙ ከፍተኛ በመሆኑ ሕዝቡን ማስጠንቀቅ አለብኝ ይላል::

Page 22: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 22 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ማስታወቂያ

INVITATION FOR SALE OF VEHICLE

The Ethiopia-Canada Cooperation Office intends to sell by sealed bid the following vehicles:

1) Brand : Toyota CorollaModel : EE110L-AEMDS

Year of Manufacture : 1999Chassis Number : EE110-3014181

Engine Number : 2E-3171012 Current plate number : 12-005 Color : White Fuel : Benzene Present kilometer reading: 113176

2) Brand : Toyota CorollaModel : EE105L-AWMDS

Chassis Number : EE105-0004157 Engine Number : 2E-2784402 Current plate number : 12-006 Color : White Fuel : Benzene Present kilometer reading: 136120

The vehicles will be sold “as is/where is” basis. ECCO provides no warranty as to condition at the time of sale or thereafter. The vehicles are registered as “Duty Free” and the successful bidder will be responsible for payment of any duty or tax that applies to the sale.

Interested party may view the vehicle at the ECCO office from February 11, 2013 to February 19, 2013 from 8:30am to 4:30pm on Monday to Thursday and from 8:30am to 12:00pm on Friday. Standard bid forms are available at ECCO Office during viewing. Bid must be sealed in a sealed envelope marked as “Bid for Purchase of Motor Vehicle by stating the Plate Numbers” and must be returned to ECCO before Tuesday February 19, 2013 at 4:00pm.

The Bid must accompanied with CPO amount of Ethiopian Birr 5,000.00 (Five thousand) prepared in the name of Ethiopia Canada Cooperation Office (ECCO) for each vehicle. The successful bidder will be expected to make full payment of the bid amount through CPO/CASH within 72 hours of notification of the acceptance of bid. Failure to make payment in the time-frame may result in cancellation of the sale to that bidder.

ECCO reserves the right to reject any or all bids for any reason

whatsoever. ECCO will not be held responsible for bid received after

the closing nor will such bid be considered. CPO will be released for

unsuccessful bidders with in three weeks.

Our office is located in Lafto Sub-City, Kebele 04, House No. 161/01,

Old Airport Area, and the first turn to the left after Zambia Embassy. Tel.

0113 71 56 00.

ለሐበሻ ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበር ባለ አክሲዮኖች

ሐበሻ ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበር የባለ አክሲዮኖች 3ኛ መደበኛና 2ኛ ድንገተኛ ጠቅላላ

ጉባኤ ጥር 19 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲዮም ትንሸዋ አትሌቲክስ ሜዳ

በተካሄደበት ዕለት ለሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት የሚያገለግሉ የዲሬክተሮች ቦርድ አባላት

ምርጫ ማከናወኑ ይታወቃል፡፡ ከብዛቱ አንፃር በዕለቱ እንዲያሳውቅ መወሰኑም ይታወሳል፡

፡ በዚሁ መሠረት የዕለቱ የዲሬክተሮች ቦርድ ምርጫ ውጤት ከዚህ እንደሚከተለው

መሆኑን አስመራጭ ኮሚቴው ይገልፃል፡፡

ሀ/ ከነባሮቹ 12 የቦርድ አባላት በዕለቱ ለምርጫ ቀርበው የነበሩት 10 ተወዳዳሪዎች ከዚህ

በታች በየስማቸው አንፃር በቅደም ተከተል የተመለከተውን ድምጽ አግኝተዋል፡፡

1. ኢ/ር ግዛው ተ/ማሪያም …………….. 407,257

2. ኢ/ር መስፍን አቢ…………………… 399,109

3. አቶ እስክንድር ደስታ ………………. 388,054

4. አቶ ታምሩ ወንድማገኘሁ ………….. 374,324

5. አቶ ተረፈ መንገሻ ………………….. 366,835

6. ህብረት ኢንሹራንስ ኩባንያ…………... 39,788

7. ፕ/ር አበበ ድንቁ …………………….. 34,397

8. የተባበሩት ብሔራዊ ፔትሮሊየም…….. 23,087

9. ካፒቴን አመሐ ቀጸላ ………………… 13,096

10. አቶ ፀደቀ ይሁኔ ……………………... 8,403

ለ/ ከነባሮቹ ውጭ ለምርጫ የቀረቡት 6 አዳዲስ ዕጩዎችም ከዚህ በታች በየስማቸው

አንጻር የተመለከተውን ድምጽ ማግኘታቸው ተረጋግጧል፡፡

1. ኢንዱስትሪያል ደቨሎፐመንት ኩባኒያ (አይ ዲ ሲ) …………. 405,012

2. አምብሪዚዮ ኢንቨስትመንት 488 (ppc)………………………. 404,712

3. አምብሪዚዮ ኢንቨስትመንት 488 (ppc)………………………. 398,940

4. ህብረት ባንክ አክሲዮን ማህበር ………………………………. 19,864

5. ሐበሻ የኮንስትራክሽን ማቴሪያልና ልማት አ/ማ (ሐኮማል)….... 8,892

6. አቶ አበራ በጅጋ ……………………………………………….. 8,212

ሐ/ በተሻሻለው የኩባንያው መተዳደሪያ ደንብና የመመስረቻ ጽሑፍ እና የዕለቱም ጠቅላላ

ጉባኤ ውሳኔ መሰረት ለምርጫ ከቀረቡት 10 ነባር የቦርድ አባላት መካከል 5ቱ፣ እንደዚሁም

አዳዲስ ከቀረቡት 6 ተወዳዳሪዎች 4ቱ በጠቅላላው 9ኙ ባገኙት ድምጽ ቅደም ተከተል

መሠረት የኩባንያው የዲሬክተሮች ቦርድ አባላት ሆነው ተመርጠዋል፡፡ ዝርዝራቸውም

ከዚህ በታች ተመልክቶአል፡፡

1. ኢ/ር ግዛው ተ/ማሪያም

2. ኢ/ር መስፍን አቢ

3. አቶ እስክንድር ደስታ

4. አቶ ታምሩ ወንድማገኘሁ

5. አቶ ተረፈ መንገሻ

6. ኢንዱስትሪያል ደቨሎፐመንት ኩባኒያ (አይ ዲ ሲ)

7. አምብሪዚዮ ኢንቨስትመንት 488 (ppc)

8. አምብሪዚዮ ኢንቨስትመንት 488 (ppc)

9. ህብረት ባንክ አክሲዮን ማህበር

አስመራጭ ኮሚቴው

Page 23: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 23 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታወቂያማስታወቂያ

Invitation to Bid for: - “The purchase of Medical Equipments, Tools and Supplies”

The International Training and Education Center for Health (I-TECH) is a center in the University of Washington’s Department of Global Health and has offices throughout Africa, Asia, and the Caribbean. I-TECH’s 600 worldwide staff work in partnership with local ministries of health, universities, non-governmental organizations (NGOs), medical facilities, and other organizations to support the development of a skilled health work force and well-organized national health delivery systems. I-TECH Ethiopia has the largest operations working in three regions of Ethiopia – Afar, Amhara, and Tigray. I-TECH Ethiopia’s primary activities are health system strengthening, Operations research, evaluation and Prevention, care, and treatment of infectious diseases.

I-TECH ETHIOPIA country office would like to purchase Medical Equipments, Tools and Supplies & eligible bidders are invited to participate in this bid by collecting bid document from office no 107 located at the address mentioned below during working hours.

Bidders should submit the following documents along with their offers and shall agree to work under the conditions listed below. These documents are requirements for preliminary examination/ verification of bid compliance.

• Renewed or valid business licences • VAT registration certificate• Certificate of tax identification number• Bid bond amounting Birr 20,000.00• Ability to deliver the items to the main store located in Addis

Ababa using its own transportations• To accept a 30 days credit payment condition

I-TECH EthiopiaIn front of Harmony hotel, next to ABC car Rent

Bole S/C k. 03/05Tel. 25116639718/19/21/22

Fax: 25116639800P.O. Box 2695/1250

Addis Ababa, Ethiopia,

Bid, both technical and financial but separately prepared, must be put in wax – sealed envelope, clearly specifying for “Bid for Medical Equipments, Tools and Supplies” and submit to the office located in the address stated above and put it in the bid box provided for this purpose, from February11 but before 5:00PM February 19, 2013.

I-TECH reserves the right to accept or reject the whole or part of any or all bids

Invitation to Bid for: - “Documentary Film Production”

The International Training and Education Center for Health (I-TECH) is a

center in the University of Washington’s Department of Global Health

and has offices throughout Africa, Asia, and the Caribbean. I-TECH’s

600 worldwide staff work in partnership with local ministries of health,

universities, non-governmental organizations (NGOs), medical facilities,

and other organizations to support the development of a skilled health

work force and well-organized national health delivery systems. I-TECH

Ethiopia has the largest operations working in three regions of Ethiopia

– Afar, Amhara, and Tigray. I-TECH Ethiopia’s primary activities are health

system strengthening, Operations research, evaluation and Prevention,

care, and treatment of infectious diseases.

I-TECH ETHIOPIA country office would like to have consulting firms for

the production of Documentary Film & eligible bidders are invited to

participate in this bid by collecting bid document from office no 107

located at the address mentioned below during working hours.

Bidders should submit the following documents along with their offers

and shall agree to work under the conditions listed below. These

documents are requirements for preliminary examination/ verification

of bid compliance.

• Renewed or valid business licences

• VAT registration certificate

• Certificate of tax identification number

• Bid bond amounting Birr 20,000.00

• Ability to accomplish the work within a month

• To accept a 30 days credit payment condition

I-TECH Ethiopia

In front of Harmony hotel, next to ABC car Rent

Bole S/C k. 03/05

Tel. 25116639718/19/21/22

Fax: 25116639800

P.O. Box 2695/1250

Addis Ababa, Ethiopia,

Bid, both technical and financial but separately prepared, must be put

in wax – sealed envelope, clearly specifying for “Documentary Film Production” and submit to the office located in the address stated above

and put it in the bid box provided for this purpose, from February11 but

before 5:00PM February 19, 2013.

I-TECH reserves the right to accept or reject the whole or part of any

or all bids

Page 24: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 24 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ማስታወቂያ

Page 25: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 25 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታወቂያ

Page 26: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 26 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ማስታ

ወቂያ

በኢዮብ ተመስገን በቅርቡ ክቡር አምባሳደር ዘውዴ ረታ ‹‹የቀዳማዊ

ኃይለ ሥላሴ መንግሥት›› በሚል ርዕስ ስለ አባባ ጃንሆይ መንግሥት ያስረዱበትን መጽሐፍ ለንባብ አብቅተዋል:: በዚህ መጽሐፍ ስለመንበረ ጴጥሮስና ስለርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፒዮስ 11ኛ የሰጡትን ምስክርነት በመቃወም ግሎባል አልያንስ በማለት ራሱን የሚጠራውን አውቅላቹኋለሁ ባይን በመወከል፣ አቶ ኪዳኔ ዓለማየሁ ኅዳር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. በወጣው ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ስለመጽሐፉ ያቀረቡትን ትችት አንብቤአለሁ:: የፋሽስት ጣሊያን መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ የፈጸመውን መጠን የለሽ ጥቃት ቤተ ክርስቲያናችን አብራ ያደረገች አስመስለው አቅርበዋል:: ይህንን ድብቅ የሃይማኖት ተልዕኮ ለመወጣት ሲሞክሩ እያየሁ ማለፍ ባለመቻሌ ምላሽ ለመስጠት ሳስብ፣ ይህንን በኢትዮጵያውያን ካቶሊኮች ላይ ያነጣጠረ ዘመቻ መመከት የምንችልና እንዲሁም እኛ ኢትዮጵያውያን ካቶሊኮች ለማንኛውም የመንበረ ጴጥሮስ (Holy See) ጥያቄዎች መልስ መሆን እንደምንችል አንባቢያን ልታውቁልኝ ይገባል::

ይህ ቡድን ዘመቻውን ከጀመረ ዓመታትን ያስቆጠረ ቢሆንም፣ እስካሁን ተቀባይነት ያላገኙ 3,500 የማይሞሉ ፊርማዎችን በማሰባሰብ ኢትዮጵያውያን ካቶሊኮችን በነገርና በቃላት ሲወጋን ከርሟል:: እኔም በትዕግስት ፍቅርን ለመስጠት ዝምታን መረጥኩ:: ዛሬ ግን ይህንን በትዕግስት ለመታገስ የሚያቅት ደረጃ አድርሶኛል:: ምክንያቱም ‹‹ያየ ሳያወራ የሰማ አላስወራ አለ›› እንደተባለው በቦታው የነበሩት ክቡር አምባሳደሩ ያዩትን ሲናገሩ በቦታው ያልነበረና የሰማው አላስወራ ማለቱ የሚገርም ነው::

‹‹የሞኝ ለቅሶ መልሶ መላልሶ›› እንደሚባለው ይህ ቡድን አዘውትሮ የያዘው መፈክር መንበረ ጴጥሮስ (Holy See) ይቅርታ ትጠይቀን የሚል ሲሆን፣ አንባቢያን ልትረዱት የሚገባው ቤተ ክርስቲያን ሁልጊዜ የሚታየው የክርስቶስ አካል እንደመሆኗ መጠንና ሚስጥራዊ የክርስቶስ አካል (Mystical Body of Christ)፣ እንዲሁም በክርስቶስ ደም የታወጀች በመሆኗ ለይቅርታ ጊዜ አትሰጥም:: ብፁዕ ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ በሚሊኒየሙ ወቅት ብቻ ከመቶ ጊዜ በላይ ይቅርታ ጠይቀዋል:: ነገር ግን ይህ ቡድን የራሱ ድብቅ ዓላማ ያለው በመሆኑ የሚያቀርባቸው ምክንያቶችና ፎቶግራፎች እጅግ የሚያሳዝኑ፣ የሚያስተዛዝቡና አውቅላቹኋለሁ ባይ መሆኑን የሚገልጹ ናቸው::

በዚህ በተያዘው የግሎባላይዜሽን ዘመን አንድ የመለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ የሞባይል

ተ ሟ ገ ት

ስልክ በእጁ መያዙ የታወቀ ነው:: በዚህ ሞባይል ስልክ ኢንተርኔት መጠቀሙም አይቀሬ ነው:: ታዲያ በጎግል ድረ ገጽ መፈለጊያ ገብቶ ‹‹ላተራን ትሪቲ›› (Lateran Treaty) ብሎ ቢጽፍ መልሱን በቀላሉ ሊያገኘው የሚችል ሲሆን፣ ይህንን ፀሐይ የሞቀውንና አገር የሚያውቀውን ስምምነት ይህ አውቅላቹኋለሁ ባይ ድርጅት ከእኛ ኢትዮጵያውያን የተደበቀ ነገር አድርጎት፣ ራሱም ደብቆን ሊዋሸን መሞከሩ ያሳዝናል ደግሞም ያስተዛዝባል:: እንዲሁም አሳፋሪ ድርጊት ነው::

እውነቱ ግን የ‹‹ላተራን ትሪቲ›› በመባል የሚታወቀው ስምምነት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳትና የጣሊያን መንግሥት መንበረ ጴጥሮስን ነፃ የሆነች የክርስቲያኖች መንበር (ecclesiastic state) ለማድረግ ቀደም ብሎ ለምሳሌ እ.ኤ.አ በ1870 ይህ ጥያቄ ተነስቶ ሳይፈጸም የቀረ ሲሆን፣ እ.ኤ.አ በ1929 ይህ ስምምነት ተደረገ:: በንጉሥ ቪክቶር አማኑኤል ሣልሳዊ ተወክሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞሶሎኒ፣ እንዲሁም ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳትን ወክለው ከካርዲናል ጋስፓሪ ጋር

የተደረገ ስምምነት ከመሆኑም በላይ፣ ዛሬ ቫቲካን ወይም መንበረ ጴጥሮስ በመባል በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት የምትመራ ሉዓላዊ ክርስቲያናዊ (ካቶሊካዊ) አገር ስትሆን ይህ ማለት ቫቲካንና ሮም ተለያዩ ማለት ነው:: እውነቱ ይህ ሆኖ ሳለ ኢትዮጵያን ለመውረር የተደረገ ስምምነት አስመስሎ ማቅረቡ ምን ይባላል? ወንጀል ወይስ ኃጢያት? በሌላ በኩል ይህ ራሱን ግሎባል አልያንስ እያለ የሚጠራውና በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያንና በኢትዮጵያውያን ካቶሊኮች ላይ ያነጣጠረ ልዩ ተልዕኮ ያነገበው ድርጅት የሚያወራውና የሚያቀርባቸው ምስሎች ‹‹ፍየል ወዲያ ቅዝምዝም ወዲህ›› እንደተባለው ነው::

አንባቢያን እንድትመለከቱት የምፈልገው ነጥብ ይህ ድርጅት በቃላት ‹‹የሞሶሎኒና የቫቲካን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፒዮስ 11 ተፈራረሙ›› ብሎ ሲያበቃ፣ የሚያሳየን ፎቶ ደግሞ ካርዲናል ጋስፓሪኖንና ሞሶሎኒን ነው:: ይህ ለሐሰት መፍጠሪያው በር የከፈተለት ሲሆን፣ ከዚህ ሌላ አሉ አሉ በማለት የሚያቀርበው ካልሆነ በቀር ምንም

ቫቲካንን ከፋሽስት ወረራ ጋር በማያያዝ ነጋሪት መጎሰም ይብቃ

ማስረጃ የሌለው ዕርቃነ ቢስ ነው:: በሁለተኛው ደግሞ በቃላት ‹‹ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ጦር ሲባርኩ›› ይለንና ውሸት ለመፍጠር የተጠቀመው ሌላ ቄስ (ካህን) ያውም በእጃቸው ምን እንደያዙ የማያሳይ ነገር ግን መድፍ አጠገባቸው ለምን ምክንያት እንደቆመ የማይገልጽ ምስል ያቀርብልናል:: እስቲ አንባቢያን ይህንን ምስል በዙም (Zoom In) አድርጋችሁ ተመልከቱት:: ስለእውነት ለመናገር የመጨረሻ አሳፋሪ ድርጊት እንደዚህ አይቼ አላውቅም:: ካህኑ በእጃቸው ምን እንደያዙ እንኳን ምስሉ አያሳይም::

እኔን ያሳፈረኝ ይህ ድርጅት በእኛ በኢትዮጵያውያን ስም እንደዚህ ዓይነት አሳፋሪ ነገር ወይም ምክንያት ማቅረቡ ነው:: ጦር ባረኩ ከተባለ ጦሩስ የታለ? ሊዘምት የተዘጋጀ ጦር ተሠልፎ መኖር አይገባውም? አንባቢያን በእኛ በካቶሊካውያን ባህል በብዙ አገሮች ለሁሉም ነገር መሪ ካህን (Chaplain) ይኖራል:: ለምሳሌ የሕግ ታራሚዮች መሪ ካህን፣ የሕሙማን መሪ ካህን (በሆስፒታል)፣ የወታደሮች መሪ ካህን ይኖራል:: ወታደር ሁልጊዜ ወንጌል ይሰበካል፣ ቅዳሴ ያስቀድሳል፣ ንሰሐ ይገባል:: ይህ ሁሉ በካምፕ ውስጥ ካህን ቤት ተሰጥቶት አብሮ እየኖረ በቻፕል ውስጥ ይህንን መንፈሳዊ አገልግሎት ይሰጣል:: ማረሚያ ቤቶች በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ማኅበራዊ አስተምህሮ ታራሚዎች ካለባቸው መጥፎ ልማድ የሚድኑበት፣ ባህሪያቸውን የሚለውጡበትና የሚቀየሩበት በመሆኑ በማረሚያ ቤቶችም ለታራሚዮች ቅዳሴ፣ ንሰሐና ትምህርት ያስፈልጋል:: ይህ ሁሉ ታራሚዎችን የሚለውጡና የሚያስተምሩ በመሆናቸው ነው:: ሌላው በሆስፒታልም እንዲሁ ንሰሐና የተለያዩ ሚስጢራትን ነፍሳቸው ሳትለይ ይቀበላሉ:: ይህ ነው የካቶሊካውያንን ባህል ለየት የሚያደርገውና ካቶሊክም ያሰኘን::

በኢትዮጵያም ውስጥ በአባባ ጃንሆይ ጊዜ ለወታደሩ በየሻለቃው አንዳንድ ቄስ እንደነበርና የሃይማኖት አገልግሎት ይሰጥ እንደነበር ጠይቄ ለመረዳት ሞክሬያለሁ:: ግሎባል አልያንስም ይህንን አንድ ካህን አገልግሎት እየሰጡ ባሉበት ቦታ የተነሳ ፎቶግራፍ ይዞ ይዋሸናል:: እንዲያውም የእኚህ ካህን እጅ የሚያሳየን ጽዋ እንጂ መስቀል አለመሆኑን አንባብያን ልትመለከቱት ትችላላችሁ:: ይህ ድርጅት ስም እያጠፋ እንጂ በእውነት ርዕሰ ሊቃነ

የሐራጅ ማስታወቂያሕብረት ባንክ አ.ማ. ከዚህ በታች በተመለከተው ቅርንጫፎቹ በኩል ለሰጠው ብድር በመያዣነት የያዛቸውን ንብረቶች በአዋጅ ቁጥር 97/90 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በግልጽ ሐራጅ (ጨረታ) አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡

ተ.ቁ አበዳሪ

ቅርንጫፍ

የተበዳሪው ስም የአስያዥ ስም ቤቱ የሚገኝበት አድራሻና የቦታ ስፋት

የይዞታ ማረጋገጫ ቁጥር የሐራጅ መነሻ ዋጋ

ሐራጁ የሚካሄድበት ቀንና ሰዓት

1 አዳማ አቶ ታደለ አደሬ አቶ ታደለ አደሬ አዳማ ከተማ ቀበሌ 04 የቤ.ቁ. አዲስ የቦታ ስፋት 1035 (ለሁለተኛ ሐራጅ የቀረበ)

737885/2002

2,545,048.70መጋቢት 23 ቀን 2005 ዓ.ም

ጠዋት

4፡00 - 6፡00 ሰዓት

2 ተ/ኃይማኖት ኩንፈየኩን ኀ/የተ/የግ/ማ

አቶ ሰይድ ጀማል አ.አ ቂርቆስ ክ/ከተማ የቀድሞው ቀበሌ 35 የቤ.ቁ 272 የቦታው

ስፋት 447 ካ.ሜ

(ለሁለተኛ ሐራጅ የቀረበ)

CKS02/102/614/239

22/00

2,279,510.59 መጋቢት 24 ቀን 2005 ዓ.ም ከጠዋቱ

4፡00 - 6፡00 ሰዓት

3 ተ/ኃይማኖት ኩንፈየኩን ኀ/የተ/የግ/ማ

አቶ አብዱ ጀማል አ.አ ቂርቆስ ክ/ከተማ ቀበሌ 02/03 የቤ.ቁ 313 የቦታው

ስፋት 278 ካ.ሜ

(ለሁለተኛ ሐራጅ የቀረበ)

CKS03/80/4249/211

77/01 1,448,227.61መጋቢት 25 ቀን 2005 ዓ.ም

ጠዋት

8፡00 - 10፡00 ሰዓት

4 ቦሌ መድኣኒአለU

የገነት ሓ/የተ/የግ/ማህበር

አቶ ፋሲል ዘውዴ ድንቁ

አ.አ አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ቀበሌ 10 የቤት ቁጥር አዲስ/ማሜ ብረታብረት እንዱስትሪ

ጀርባ የሊዝ ይዞታድርጅት 2780 ካ.ሜ

(ለሁለተኛ ሐራጅ የቀረበ)

ድ3079/96 12,945,693 መጋቢት 26 ቀን 2005 ዓ.ም 8፡00 - 10፡00 ሰዓት

የሐራጅ ደንቦች፣1.

2. ተጫራቾች የሐራጁን መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲ.ፒ.ኦ.) ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፡፡ አሸናፊ የሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በአሥራ አምስት (15) ቀናት ውስጥ አጠቃልሎ ካልከፈለ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ሐራጁ ይሠረዛል፡፡ በተጨማሪም ንብረቱ ድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚታየው የዋጋ ልዩነት ይጠየቃል፡፡

3. በሐራጅ ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች፣ ተበዳሪዎችና አስያዦች ብቻ ናቸው::4. የሐራጅ ሽያጩ የሚካሄደው የመያዣው ንብረት በሚገኝበት ቦታ ላይ ነው፡፡ 5. የተጫራቾች ምዝገባ ከሐራጁ መዝጊያ ሰዓት ሰላሳ ደቂቃ በፊት ይጠናቀቃል፡፡ በሐራጁ የመጨረሻ ሰላሳ ደቂቃዎች የተጫራች ምዝገባ አይካሄድም፡፡6. ለሐራጅ የቀረበውን ንብረት ለመጎብኘት የሚፈልጉ ከአበዳሪው ቅርንጫፍ ወይም ከሕግ አገልግሎት ጋር አስቀድሞ ቀጠሮ በመያዝ መጎብኘት ይችላሉ፡፡ 7. ተጨማሪ እሴት ታክስ እና ሌሎች ገዥ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ታክስና ግብሮችን ገዢው/አሸናፊው ይከፍላል፡፡8. ማንኛውንም ከሊዝ ክፍያ ጋር በተያያዘ ለመንግስት ሊከፈል የሚገባውን ክፍያ የጨረታው አሸናፊ የሚከፍል ይሆናል፡፡9. ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-465-52-22 የውስጥ መሥመር 220 ወይም 011-466-65-93 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

Page 27: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 27 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1

ተ ሟ ገ ት

ጳጳሳት ጦር ባረኩ ካለም ለምን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሲባርኩ አያሳየንም? አለበለዚያ በፎቶግራፉ ላይ የሚታዩት ካህን ቢሆኑም ለምን ሙሉ ምስላቸው አይታይም? የሚባርከው ብቻ ሳይሆን የሚባረከው ጦርና ሠልፍ ለምን አልታየም? በዚያን ወቅት ፎቶ የለም እንዳይባል የላተራኑን ጉባዔ ፎቶ ለጥፏል:: ሌላው የሚገርመው ነገር ርዕሰ ለቃነ ጳጳሳት ፒዮስ 11ኛ የተወለዱት በሎምባርዲ ኢጣሊያ ሲሆን፣ ‹‹The Peace of Christ in the Kingdom of Christ›› (በክርስቶስ መንግሥት የክርስቶስ ሰላም) በሚባለው ቃል እንዲሁም የኢትዮጵያ ወዳጅ በመባል የሚታወቁ ሲሆን፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በተለያዩ አገሮች በኑንሲዎነት ያገለገሉ ናቸው:: ‹‹Pius’ pontificate soon witnessed the rise to power of Benito Mussolini, who signed (Feb. 11, 1929) with him the Lateran Treaty that allowed the existence of the independent Vatican City state, over which the pope ruled.›› በተጠቀሰው ዕለትና ዓ.ም. መንበረ ጴጥሮስን ከተረከቡ በኋላ ቀደምት ኢትዮጵያውያን በእንግድነት ወደ ቅድስት አገር (እስራኤል) ከተጓዙ በኋላ ቅድስት መንበርን (መንበረ ጴጥሮስ) ይሳለሙ ስለነበር ለእነሱ የሚሆን ቦታ ተሰጥቷቸው ነበር (1481 ዓ.ም.):: እዚያ ቦታ ላይ የአቢሲኒያው የቅዱስ እስቲፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶበታል::

ከዚያም የኢትዮጵያ ኮሌጅ ቀደም ብሎ እ.ኤ.አ በ1539 የተሠራ ሲሆን፣ አሁን ያለውን አዲሱን የኮሌጁን ሕንፃ አሠርተውልናል:: ይህ ቤተ ክርስቲያን ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት መኖሪያ ጋር የተያያዘ ነው:: እንዲሁም አቡነ ኪዳነ ማርያም ካሳ የተባሉትን ጳጳስ የቀቡልን በዚያው አዲሱ የኢትዮጵያ ኮሌጅ ሲመረቅ ነው:: እዚህ ላይ መንበረ ጴጥሮስ ሉዓላዊነቷን ስታረጋግጥ ማናቸውም ድርጅትና እንግዶች በሙሉ ከቫቲካን እንዲወጡ ሲደረግ፣ የኢትዮጵያ ኮሌጅ ግን ራሱን የቻለና የራሱ ታሪክ ያለው በመሆኑ ‹‹it is always good to have some black on white.›› (በነጭ ላይ ጥቁር መገኘቱ ሁልጊዜ ያምራል) በማለት የኢትዮጵያውያን ኮሌጅ በቦታው እንዲቆይ መደረጉን ለአንባቢያን ማሳወቅ ግድ ይላል:: ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በንባበ መለኮት፣ በፍልስፍናና በካናን ሎው የተለያዩ ዲግሪ ያላቸው ከመሆኑም በላይ፣ ስለአስተዳደጋቸውና ስለእሳቸው ብዙ ከተናገርን ማንነታቸው የገዘፈ አባት ስለሆኑ እንዲህ መባላቸው የባሰ ያሳዝናል:: ነገር ግን አንድ ነገር ልበላችሁ:: እኝህ ሰው (ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት) ጣሊያናዊ ናቸው:: የአገራቸው መንግሥት ፋሺዝምን እያራመደ የሰው አገር ልውረር ሲል እሳቸው ግን የጴጥሮስ ተተኪ ስለሆኑ፣ በምድራዊው መንግሥት ሳይሆን ለሰማዩ መንግሥት የተሾሙ በመሆናቸው ሞሶሎኒን አልተቀበሉትም:: በዛሬ ጊዜ ይህ ነገር አለ? በአገራችንስ አለ? እናንተስ ብትሆኑ? ያውም የእናንተ

ዓይነቱ በዚያ ቦታ ቢሆን ኖሮ ከሞሶሎኒ ባትብሱ ነው? እንደዚህማ ባይሆን ኖሮ ያልናችሁን በሰማችሁ ነበር::

ከሳሻችን ግሎባል አልያንስና ሌሎቹም ከሚያነሱት አንዱ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ናዚንም አልተቃወሙም ይሉናል:: እንግዲህ ፋሺዝም ይሁን ናዚዝም ለመከላከል ያልተደረገ ነገር አለ ለማለት ያስቸግራል:: ነገር ግን በእኛ ባህል መሠረት የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አራተኛውን ሐዋርያዊ መልዕክት (Encyclical Letter) ‹‹humani generis unitas›› (On the Unity of the Human Race) ፋሽስትንና ናዚን በመቃወም እንደተጻፈ ይታወቃል:: የሐዋርያዊ መልዕክት ምንድን ነው? ብትሉ ለእናንተ አንባብያን ከማስረዳት ይልቅ በመጽሐፍ ቅዱስ የሐዋርያዊ መልዕክትን እንደምታውቁ እርግጠኛ ነኝ:: ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ለጳጳሳትና ለዓለም አቀፏ ቤተ ክርስቲያን (Universal Church) ምዕመናን ስለቤተ ክርስቲያንና ስላለው ስለወቅቱ ሁኔታ የሚጽፉት (Encyclical Letter) መልዕክት ሲሆን፣ ሁሉም ተቀብሎ በሥራ ላይ ያውለዋል::

ይህንን ሁሉ አደረገች የምትሏት ቤተ ክርስቲያን የእናንተ ቤተ ክርስቲያን ብትሆን ኖሮ እርግጠኛ ነኝ ናዚም ሆነ ፋሺዝም ትክክለኛ ነው ብላችሁ እንደምትሞግቱን አልጠራጠርም ነበር:: ነገሩ አሁንም በእኛ ላይ የምታደርጉት ተግባር ከፋሺዝም ወይም ከናዚዝም በምን ይለያል? ይህችን በዓለም ያለች አንድ ቤተ ክርስቲያን ከፋሺስት ጋር ወገነች ካላችሁ ለመሆኑ ፋሺስት ምን ማለት እንደሆነ አውቃችኋል? ናዚስ? ለእናንተ ጠፍቷችሁ ነው ብዬ አይደለም:: ግን እኛን ከምን ጋር እንደምታነፃፅሩን ስለሚገባንና የእናንተን ማር ወለላ አድርጋችሁ በማየታችሁ የሃይማኖት ተልዕኮ እንዳነገባችሁ እናውቃለን ለማለት ነው:: ስለዚህ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ስለአይሁዳውያን (Anti Semitism) ‹‹spiritually, we are semities 6 Sep.1938›› (በመንፈስ እኛ ሴሜቲስት ነን) የሚለው አባባላቸው በቂ አይመስላችሁም? የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እናንተ ዛሬ እንደ አገራችሁ የምትቆጥሯትን ኢየሩሳሌምን ከባንዛንታይን ተከላክላ እዚህ ያደረሰቻት ማነችና? ኧረ ወዴት ወዴት ወገኔ እንዴት ተደርጎ ፀረ ሴሜቲዝምን (Anti-Semitism) ቤተ ክርስቲያን ትደግፋለች ትላላችሁ? ያውም ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያንን ደም የከፈለችበትን:: ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፒዮስ 11ኛ እ.ኤ.አ ጥቅምት 23 ቀን 1938 ለአባ ቬንቱሪ ሲናገሩ፣ ‹‹ጣሊያንያዊ በመሆኔ አፍሬያለሁ:: እባክዎትን ለሞሶሎኒ ንገሩልኝ እንደ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሳይሆን እንደ አንድ ጣሊያናዊ በራሴ አፍሬያለሁ:: የጣሊያን ሕዝብ እንደ በግ መንጋ ሆኗል:: የምፈራው ነገር የለም እናገራለሁ፤›› ሲሉ ተናግረዋል:: ቅዱስነታቸው በዚያ ዘመን ከነበረባቸው ጫና፣ የልብ ሕመምና አስም የአገራችን ጉዳይ ያስጨንቃቸው እንደነበርና ለኢትዮጵያውያንም እንዴት እንደለፉ የሚያመለክት ነው:: ኤሪክ ሉንደርም ስለተባለው ስዊድናዊ ጋዜጠኛም ብዙ ማለቱ አስፈላጊ አይደለም:: ስዊድናዊ ነው መባሉ ብቻ በቂ ነው:: ምክንያቱም ራሱም ቫቲካን ላይ

የሃይማኖት ጥያቄ ያለው ሃይማኖተኛ ስለሆነና እንዲሁም ሶሻሊስቶች በፋሺስቶች ግራ ተጋብተው የነበረበት ወቅት ስለነበር ነው::

ሌላው ሳናውቅ ፍርደ ገምድል ሆነን መፍረዳችን የሚገርም ነው:: ኅዳር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. በወጣው ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ጸሐፊው አቶ ኪዳኔ አለማየሁ እንዳሉት፣ ‹‹በተጨማሪ ማንም ሊገነዘበው የሚችለው ሀቅ በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ጳጳሶችና ካህናቱ ሌላ አገር ለማጥቃት የሚጓዝ ጦር ሲባርኩ ያለቫቲካን መሪ ፖፕ ፒዮስ 11ኛ ፈቃድ በግል ፍላጎታቸው ነበር ማለት የሚያስገርም ነው፤›› ያሉት ቢያስገርምዎትም፣ እኔን ደግሞ ባይገረሙ ነበር የሚገርመኝ:: ምክንያቱም ስለቤተ ክርስቲያን በተለይም ዓለም አቀፏ ቤተ ክርስቲያን (Universal Church) ያለዎት ዕውቀት ትንሽ በመሆኑ፣ ወይም ባለማወቅዎ ነው:: አለማወቅ ወንጀል ባይሆንም ተምሮ የማይቀየር ምን ሊባል እንደሚችል ለእርስዎ ትቼው፣ ዋናውን ቁም ነገር ልንገርዎትና ለመለወጥ ይሞክሩ::

የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት እንደ መንግሥት ሥልጣን ተዋረድ፣ እንደ ፖለቲካ ፓርቲና እንደ ሚሊተሪ እልቅና ሳይሆን ሁሉም በራሱ ዕውቀትና ችሎታ ታምኖበት የሚሰጠው አገልግሎት ነው:: ጠለቅ ያለ ማስረጃ በምሳሌ ላሳይዎት:: በአዲስ አበባ ለገሀር የሚገኘውን የመድኃኔዓለም ቁምስና (Parish) እንውሰድና የቁምስናው ቆሞስ (Parish Priest) ማለትም የቤተ ክርስቲያኑ ኃላፊ ሆነው የተመደቡት፣ እዚያ ቤተ ክርስቲያን የሚያደርጉትንና የሚሠሩትን ሥራ ለማኅበር አለቃ (Provincials) ወይም ለሀገረ ስብከቱ አቡን (ጰጳስ) ማሳወቅ አይጠበቅባቸውም:: አገረ ስብከቶችም ለምሳሌ የአዲግራት ወይም የሐረር ሀገረ ስብከት የሚያደርጉትን ለብፁዕ ሊቀ ጳጳሳችን ማሳወቅ ወይም መንገር ወይም ማስፈቀድ የለባቸውም:: መንበሩ የአቡናቱ በመሆኑ ኃላፊነቱ የእነሱ ነውና:: የተለያዩ ማኅበራትም (Congregation) እንደዚያው ናቸው:: ይህ ነው እንግዲህ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ፖለቲከኞቹ ያልፈጸሙት የፌዴራሊዝም ምንጭ ናት የሚያሰኛት::

እዚህ ላይ አቶ ኪዳኔ እንደሚሉን ገና ሌላም የባረክነው ጦር አለ ማለት ነውን? ‹‹ሌላ አገር ለማጥቃት የሚጓዝ ጦር ሲባርኩ›› ያሉን ወይስ ይህንኑ ነው? ወደ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ልመልሳችሁና ከኢትዮጵያውያን ጋር ልዩ ግንኙነት እንዳላቸው የሚያሳየን፣ አባባ ጃንሆይ ገና ራስ እያሉ እ.ኤ.አ በ1924 በአሳዳጊያቸው በአቡነ እንድሪያስ ጃሮሶ አማካይነት በቫቲካን ተገኝተው ስለወደፊቱ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ተወያይተዋል:: እንዲሁም በ1932 ልዑል አስፋው ወሰንና ልዕልት ተናኜ ወርቅ ለመንበረ ጴጥሮስ እንግዳ ነበሩ::

እውነቱን ለመናገር ይህ ራሱን ግሎባል አልያንስ ብሎ የሚጠራው ድርጅት ከማን በልጦ እሱ ታላቋን ዓለም አቀፍ ቤተ ክርስቲያን (Universal Church) ይቅርታ እንድትጠይቅ ጠያቂ አደረገው? በአገራችን ታላላቆቹ የፖለቲካና

ማስታ

ወቂያ

LABATA FANTALLE ORGANIZATIONBy the community for the communityUummataan, uummataaf

Labata Fantalle Organization is an Ethiopian resident charity established in auditors/audit firms to send their technical and financial proposal to perform annual audit for the fiscal year ended December 31,2012. The audit firms should meet the following criterial to participate in the bid:

• Renewed business license

• Official registration letter with the office of Auditor General

• Evidence of TIN certification

• Experience in auditing NGOs and familiarity with EFDR Charities and Societies Agency’s Auditing Regulation No. 08/2004

Interested firms who fulfill the criteria mentioned above can submit their technical and financial proposals to the address below before February 14, 2013.

Preferably by E-mail to [email protected] orLabata Fantalle OrganizationP.O.Box 27, Metahara

Page 28: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 28 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ማስታ

ወቂያ

Invitation to BidYirgachefee Coffee Farmers Cooperative Union (YCFCU) wants to maintain its building conventionally called “Lael building” in Dilla town. Therefore, YCFCU would like to invite local contractors of category GC/BC 5 and above.

1. Interested contractors who are registered for VAT and Tax Payer and who can present the following renewed licenses for the Ethiopian fiscal year of 2005.

• Trading license from the Ministry of Trade

• Registration certificate from Ministry of Construction and Urban Development

• Fulfillment of clearance to bid from Ministry of inland Revenue will be taken eligible for the bid.

2. The bid documents can be obtained for non-returnable amount of only ETB 350.00 (Three Hundred Fifty) at the flowing address within 15 calendar days of this announcement:

Yirgacheffe Coffee Farmers Cooperative Union Office, Dilla, Opposite to NOC Fuel Station.

Tel. 251-463-312-671/251-911-996-523

3. The bidders shall submit the original and one copy of the officer document which are sealed

in a separate envelope and marked :Original offer document”:

4. The bid documents shall be accompanied with bid security of ETB 30,000.00 (Thirty thousand) in an acceptable form of Bank guarantee/CPO and must be addressed to YCEFCU in a separate envelope marked “Bid security”. The tender documents and bid security shall then be sealed in an outer envelope marked “Offer Documents for the Maintenance of “Lael Building”

5. The company profile shall be submitted in a separate envelope and marked “Company Profile Document”.

6. Wax Sealed envelopes containing offer and company profile documents shall be submitted to Yirgacheffe Coffee Farmes Cooperative Union Office at Dilla on or before 10 hours (morning, 4 AM) the 16th calendar day beginning from the first issuance date of the bid on the Newspaper. If the 16th day is not the working day, the submission day will be the next working day.

7. Pre-tender meeting and site visit will be conducted two day before the submission date.

8. The employer reserves the right to reject the bid.

በትግራይ ክልል ፣ በመቐለ ከተማ፣ ዓዲሓውሲ ቀበሌ የሚገኝ

• 320 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው ባለ አንድ ፎቅ /G+1/ መኖርያ ቤት፤

• በዋናው ፎቅ 1 ሳሎን ፣ 4 መኝታ ቤት ፤ 3 ሽንት ቤትና ሻወር ፣

እንዲሁም የሰርቪስ ክፍሎች ያሟላ ውብ ቪላ ዓይነት የግል ፎቅ ለሽያጭ

ቀርቧል፡፡

• ለበለጠ መረጃ - Visit “betoch.net” and click “house for sale” or “Live

in Ethiopia” under Abadi on the Internet

0914-706475, ወይ +17708374555, Fax 0344-408768 Atte.

Amare G/T, Email [email protected] or

[email protected]            

የሚሸጥ ህንፃ

ተ ሟ ገ ት

የሃይማኖት መሪዎች፣ አንደበተ ርቱው የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊና ፓትርያኩ አቡነ ጳውሎስ ወደ መንበረ ጴጥሮስ በተደጋጋሚ መሄዳቸው የታወቀ ነው:: አንድም ቀን ይህ አውቅላቹኋለሁ ባዩ ድርጅት እንደሚለው መንበረ ጴጥሮስ ይቅርታ ትጠይቀን ያሉበት ጊዜ የለም:: በተለይም ደግሞ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ እንደሚታወቀው ሁሉ በታሪካቸው ከሠሩት ውስጥ አንዱ የአፍሪካን ኅብረት ከኢትዮጵያ ለማስወጣት የተደረገውን ጥረት በመበጣጠስ የማንም የውጭ ተፅዕኖ ሳይኖር፣ እንዲሁም አገራችን ለአፍሪካ ያደረገችውን ሁሉ በመተንተን አሳምነው የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ አገራችን ውስጥ እንዲቀር አድረገዋል:: ታዲያ መንበረ ጴጥሮስ በሄዱበት ወቅት የጠየቁት ጥያቄ በትምህርት፣ በጤና፣ በመሠረተ ልማት፣ በተለይም በአሁኑ ወቅት ሥራውን የጀመረውን የካቶሊክ ዩኒቨርሲቲና በኤችአይቪ ዙሪያ ነበር እንጂ፣ ካላቸው ችሎታና በተግባር ካደረጉት አንፃር ይህንን ማድረግ ተስኗቸው ይሆን? አይሆንም:: ይህንን ጥያቄ መጠየቅና ለማሳመን አይሞክሩም ማለት ደግሞም አይቻልም:: ቤተ ክርስቲያናችን ከሞሶሎኒ ጋር ወግና ቢሆን ኖሮ ይህንን ድርጅት ሳንጠብቅ ራሳችን ካቶሊካውያን መንበረ ጴጥሮስን ይቅርታ እንድትጠይቅ የቅድሚያ ሥራችን በሆነ ነበር:: እንዲሁም የአክሱምን ሐውልት ያስመለሰው ኮሚቴስ ዝም ይል ነበር ብላችሁ ነው? ነገር ግን የሚያሳዝነው ጸሐፍት (ደራሲያን) ሳይቀሩ ያልተረጋገጠ ወሬ ይዘው እኛ ኢትዮጵያውያን ካቶሊኮችን ጭንቅላታችንን በብዕራቸው ቧጠጡን:: የሚገርመው ከጋዜጣ ወስደው የታሪክ መጽሐፍ ብለው አወጡት የሚያሳዝን ምግባር::

ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ቃሉ በኤፌሶን እንደሚናገረው ‹‹አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት›› የተባለላት በዓለም ዳር እስከ ዳር ያለች፣ የዓለም ከአንድ አራተኛ በላይ ሕዝብ የሚከተላትና እንደሌሎቹ የተለያች ሳትሆን፣ በአንድ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት የምትመራና በዓለማችን በተለያዩ ምክንያቶች በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በዘር፣ በቀለም፣ በሃይማኖት፣ በጦርነት፣ በበሽታ፣ በኃጢያት የሰው ልጅ ያጣውን ክብር ለማስመለስ ስለሰው ልጅ የምትታገልና የምትፀልይ፣ እንዲሁም ሕዝበ እግዚአብሔርን ከእግዚአብሔር የምታስታርቅ የእግዚአብሔር መንግሥት ነች:: መንበረ ጴጥሮስ በምድር የክርስቶስን ሥራ እየሠራች በሚስጢራቷ ሕዝበ እግዚአብሔርን ወደ ገነት ትመራለች፣ ትባርካለች እንጂ ጦር አትባርክም::

የሁሉም እናት ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ አካልና በምድር የክርስቶስን ሥራ በምትሠራበት ጊዜ ከባዛንታይን፣

ከሁለቱ የዓለም ጦርነቶች፣ ከፋሺዝምና ናዚዝም እንዲሁም በሽብርና በፖለቲካ ምክንያት በሚፈጠሩ የእርስ በእርስ ጦርነቶችና በሽታዎች እስካሁን በፈተና ውስጥ ትገኛለች:: በአሁኑ ወቅትም ፍቺ በበዛበት ዓለም፣ የፅንስ ማቋረጥ፣ የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ፣ ሰው ሠራሽ የወሊድ ቁጥጥርን ሁሉ እየታገለች የክርስቶስን መንግሥት ታስፋፋለች:: ይህ ሁሉ ነገር በአሁኑ ወቅት በአገራችን ከመጠን ባለፈ ሁኔታ እየተስፋፋ ነው:: መናገርና ሐሳቡን መግለጽ የማይችል ሕፃን እየተጨናገፈ ሞት ሲፈረድበት፣ በማዘጋጃ ቤት ትዳር ከሚመሠርቱት እኩል ፍቺው እየበለጠና በሰው ሠራሽ የወሊድ ቁጥጥር ሴቶቻችን እየተጎዱ ባሉበት፣ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት በበዛበት በዚህ ወቅት ለእነዚህ ነገሮች ትኩረት የሚሰጥና የሚሟገት አለመኖሩ የሰው ልጅ ክብሩን ማጣቱን ያሳየኛል:: ይህ ግሎባል አልያንስ የሚባል ድርጅትና አቶ ኪዳኔ በቀላሉ እንኳን በአዲስ አበባ በየሚኒባስ ታክሲ ውስጥ የቆንጆ ውብ የአገራችን ሴቶች ፎቶአቸው ተለጥፎ ‹‹አይ ፕላን፣ ቾይስ፣ ኮንፊደንስ፣ ሉፕ . . . ›› እየተባለ ማስተዋወቂያ ከሆኑ ሰንብተዋል:: ኮንዶም እንዲሁም የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት በደራበት መዲናችን በየቦታው የፅንስ ማቋረጫ ክኒሊኮች በዝተው የሕፃን ልጅ አካል ተበጣጥሶ በየቆሻሻውና በየወንዙ ሲጣል፣ ለእዚህና ለሚያስከትለው የባህል መዝቀጥ የሰው ልጅ ክብሩን ማጣት እንኳን መፍትሔ የሌላችሁ ሆናችሁ፣ ድምፅ ለሌለው ድምፅ ሆና ያለችንና የራሷ የተፈጥሮ የወሊድ ቁጥጥር ያላትን፣ ፍቺ የማትፈቅድን፣ ውርጃን ከኃጢያት የምትቆጥርን፣ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን የምታወግዝን ቤተ ክርስቲያንን ለመውቀስ መነሳቱ ድብቅ ተልዕኮ እንዳነገባችሁ ያሳየናል::

ውድ አንባቢያን ኢትዮጵያውያን ካቶሊኮች እንዲሁም መልካም ፈቃድ ላላችሁ ሁሉ ክቡር አምባሳደር ዘውዴ ረታን በእውነት ከልቤ ሳመሰግናቸው፣ እውነት ለመናገር ያደጉበት ማኅበረሰብና አካባቢ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጎላቸዋል:: በፍቅር ያደጉ በመሆኑ እውነትን ለመናገርና ለመመስከር የሚቆጥቡት አንደበት የላቸውም:: በአሁኑ ጊዜ ከእሳቸው ልንማር የሚገባን በእምነት (በእውነት) ጠንክረን በፅናት መኖርን ነው:: እንዲሁም እውነትና ንጋት እያደር ይጠራልና ባልሰማነውና ባላየነው ወንድማችን ላይ ጣትን መቀሰር (መመስከር) በኋላ የሚያስተዛዝብ ባቻ ሳይሆን፣ ወንጀልም በመሆኑ ያስጠይቃልና እንጠንቀቅ:: በተመሳሳይም ውሸት የሰበኩንን፣ ማረጋገጫ ሳይኖራቸው የፈረዱብንን ሁሉ ይቅር እንድንል እንገደዳለን:: ግሎባል አልያንስም ሆነ አቶ ኪዳኔ አለማየሁ በቫቲካን ላይ ድምፅ ማሰባሰብና ካቶሊኮችን የመውቀስ ነጋሪትን መጎሰም ትታችሁ ፊታችሁን ወደ ሰላምና ፍቅር በመመለስ ተደጋግፎ መኖር ግድ ይላችኋል:: በዓለም ታላቋ የእግዚአብሔር መንበርም ፍቅርን እየሰበከች፣ ሰላምን እየዘመረች፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ፀንታ በልጆቿ ተወዳ ትኖራለች::

ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል::

Page 29: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 29 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1

Expression of Interest for House Rent

Concern Worldwide is a non-governmental, international, humanitarian organization which envisions a world where no one lives in poverty, in fear or oppression, where all have access to a decent standard of living and have opportunities and choices essential to a long, healthy and creative life.

Concern Worldwide would like to sign a one year contract with possibilities of extension to rent a house that fulfills the following criteria.

Description• A minimum of five bed rooms at least 8square meters each • Leaving room should be at least 20square meter• kitchen with built-in cupboard • Bath rooms and toilets (external and internal) • Well ventilated with open space• Parking space should park at least two average size saloon vehicles• There should be a Guard’s room at the gate• The house should be situated within one and half kilometers radius from Concern Worldwide

in Ethiopia head office (located at Shola market) and close to the main road• Fence should be a well-constructed by hollow block, stone, concrete and alike• House should have well working utilities(water line, Electricity & Telephone)• There should be at least a one thousand liter water Tank• A garden area is preferable• A house in a compound is much preferable for security

Thus, Concern Worldwide would like to invite eligible and competitive house owners to submit their offer with sealed envelope to Concern Worldwide-Ethiopia Country office, which is located around Sholla Market on or before February 20, 2013 to the following address.

Concern World Wide, Addis Ababa Ethiopia, Sholla MarketYeka Sub- city, kebele 13/14

P.o. Box: 2434Telephone: + 251 11 661 17 30 /651 23 60

Fax: + 251 11 661 15 44

For further clarification, please contact our administration unit at any of working hours before the deadline with following address; telephone +251-116-611730 e-mail concern.

[email protected]

NOTE: Concern Worldwide reserves the right to reject all or part of the bids.

T-shirt specificationsEvery partner should print t-shirts in two colors green and red. The t-shirts should come in all sizes small, medium and large sizes as per the needs. For instance, if you decide to print 2000 t-shirts this is how you should do it; 916 green (make sure to have different size ranges for each color as per your need) 1000 red (make sure to have different size ranges for each color as per your need)

The material of the t-shirts should be of maximum quality, preferably should weight 250 gram.The t-shirts should be printed in heat press that gives the maximum quality print. Yekokeb Berhan banner (size 23cm height*21cm width) should be placed at the front side of the t-shirt (see the designs below).Program name “Yekokeb Berhan” should be placed at the top of the banner with Font type: Gill Sans MT Font size: 36 Font color: white (see below)

Please not that “Yekokeb Berhan”, should not be translated to other languages since it is a program name. It should be kept as it is.Front sides of the t-shirts should look like this

Logos of PEPFAR, USAID and Pact should come first at the back side of the t-shirt as per given order withsize of (6cm height *6cm width). (Refer to the designs below).As you can see, you can replace the Amharic version of the slogan (በጋራ ለህፃናት) to Tigrigna, Oromiffa

andSomaligna to suit your specific region. We have translated the slogan as follows and these can be furtheredited if the need arises ;

ንህፃናት ብሓባር _______Tigrigna versionWal-wajjin Daa'immaanif____Afan Oromo version

Aynu si wadaiir ah carruuteena______ Somaligna versionPartners can put their logos in between of FHI 360 and Child Fund logo. Please note that it is optional toinsert partner logo. Partner’s logo that is inserted should be the same size as FHI 360 and Child Fundlogo sizes (5cm*5cm).Back sides of the t-shirts should look like

T-shirt specifications Every partner should print t-shirts in two colors green and red. The t-shirts should come in all sizes small, medium and large sizes as per the needs. For instance, if you decide to print 2000 t-shirts this is how you should do it;

916 green (make sure to have different size ranges for each color as per your need) 1000 red (make sure to have different size ranges for each color as per your need)

The material of the t-shirts should be of maximum quality, preferably should weight 250 gram. The t-shirts should be printed in heat press that gives the maximum quality print. Yekokeb Berhan banner (size 23cm height*21cm width) should be placed at the front side of the t-shirt (see the designs below). Program name “Yekokeb Berhan” should be placed at the top of the banner with

Font type: Gill Sans MT Font size: 36 Font color: white (see below)

Please not that “Yekokeb Berhan”, should not be translated to other languages since it is a program name. It should be kept as it is. Front sides of the t-shirts should look like this

Logos of PEPFAR, USAID and Pact should come first at the back side of the t-shirt as per given order with size of (6cm height *6cm width). (Refer to the designs below). As you can see, you can replace the Amharic version of the slogan (በጋራ ለህፃናት) to Tigrigna, Oromiffa and Somaligna to suit your specific region. We have translated the slogan as follows and these can be further edited if the need arises ;

ንህፃናት ብሓባር _______Tigrigna version Wal-wajjin Daa'immaanif____Afan Oromo version

Aynu si wadaiir ah carruuteena______ Somaligna version Partners can put their logos in between of FHI 360 and Child Fund logo. Please note that it is optional to insert partner logo. Partner’s logo that is inserted should be the same size as FHI 360 and Child Fund logo sizes (5cm*5cm). Back sides of the t-shirts should look like

Kindly use the logos we have attached in the email to maintain high quality print of the t-shirts and make sure the logs aren’t stretched disproportionally. In terms of quantities: partners should use the budget that is approved by the Grant Office to determine the number of t-shirts to be printed. Finally, we would like to remind you to print the logos as the exact order as presented on the designs above. Please also make sure the sizes of the logos are as specified above. If you have any questions or want address of recommended printing place, contact Nardos Mengesha, Senior Technical Communication Officer, at 0913030434 or [email protected] Respective Regional Managers for your area.

Kindly use the logos we have attached in the email to maintain high quality print of the t-shirts and make sure the logs aren’t stretched disproportionally.In terms of quantities: partners should use the budget that is approved by the Grant Office to determine the number of t-shirts to be printed.Finally, we would like to remind you to print the logos as the exact order as presented on the designs above. Please also make sure the sizes of the logos are as specified above.If you have any questions or want address of recommended printing place, contact Nardos Mengesha, Senior Technical Communication Officer, at 0913030434 [email protected] Respective Regional Managers for your area.NoticePls consider the following additional specification1.Size of the t-shirt are Medium-500pcs,L=500pcs,XL=500pcs and XXL=416pcs2. Colour of the t-shirt are Red =1000pcs and green=916pcs3. Please bring one t-shirt sample at the time of open the bid. በጨረታው የሚወዳደሩ ሁሉ ከዚህ በታች የተመለከቱትን መመሪያዎች ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ 1. የታደሰ የንግድ ፈቃድ ፎቶ ኮፒ2. የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ምስክር ወረቀት3. ተጫራቾች ጫራታቸውን በሰም በታሸገ ኢንቬሎኘ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡ 4. ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ቲሽርት ናሙና ማቅረብ ያለባቸው ሲሆን ናሙና ያላቀረበ ተጫራች

ከጨረታው ይሰረዛል፡፡ 5. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን እስከ ጨረታው መዝጊያ እለት በስራ ሰዓት ከቀኑ 8፡00 ሰዓት

ድረስ በግዥ ክፍል በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ገቢ ማድረግ አለባቸው፡፡ 6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 30 /ሰላሳ ብር ብቻ/ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ

በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ አዲስ አበባ በሚገኘው ጽ/ቤታችን ቢሮ ቁጥር 305 ወይም ባህር ዳር በሚገኘው በአልማ ዋ/መ/ቤት ቢሮ ቁጥር 411 መውሰድ ይቻላል፡፡

7. የ ጨረታ መክፈቻ የካቲት 11/2005 ዓ.ም 8፡30 ሰዓት ተጫራቾች በተገኙበት ይከፈታል፡፡ 8. መ/ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡9. ተጫራቾች የተጫረቱበትን ዋጋ 2% ሲፒኦ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0115512528/0582264982/0582266364 በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡ አድራሻ ፡-ቦሌ መንገድ ቦሌ ማተሚያ ጎን

ማስታወቂያ

Page 30: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 30 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ማስታ

ወቂያየጨረታ ሰነድ ቁጥር /027/2012/2013

ትራንስ ኢትዮጵያ ኃ.የተ.የግ.ማህበር ለስፖርተኞች የሚሆን ልብስ፣ ጫማ እና ተዛማጅ እቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

ስለሆነም ተጫራቾች፡-

1. ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑ ግብር የከፈሉ መሆን አለባቸው /የማስረጃው ፎቶ ኮፒ ማያያዝ ያስፈልጋል/

2. ተጫራቾች በዚሁ ስራ የተሰማሩ መሆናቸው ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው፣

3. ተጫራቾች የጨረታ ዋጋ ሲያስገቡ በጨረታ ዶኩሜንቱ በተቀመጠው ስፔስፍኬሽን መሰረት መሆን አለበት፣

4. የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 50 /አምሳ ብር/ በመክፈል አዲስ አበባ ላይዘን ኦፊስ እና መቐለ በሚገኘው የግዢ፣ ንብረት አቅርቦትና ቁጥጥር መምሪያ ቢሮ መውሰድ ይችላሉ፣

5. የጨረታ ማስከበሪያ ከጠቅላላ ዋጋ 2% በሲፒኦ (CPO) መልክ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

6. የጨረታው አሸናፊ ጨረታው ካሸነፈበት ቀን ጀምሮ በ10 ቀናት ውስጥ በራሱ ማጓጓዣ ስቶራችን ድረስ ማቅረብ አለበት፡፡

7. ተጫራቾች ላሸነፉት መለዋወጫ ዕቃ ክፍያ የምንፈፅመው እቃው ኢንስፔክት ተደርጎ (GRV) ተቆርጦ መጋዘን እንደገባ መሆኑ ማወቅ አለባቸው፡፡

8. ተጫራቾች በተሰጣቸው ሰነድ ውስጥ ብቻ ዋጋቸውን ሞልተው በሰም በታሸገ ኤንቨሎኘ እስከ የካቲት 20 ቀን 2005 ዓ.ም. ከጠዋቱ 4፡00 ባለው ጊዜ ውስጥ መቐለ ግዢና፣ ንብረት አቅርቦትና ቁጥጥር መመሪያ ቢሮ ወይም አዲስ አበባ ላይዘን ኦፊስ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡

9. ጨረታው በዚሁ ቀን ማለትም የካቲት 20 ቀን 2005 ዓ.ም. ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አዲስ አበባ ላይዘን ኦፊስ እና መቐለ የግዢ፣ ንብረት አቅርቦትና ቁጥጥር መምሪያ ቢሮ በተመሳሳይ ይከፈታል፡፡

10. ኩባንያው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

11. ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር 034-441 64 39/0914731903/034-440 82 05 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

Invitation for the supply of Computer, Sonic

WALL and Health Related BooksJhpiego Corporation, an affiliated of Johns Hopkins University, works to improve the health of Women and families in limited-resource settings worldwide through strengthening the capacities of local institutions, systems, and facilities in the health sector.

Jhpiego Ethiopia would like to purchase the under listed items as per stated specifications.

1. Desktop Computer

Computer Specification

Model Dell Optiplex 3010

Processor Intel i3-2120 / 3.3 GHz

RAM 2 GB

Optical drive DVD+RW

HDD 320 GB

Graphics Intel HD Graphics Dynamic Video Memory Technology 5.0

Communication Intel Gigabit Ethernet LAN 10/100/1000 Dell Wireless 1520 PCIe WLAN card (802.11n)

Audio Realtek High Definition Audio Codec

keyboard and mouse Standard Keyboard and optical mouse

Quantity – 800pcs

• Vendor MUST BE DELL AUTHORIZED SERVICE

CENTER & AUTHORIZED DEALER2. Sonic WALL

Product Quantity

NSA 250M Network Security Appliance Secure Upgrade - 3 Years (A5572006)

1

Sonic WALL - Rack mounting kit - for NSA 250M (A5961441)

2

NSA 250M HIGH AVAILABILITY (A5586648) 1

UPG NSA 250M STATEFUL HA (A5564431) 1

3. Health Related Books – Interested vendors can collect list of health related books from Operation Manager Office, Jhpiego Ethiopia office.

N.B - Interested bidder should attach the following with price quotations

• Renewed business license.

• Tax payer registration certificate.

Interested bidders are invited to submit bids in sealed envelopes within seven working days from the date of advertisement on the newspaper to the Jhpiego Ethiopia Country office, WolloSefer near Mina Building P.O. Box 2881, code 1250 Addis Ababa, Tel. 0115-50-21-24 or 0115 – 540643.

Bid should be addressed to Operations Manager, Jhpiego.

Jhpiego Ethiopia reserves the right to reject the bid fully or partial.

InvItatIon for ConsultanCy servICeThe Private Sector Development Hub invites eligible national consultants to participate in a bid to conduct studies on:

a. Property Rights Protection and Private Sector Development in Ethiopia

b. Revisiting the Ethiopian Private Sector Associative Formats

1. Eligible consultants may bid for one or both studies.

2. Consultants may associate with other consultancy firms to enhance their capacity

3. The tender documents consisting of the Terms of References (ToR) and Instructions to Bidders (IB) can be obtained from the PSD Hub, Mexico Square, Chamber Building 7th Floor Room No 705, during normal working hours Monday to Friday, starting from Monday, February 11, 2013.

4. Interested bidders should submit currently renewed trade license and other required documentation for qualification of bidders as indicated in the instruction to Bidders.

5. Bidders should submit their Technical and Financial Proposals in separate envelopes to following address on or before Monday, February 25, 2013, 5:00 P.M.

Private Sector Development Hub Ethiopia Chamber of Commerce and Sectoral Associations (ECCSA)

Mexico Square Room No. 707Addis Ababa

6. Technical Proposals of Bidders will be opened on Tuesday, February 26, 2013 at 10:00 A.M in the Board Room of ECCSA in the presence of bidders or their representatives who choose to attend.

7. The PSD Hub reserves the right to accept or reject any or all bids 8. For further information and queries, please contact

Attention: Manager, PSD Hub Tel: 011 554 9684/55494 25

Fax: 011 554 92 78

AACCSA SIDAECCSA

Private Sector Development Hub

ማስታወቂያ

Page 31: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 31 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1

የአገር ውስጥ ዜና የዓለም ዜናተስፍሽ እና ገብርሽየማሊ ጦርነት ፈረንሳይን በቀን

2.7 ሚሊዮን ዩሮ እያስወጣት ነውየማሊን ሰሜናዊ ክፍል ተቆጣጥረው የነበሩትን

ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት ያላቸውን አክራሪ አማፂያን ለመዋጋት ዘመቻ የጀመረችው ፈረንሳይ በቀን 2.7 ሚሊዮን ዩሮ ወጪ እያደረገች መሆኑን የዘገበው ፍራንስ 24 ነው:: እስካለፈው ረቡዕ ድረስ 70 ሚሊዮን ዩሮ ወጪ ማድረጓን የፈረንሳይ መከላከያ ሚኒስትር ዣን ይቨስ ለ ድሪያን ለፓርላማ መግለጻቸውን ዘገባው አመልክቷል:: በአውሮፓ በደረሰው የፋይናንስ ቀውስ ምክንያት የበጀት ጉድለት የገጠማት ፈረንሳይ፣ የአየር ኃይሏንና የምድር ጦሯን ከማሊ ወታደሮች ጋር በማሠለፍ የአክራሪ አማፂያኑን ጠንካራ ይዞታ ማስለቀቋ ይታወቃል:: በማሊ የሚደረገው የፈረንሳይ ዘመቻ ወጪ መናሩን የጠቆመው ዘገባው፣ ይህ ወጪ ፈረንሳይ በሊቢያና በአፍጋኒስታን በቀን ካወጣችው ይልቃል ብሏል:: ፈረንሳይ የሙአመር ጋዳፊን መንግሥት ለማስወገድ በተካሄደው የሊቢያ ዘመቻ በቀን 1.6 ሚሊዮን፣ በአፍጋኒስታን ደግሞ 1.4 ሚሊዮን እንደምታወጣ ተነግሯል:: ፈረንሳይ በማሊ 4,600 ወታደሮችን በማሰማራት ከአየርና ከምድር አክራሪ አማፂያንን በመደብደብ በርካታ ይዞታዎችን መቆጣጠሯ አይዘነጋም::

ደቡብ አፍሪካ የኮንጎ አማፂያንን በመፈንቅለ መንግሥት ሴራ ከሰሰች

የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አማፂ ቡድን አባላት የሆኑ 19 ተጠርጣሪዎችን በመፈንቅለ መንግሥት ሴራ በመወንጀል ደቡብ አፍሪካ ክስ መሠረተች:: እንደ ቢቢሲ ዘገባ፣ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንትን በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ለማውረድ አሲረዋል የተባሉት ተጠርጣሪዎች፣ በደቡብ አፍሪካ ፀረ ሽብር ኃይል ባለፈው ሳምንት ውስጥ ተይዘዋል:: በፕሬዚዳንቱ የሥልጣን ዘመን በአማፂያን ግጭቶች የምትታመሰው ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በቅርቡ ደግሞ ኤም23 በሚባሉ አማፂያን ጦርነት ቁምስቅሏን እያየች ነው:: አባታቸው ከተገደሉ በኋላ እ.ኤ.አ በ2001 ሥልጣን የያዙት ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ካቢላ፣ ሊገለብጡዋቸው አሲረዋል ተብለው ከተያዙት ውስጥ አንዱ የአሜሪካ ዜግነት እንዳለው አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል:: ተጠርጣሪዎቹ ደቡብ አፍሪካ የገቡት ይኼንን ሴራ ለማስተባበር መሆኑንም ዘገባው አክሎ ገልጿል::

ሕገወጥ የገንዘብ ፍልሰትን ለማስቆም የዘጠኝ ሚሊዮን ዶላር ፈንድ ተገኘ

ትረስት አፍሪካ የተሰኘ ተቋም ከፎርድ ፋውንዴሽን በተገኘ የዘጠኝ ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ከአፍሪካ በሕገወጥ መንገድ የሚሸሽ ገንዘብ ዝውውርን ለማስቆም አዲስ እንቅስቃሴ ጀመረ:: ተቋሙ ከሴኔጋል ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ፈንዱ የሚውለው የሲቪል ማኅበረሰቦች ከአፍሪካ በሕገወጥ መንገድ የሚወጣውን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እንዲያስቆሙ የጉትጎታ ሥራ እንዲሠሩ ያስችላቸዋል:: በዚህም መሠረት የሚቋቋመው ፕሮጀክት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለማስቆም የሚያደርጉትን ጥረት ለማጠናከር ያግዛል ተብሏል:: የግሎባል ፋይናንሻል ኢንተግሪቲ ሪፖርትን ዋቢ ያደረገው መግለጫው፣ ከአፍሪካ አኅጉር የሚወጣውን ሕገወጥ ገንዘብ ማስቆም ከተቻለ አኅጉሪቱ ያለባትን 250 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ ለመክፈል ከበቂ በላይ ነው ብሏል:: በአፍሪካ ሕገወጥ የገንዘብ ማሸሽ መገለጫዎች የኮንትሮባንድ ዕፅ ዝውውር፣ ታክስ ማጭበርበር፣ የገቢና የወጪ ምርቶችን ዋጋ ማጭበርበር የመሳሰሉት ናቸው:: እነዚህ ችግሮች በመንግሥታትና በትላልቅ ኮርፖሬሽኖች አማካይነት ያለተጠያቂነት የሚከናወኑ መሆናቸው ተገልጿል:: እንዲህ ዓይነቱን ድርጊት ለማስቆም የሲቪል ማኅበረሰቡ ትክክለኛ ፖሊሲዎች እንዲወጡ ድምፁን ማሰማት አለበት መባሉን መግለጫው አስታውቋል::

ናይጄሪያ ውስጥ ታጣቂዎች ዘጠኝ ሴት የጤና ባለሙያዎችን ገደሉበናይጄሪያ ካኖ በተባለ ከተማ የፖሊዮ ክትባት

በመስጠት ላይ የነበሩ ዘጠኝ ሴት የጤና ባለሙያዎች ባልታወቁ ታጣቂዎች መገደላቸውን የዘገበው ቻናልስ የተሰኘው ድረ ገጽ ነው:: በባለ ሦስት እግር የሞተር ብስክሌቶች ላይ ሆነው ነው ተኩስ የከፈቱት ታጣቂዎች ቤት ለቤት በመሄድ በሥራ ላይ በነበሩት ሴቶች ላይ መሆኑን የዓይን እማኞች መናገራቸው ተዘግቧል:: በአካባቢው በሞተር ብስክሌቶች በመጠቀም ጥቃት ሲፈጸም የመጀመርያው ነው ተብሏል:: ናይጄሪያ ውስጥ እ.ኤ.አ በ2003 የተወሰኑ የሙስሊም ሃይማኖት መሪዎች የፖሊዮ ክትባትን መቃወማቸውን ዘገባው ጠቁሞ፣ በምክንያትነት ያስቀመጡት ደግሞ የፖሊዮ ክትባት የሰው ልጅ መራባትን ያጨናግፋል በሚል መሆኑን አስታውቋል::

ባለፈው ሳምንት በአንድ የኤፍኤም ሬዲዮ ጣቢያ በሁለት ግለሰቦች መካከል ገላጋይ የለም ወይ አስኪባል ድረስ የሰማሁት ጭቅጭቅ ለገጠመኜ መነሻ ሆኖኛል:: የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ከ31 ዓመታት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ውድድር የመለሰው አሠልጣኝ ሰውነት ቢሻውና የስፖርት ጋዜጠኛና ተንታኝ ነኝ የሚለው ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ደቡብ አፍሪካ ደርሶ በተመለሰው ቡድን ላይ ሲነጋገሩ፣ ውይይቱን ተቆጣጥሮ መምራት በተሳነው ጋዜጠኛ ምክንያት ለጆሮ የሚቀፉ ነገሮችን ሰምተናል:: በተለይ አቶ ገነነ የሚባለው ሰው የዋና አሠልጣኙን የሚመሰገን ተግባር በማንቋሸሽና በድክመቶች ላይ ብቻ በመንጠላጠል በአሽሙርና በአግቦ የተሞሉ ትንኮሳዎችን ሲፈጽም በጣም ነው ያዘንኩት:: እኛ በሚሊዮኖች የምንቆጠር ኢትዮጵያውያን የእግር ኳስ አፍቃሪያን የብሔራዊ ቡድናችንን ድክመቶች ባየንበት ዓይናችን ተስፋ ሰጪ የሆኑ እንቅስቃሴዎችን መገንዘብ የቻልነው በአሠልጣኝ ሰውነት ቢሻው አመራር ነው:: አቶ ገነነ ግን ቂምና ቁርሾ ያለበት እስኪመስል ውስጡን በጥላቻ ሞልቶ ሲተፋው የነበረው መርዝ ለማን እንደሚጠቅም ሊገባኝ አልቻለም:: እኔ ብቻ ሳልሆን በዚህ ጉዳይ ያዘኑ በርካታ ሰዎች በተለያዩ ድረ ገጾች ጭምር አስተያየታቸውን ሰጥተዋል:: የአቶ ገነነ አስተያየት ከሚባል ይልቅ ተራ ጥላቻ ቢባል ይቀላል::

የአቶ ገነነው ችግር የሚጀምረው ቀና አስተሳሰብ (Positive Thinking) ስለሌለው ነው:: የአገራችን እግር ኳስ ችግር ሲታሰብ ግለሰብ ላይ ለመንጠላጠል ካሰብን የእኛ ጉዳይ እዚያ ላይ ያልቅለታል:: አቶ ገነነው ለአገሪቱ እግር ኳስ ችግር መነሻና መድረሻ ለማድረግ የሞከረው አሠልጣኝ ሰውነትን አስመስሎበታል:: ይህ ዓይነቱ ጨለምተኛ አስተሳሰብ (Negative Thinking) የሚመነጨው ደግሞ ካለማወቅ ሳይሆን ከጥላቻ ነው:: አሠልጣኙ ሬዲዮ ጣቢያው ስቱዲዮ ተገኝቶ ገለጻ ሲያደርግ በጋዜጠኛው አማካይነት በስልክ መስመር አሳብሮ የገባው አቶ ገነነው፣ የአገሪቱ እግር ኳስ ችግር ከብሔራዊና ከክልል ፌዴሬሽኖች አወቃቀር፣ ከባለሙያ እጥረት፣ ከፋይናንስ ችግር፣ የክለቦች ለዘመናት ከተጠመዱበት ልማዳዊ አሠራር አለመውጣት፣ ለታዳጊዎች ትኩረት አለመስጠት፣ ለወጣቶች ዕድል በመንፈግ ዕድሜያቸው የገፉ ተጫዋቾችን ከአንዱ ክለብ ወደ አንዱ ክለብ ማዘዋወር (Recycle)፣ ወዘተ መሆኑ አይጠፋውም ነበር:: ቀና አመለካከት ባለመኖሩ ግን በቡድኑ ቆይታ ላይ ሊነሱ የሚገባቸው በርካታ ጉዳዮች ተትተው የቂምና የቁርሾ መድረክ ሆነ:: በዚህ አሳዛኝ ድርጊት ሬዲዮ ጣቢያው አድማጮቹን ይቅርታ መጠየቅ ነበረበት:: በበኩሌ እንዲህ ዓይነቱን አሳፋሪ ነገር ሳይሆን በጠንካራ አገራዊ ጉዳዮች ላይ የሞቀ ክርክር ማዳመጥ ይሻል ነበር እላለሁ:: ከንቱ የመንደር ወሬ ለማንም አይጠቅምምና:: እንዲህ ዓይነቱ ችግር በየቦታው ይስተዋላል:: ቀና አመለካከት ወይም አስተሳሰብ የሌላቸው ሰዎች በየቦታው ሰዎችን ሲያደናቅፉ ማየት የተለመደ ነው:: አንድ መሥርያ ቤት ሄዳችሁ መረጃ ስትጠይቁ “እሺ” ከሚላችሁ ይልቅ “እምቢ” የሚሉ ይበዛሉ:: አንድ ሠፈር ሄዳችሁ የሰው ቤት ስትጠይቁ ከሚያመላክታችሁ ይልቅ “አላውቅም” የሚሉ በሽ ናቸው:: አንድ ጊዜ ቦሌ ኢድና ሞል አጠገብ ደርሼ ሃርመኒ ሆቴልን እንዲያመላክተኝ የጠየቅኩት ግለሰብ “ምን ያደርግልሃል?” ሲለኝ ራሴን አላመንኩም ነበር:: ሌላ ጊዜ ደግሞ የኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን አራት ኪሎ ጽሕፈት ቤት ለጉዳይ ሄጄ አለቃውን እንደምፈልግ ለአንዱ ሠራተኛ ብነግረው፣ “ማንን ከሥራ ለማስባረር ፈልገህ ነው ለአቤቱታ የመጣኸው?” ሲለኝ በጣም ነበር የደነገጥኩት:: የሰውን ሐሳብ በጥሞና አዳምጦ በጥሩ አቀራረብ መነጋገር ሲቻል ለጠብና ለዱላ የሚቸኩሉም ሞልተዋል::

ቀና አስተሳሰብ በመጉደሉ ምክንያት ሰዎች ሰብዓዊ ክብራቸውና መብታቸው ተገፎ ሲንገላቱ የሚደሰቱ አሉ:: በመልካም አስተዳደር እጦት ምክንያት የተከፉ ዜጎች ሲያለቅሱ ለእነሱ የክብር ያህል የሚሰማቸው ጉዶች በየቦታው አሉላችሁ:: ፍትሕ ተረግጦና የሕግ የበላይነት ተንዶ ዜጎች መፈጠራቸውን ሲያማርሩ ጮቤ የሚረግጡ በየቦታው ተዘርተው ይታያሉ:: ዳኞችንና ዓቃቢያነ ሕግን በቃልና በስልክ እያስፈራሩና እያዘዙ ፍትሕን የሚያዛቡና ወገንን ደም እንባ የሚያስለቅሱም እንዲሁ:: በአገርና በሕዝብ ንብረት በሕገወጥ መንገድ ከብረው ከማፍያ ያልተናነሱ አሰቃቂ ተግባራትን የሚፈጽሙ ሞራላቸው የዘቀጠ በየቦታው አሉላችሁ:: እንዲህ ዓይነቶቹን ከንቱዎች ለማስተካከል ወይም ለማረም የሚነሱ ሰዎች ደግሞ ኢፍትሐዊ በሆነ መንገድ በደል ይደርስባቸዋል:: ቀና አስተሳሰብ ቢኖር ኖሮ ግን ይህ ሁሉ ምሬትና ጉስቁልና በደስታ ይቀየር ነበር:: አገርም ትባረክ ነበር::

ወደተነሳሁበት ጉዳይ ልመልሳችሁና አቶ ገነነው አሠልጣኝ ሰውነትን በመተንኮስና በማበሳጨት ስሜታዊ ሆኖ ያልተገቡ ንግግሮችን እንዲያደርግ ሲገፋፋው ነበር:: አሠልጣኝ ሰውነት ብዙ ጊዜ ራሱን ለመቆጣጠር ቢሞክርም አልፎ አልፎ ሲበሳጭና ሲቆጣ ተሰምቷል:: ላለፉት 31 ዓመታት ከአኅጉራዊ ውድድር ርቆ የቆየን ቡድን ከነችግሮቹ ተሸክሞ ደቡብ አፍሪካ የተጓዘው አሠልጣኝ ሰውነት ውጤት ማምጣት ነበረብህ ዓይነት ዘለፋና ማንጓጠጥ ሲደርስበት በጣም አዝኛለሁ:: ከብሔራዊ ቡድኑ ማን ውጤት ጠበቀ? በተቻለ መጠን ጥሩ ተፎካካሪ እንዲሆን ተመኘን እንጂ እንደ አቶ ገነነው ዓይነት ቅዠት አልቃዠንም:: ቡድኑ በተለይ ከዛምቢያና ከናይጄሪያ ጋር ያደረጋቸው ጠንካራ ፉክክሮች ብዙዎቻችንን አስደስቶናል:: ከቡርኪና ፋሶ ጋር በተደረገው ግጥሚያ ቡድኑ የዚያን ያህል ጎል ሊገባበት አይገባም ማለት እንችላለን:: ነገር ግን ለምን ተሸነፈ ማለት ትክክል አይደለም:: እኔ ቀና አስተሳሰብ ሊኖር የሚገባው እዚህ ላይ ነው እላለሁ:: ይኼ ውድድር ትልቅ ትምህርት ተገኝቶበታል:: ለመጪው ጊዜ ወጣቶቻችንን ለማዘጋጀትና ብርቱ ተፎካካሪ ለማድረግ ዓይናችን ከፍቶልናል:: ከዚህ ውጭ ብሔራዊ ጉዳይን ከመንደር አሉባልታ ወሬ ጋር እያቀላቀልን የትውልዱን ተስፋ አናበላሽ:: “ለወሬ የለው ፍሬ” እንደተባለው አሠልጣኝ ሰውነት ቢሻውን፣ የብሔራዊ ቡድኑን አባላትና ሌሎች ድጋፍ ሰጪዎችን እናመስግን:: ቀና አስተሳሰብ በሰፈነበት የመንደር ወሬ ቦታ የለውም::

(ሳሙኤል ተርፋሳ፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ)

ገጠመኝ

የአዲስ አበባ አስተዳደር ባለፉት ስድስት ወራት ለቤቶች ግንባታ ሦስት ቢሊዮን ብር አውጥቷል

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተያዘው በጀት ዓመት ግማሽ ለቤቶች ግንባታ ሦስት ቢሊዮን ብር ያህል ማውጣቱን አስታወቀ:: እንደ ኢዜአ ዘገባ፣ በአስተዳደሩ የኮንስትራክሽንና ቤቶች ልማት ቢሮ እንዳስታወቀው በተያዘው በጀት ዓመት በ5.7 ቢሊዮን ብር የቤቶች ግንባታ ይካሄዳል:: የቤቶች ግንባታ ሥራ በተቀናጀና በተደራጀ መንገድ እየተመራ መሆኑን ዘገባው አስታውቆ፣ በግንባታውም የተሻለ አፈጻጸም በመታየት ላይ መሆኑን የቢሮውን ኃላፊ ዋቢ አድርጓል:: በግማሽ በጀት ዓመቱ 20 ሺሕ የሚሆኑ የጋራ መኖርያ ቤቶች ግንባታቸው ተጠናቆ ለነዋሪዎች በማስረከብ ሒደት ላይ እንደሚገኝ ቢሮው ማስታወቁን ዘገባው አመልክቷል:: ከዚህ ውስጥ የ12 ሺሕ ቤቶችን ቁልፍ ለነዋሪዎች የማስረከብ ሥራ ከአንድ ወር በፊት መከናወኑንና የቀሪዎቹ ርክክብ እየተካሄደ መሆኑን ቢሮው ማስረዳቱን ዘገባው አውስቷል:: አስተዳደሩ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመኑ 95 ሺሕ ቤቶችን ለመገንባት አቅዶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አስታውቋል::

በምሥራቅ ወለጋ ዞን በ300 ሚሊዮን ብር የስኳር ፋብሪካ ሊገነባ ነውበኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ ወለጋ ዞን ሲቡ ስሬ

ወረዳ በአንድ የውጭ ባለሀብት በ300 ሚሊዮን ብር ለሚገነባው የስኳር ፋብሪካ ሰሞኑን የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ:: እንደ ኢዜአ ዘገባ፣ የስኳር ፋብሪካው ግንባታ በ2006 ዓ.ም. ሲጠናቀቅ በቀን አምስት ሺሕ ኩንታል ስኳር የማምረት አቅም ይኖረዋል:: ፋብሪካው ከስኳር በተጨማሪ ከተረፈ ምርት 1.2 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም እንደሚኖረውና ከአምስት ሺሕ ለሚበልጡ ዜጎችም የሥራ ዕድል ይፈጥራል መባሉን ዘገባው አስረድቷል:: ለፋብሪካው የሚያስፈልገውን የሸንኮራ አገዳ ለማልማት 3,492 ሔክታር መሬት ፋብሪካው መረከቡንና በ800 ሔክታር ላይ የሸንኮራ አገዳ ተከላ እያካሄደ መሆኑ ተጠቁሟል:: ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ማምረት ሲጀምር የተረከበውን መሬት ሙሉ በሙሉ በሸንኮራ አገዳ ለመሸፈንና የአካባቢው አርሶ አደሮችም የሸንኮራ አገዳ ምርጥ ዘር አቅርበው ተጠቃሚ እንዲሆኑ እንደሚፈለግ ዘገባው አመልክቷል::

የፀረ ሙስና ኮሚሽነር የአፍሪካ ኅብረት

የፀረ ሙስና አማካሪ ቦርድ አባል ሆኑየፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን

ኮሚሽነር ዓሊ ሱሌይማን የአፍሪካ ኅብረት የፀረ ሙስና አማካሪ ቦርድ አባል ሆነው ተመረጡ:: ዋልታ እንደዘገበው፣ አቶ ዓሊ ለሁለት ዓመታት የአፍሪካ ኅብረት የፀረ ሙስና አማካሪ ቦርድ አባል ሆነው እንዲያገለግሉ የተመረጡት ኅብረቱ በአዲስ አበባ ባካሄደው 28ኛው መደበኛ ጉባዔ ነው:: ፀረ ሙስና ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ መመረጧ አገሪቱ ሙስናን በመከላከልና በመዋጋት ረገድ እያካሄደች ላለው አበረታች እንቅስቃሴ ዕውቅና የሰጠ መሆኑን ያሳያል ብሏል:: ከዚህም በላይ የአገሪቷ የፀረ ሙስና ትግል እምነት የሚጣልበት መሆኑንና በትግሉ ቁርጠኛ አቋም እንዳላት የሚያሳይ መሆኑን መረዳት እንደሚቻል ኮሚሽኑ በመግለጫው ማስታወቁን ዘገባው አመልክቷል:: ለአፍሪካ ኅብረት የፀረ ሙስና አማካሪ ቦርድ አባልነት ከኢትዮጵያ የተመረጡትን አቶ ዓሊን ጨምሮ ከኮትዲቯር፣ ከጋና፣ ከቶጎ፣ ከብሩንዲ፣ ከሊቢያ፣ ከማሊ፣ ከቤኒን፣ ከናይጄሪያ፣ ከኮንጎና ከታንዛኒያ የተውጣጡ አሥራ አንድ ግለሰቦች መመረጣቸው በዘገባው ተገልጿል::

ውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ለተጓተቱ ፕሮጀክቶች ክትትልና ድጋፍ

እንዲያደርግ ማሳሰቢያ ተሰጠውየውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ለተጓተቱ የመስኖ

ልማትና የንፁህ ውኃ መጠጥ ፕሮጀክቶች የሚያደርገውን ክትትልና ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ማሳሰቢያ ተሰጠው:: ማሳሰቢያው የተሰጠው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተፈጥሮ ሀብት ልማትና የአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሲሆን፣ የሚኒስቴሩን የመጀመርያዎቹ ስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም አዳምጦም ምላሹን ሰጥቷል:: ሚኒስቴሩ ለመስኖ ፕሮጀክቶች፣ ለመጠጥ ውኃና ሳኒቴሽን፣ ለውኃ ሀብት አስተዳደር፣ ለውኃና ኢነርጂ፣ እንዲሁም ለአቅም ግንባታ የተመደበውን በጀት ሥራ ላይ የማዋል አፈጻጸሙ ዝቅተኛ መሆኑን ቋሚ ኮሚቴው አስታውቋል:: በአገሪቱ ከተሞች፣ መንደሮችና የገጠር ቀበሌዎች የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን ለማዳረስ የሚያጋጥሙ የማከፋፈያና የማስተላለፊያ አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት ከአቅራቢ ድርጅቶች ጋር ቅንጅታዊ ትስስር መፍጠር እንደሚገባ ማሳሰቢያ መሰጠቱን ለማወቅ ተችሏል::

Page 32: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 32 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1 ማስታወቂያ

www.ethiotelecom.et

የሞባይል ካርድ በመሙላት እስከ 15 ደቂቃ

የሚደርስ ነፃ የአየር ሰዓት ያግኙ!

ከጥር 28 እስከ የካቲት 26 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ ብቻ የሚቆይ

.

አጭር የጽሑፍ

ካርድዎን

ይሙሉ

በነፃ

ያግኙ

ደቂቃ

ደቂቃ

ደቂቃ

15

10

3

550 ቀናት 20 ቀናት 15 ቀናት 100 ቀናት

7 ቀናት 5 ቀናት 3 ቀናት 10 ቀናት

10 ደቂቃ 3 ደቂቃ 5 አጭር የጽሑፍ መልዕክት 15 ደቂቃ

የነፃ የ ሀገር ውስጥ ጥሪ ወይም

100 ብር 50 ብር 20 ብር 15 ብር

የቫውቸር ካርድ የአገልግሎት ጊዜ

ነፃ የሀገር ውስጥ ጥሪ / አጭር የጽሑፍ መልዕክት

የቫውቸር ካርድ መጠን

አጭር የጽሑፍ መልዕክት የአገልግሎት ጊዜ

መልዕክት

C

M

Y

CM

MY

CY

CMY

K

amharic-final-topup&bonus-tt2.pdf 1 2/5/13 10:04 AM

Page 33: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 33 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታወቂያ

Page 34: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 34 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ማስታ

ወቂያ

የኦዲት ማስታወቂያድርጅታችን ‹‹ዶ/ር ከበደ ሚካኤል ፋውንዴሽን›› ከ2001-2003 ዓ.ም. (የሶስት ዓመት) የሒሳብ እንቅስቀሴ፣ በተፈቀደላቸው ኦዲተሮች ማስመርመር ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም፣ የሒሳብ ምርመራ ሥራውን ለማከናወን የሥራ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ ባለሙያዎችን እንዲወዳደሩ ይጋብዛል፡፡

ስለዚህ፣ ተወዳዳሪዎች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ፣ ባሉት አምስት ተከታታይ የሥራ ቀናት በአካል በመቅረብ መወዳደር ይችላሉ፡፡

አድራሻ፡- ከካዛንቺስ ወደ አዋሬ አድዋ ድልድይ በሚወስደው መንገድ፣ ኢትዮ ሴራሚክ (የቀድሞው ቀይ መስቀል) ፊትለፊት፡፡

ለተጨማሪ መረጃ፡-

የስ.ቁ. 0115 54 97 22

NATIONAL BANK OF ETHIOPIAINVITATION FOR BID

Bid No. NBE/NCB/S/05/2012/131. National Bank of Ethiopia invites interested bidders for the Provision of Gardening

service.2. A complete set of Bidding Document can be obtained from Procurement team office

found next to National Bank of Ethiopia New building (SACCDO villa) upon deposit of non-refundable fee of Ethiopian Birr 100.00 (One hundred only) for each service in the account No. 01C0799703201 at Payment and settlement Directorate found in NBE New Building, sub-basement floor during office hours (Monday to Friday 8:00-10:30 a.m and 01:00- 03:30 p.m).

3. All Bids must be accompanied by bid security 2% of the Total Bid Price in the form of CPO or Bank Guarantee.

4. Bidders shall present copy of their renewed trade license for the year 2005 E.C., Tax Identification Number, Tax clearance certificate and VAT registration certificate.

5. Bids Shall Be submitted in the tender Box prepared for this purpose on /before February 26, 2013 10:00 A.M in the above mentioned address.

6. Bid opening shall be held in the presence of bidders and/or their representatives who wish to attend, in the above mentioned address, on February26, 2013 10:30 A.M.

7. Failure to comply any of the conditions from (3) to (6) above shall result in automatic rejection.

8. Interested eligible bidders may obtain further information from the office of Procurement team, Tel. No. +251115529286 or +25115529281.

9. The Bank reserves the right to accept or reject any or all bids at any time.

NATIONAL BANK OF ETHIOPIA

በጌታሁን ወርቁ

በኅብረተሰባችን ውስጥ አነጋጋሪ ከሆኑ ቤተሰባዊ ግንኙነቶች ውስጥ አባትነትን ወይም እናትነትን ማወቅ አንዱ ነው:: ከላይ በርእስነት የተጠቀምንበት አባባል በኅብረተሰባችን እየተነገረም፣ እየተፈጸመም ዘመናት ተቆጠሩ:: አባባሉ እናት በማንኛውም ሁኔታ ማንነቷን ለማወቅ የማያስቸግር፣ አባትን ግን እናት ለልጅ በነገረችና በታመነ መጠን የሚታወቅ መሆኑን ያመለክታል:: ይህን አባባል አንዳንዶች የሴቶችን አለመታመን የሚያሳይና ስብዕናቸውን ዝቅ የሚያደርግ እንደሆነ ይገልጻሉ:: ይህ አተያይ እንዲያውም ዙረት የሚያበዙ ወንዶችን የተሻለ ገላጭ ነው:: ዙረት ያበዛ ዱካውን በእምነት ብቻ ይቆጥራል:: የእናት እውነትነትም ቢሆን በዘመኑ አስቸጋሪ ሆኗል:: አባባሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በሥነ ተዋልዶ ላይ ያመጣውን ለውጥ ለሚያስብ እናትነትም እውነት መሆኑን በድፍረት ለመናገር የማንችልበት ደረጃ መድረሱን ይረዳል:: በኪራይ ማህፀን ወይም በቤተ ሙከራ ከጥንዶች ወይም ጥንድ ካልሆኑ ተቃራኒ ጾታዎች የተወለዱ ልጆች ሁኔታ እናትነት እውነት መሆኑን በቀላሉ መረዳት እንደማይቻል ያሳያሉ::

ይህንን የቴክኖሎጂ ተፅዕኖ ካስተዋልን አንድ ሕፃን ብዙ እናት፣ ብዙ አባት ሊኖረው የሚችልበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል:: ሔርናን ኤፍ ኮራል የተባሉ የቺሊ የቤተሰብ ሕግ ምሁር ይህንን ሁኔታ ሲያብራሩ እንዲህ ብለው ገልጸውታል::

‹‹A child, at least hypothetically, might have as many as five possible parents, namely the man and women who desire the child’s birth, the donor of the male gamete contributed and the woman who donated the egg to the process and finally the mother who bears the child. Two possible fathers, three possible mothers. Not to mention that the gestational mother may be married and her husband’s paternity presumed, thus raising the number of possible parents to six: three fathers, three mothers››ከፕሮፌሰሩ ንግግር ለመረዳት እንደሚቻለው፣

እናት እውነት አባት እምነትያመጧቸው ሰዎች በሕግ ኃላፊነት ስለሚጣልባቸው የቤተሰብ ሕጉ አባትነትና እናትነት በሕግ የሚታወቅበትን ሁኔታ ያመቻቻል:: የሕጉ አቀራረፅ በዋናነት ዓላማ ያደረገው የሕፃናትን ወላጆቻቸውን የማወቅ መብትን ሲሆን፣ ይህ መብት በሕገ መንግሥትና በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ሰነዶች ዕውቅና የተሰጠው መብት ነው:: የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 36 ‹‹ማንኛውም ሕፃን ወላጆቹን ወይም በሕግ የማሳደግ መብት ያላቸውን ሰዎች የማወቅና የእነርሱንም እንክብኮቤ የማግኘት መብት አለው፤›› በማለት ይህንን መብት ዕውቅና ሰጥቷል:: ዓለም አቀፉ የሕፃናት መብት ኮንቬንሽንም ይህንን መብት በአንቀጹ 7 ዕውቅና ሲሰጥ ‹‹The child has the right to know and be cared for by his or her parents›› በሚል ተመሳሳይ ድንጋጌ ቀርጿል:: ሁለቱም ሕግጋት ወላጅን የማወቅ መብትን ከኃላፊነቱ ጋር በማጣመር ደንግገዋል:: ልጁ ወላጆቹን የሚያውቀው ይንከባከቡት ዘንድ ነው:: ይህ የሕፃናት መብት ለሕፃናቱ የሥነ ልቡና መረጋጋትና ለሌሎች መብቶች አፈጻጸም ቁልፍ ስለመሆኑ መብቱን የሚተረጉሙ ጽሑፎች ያመለክታሉ:: የሕፃናት ወላጆቻቸውን የማወቅ መብት ከስም፣ ከዜግነት፣ ከማንነት፣ ከቤተሰብ ያለመነጠል መብትና ከአሳዳጊዎች ግዴታ ጋር ቅርብ ቁርኝት አለው:: ሕጉ የሕፃኑን ወላጅ የተመለከቱ ድንጋጌዎችን ሲቀርፅ የሕፃኑንና በሕግ ወላጅ የሚባሉትን ሰዎች ጥቅም የማስታረቅ ሥራ ይጠበቅበታል:: በአንድ በኩል ሕፃኑ ያለአባት እንዳይቀር ያሉትን አማራጮች ማስፋት ይጠበቅበታል:: አባትነትን መወሰን እናትነትን የመወሰን ያህል ቀላል ባለመሆኑ ከሕፃኑ ጋር በደም፣ በተፈጥሮ፣ በድርጊት ወዘተ. የሚቀራረበውን ሰው አባት ብሎ የመፈረጅ ውሳኔ ይጠይቃል:: በሌላ በኩል ደግሞ ከሕፃኑ ጋር የወላጅነት ቅርበት (መንፈስ) የሌላቸውን ሰዎች ሁሉ አባት ላለማድረግ ጥንቃቄ ያሻል:: ሕጉ የሕፃኑንና ለወላጅነት የቀረቡ ሰዎችን የተለያዩ ሁኔታዎች መሠረት በማድረግ መስፈርቶች በማውጣት ወላጅነትን ይወስናል:: ጋብቻ፣ አብሮ መኖር፣ ማሳደግ፣ መንከባከብ አባትነትን ለመወሰን ጥቅም ላይ ከሚውሉ መስፈርቶች የተወሰኑት ናቸው::እናት እውነት

ከሕፃኑ አንፃር ከተመለከትን ልጁ እናቱንም

የሚቀበለው በእምነት ነው:: ልጁ ከእናቱ እንደተገኘ እናቱና ሌሎች ሰዎች ካልሆኑ እሱ ምስክርነት መስጠት አይችልም:: ምስክርነት ለመስጠት ከእናት በፊት መገኘት ይጠይቃል:: ይህ ደግም የማይቻል ነው:: ሆኖም በዚህ ርእስ የምንመለከተው እናትነት ለሁሉም የሚታወቅበትንና የሚረዳበትን ነው:: እናት ማን እንደሆነች መልስ የሚገኘው ከተፈጥሮ ነው:: ሕጉም በዚህ ረገድ ከተፈጥሮ መለየት የፈለገ አይመስልም:: በፌዴራል ተፈጻሚ የሆነው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 124 ‹‹እናት የተባለችው ሴት ልጁን የወለደችው በመሆንዋ ብቻ እናትነቷ ይታወቃል፤›› በሚል እናት በኢትዮጵያ ሁኔታ ሁልጊዜም በመውለዷ ብቻ ስለመታወቁ በማያሻማ መልኩ ደንግጓል:: ስለዚህ በእኛ አገር ሕግ እናት የምትባው ልጁን የወለደች በመሆኗ ዘመናዊ ቴክኖሎጂው ወደ አገር ገብቶ በኪራይ ማህፀን ወይም በቤተ ሙከራ ልጅ ቢወለድ እንኳን የእናትነት ብዙህነት አይኖርም:: እናት በተፈጥሮ አርግዛ በመውለዷ እንጂ በሰው ሰራሽ የምትወልድበት ሁኔታ ሒደት በሕጉ አልተመለከተም:: በሌሎች አገሮች ያለው ተሞክሮ ከዚህ ይለያል:: ጽንሱን ለዘጠኝ ወራት ተሸክማ አምጣ የምትወልደው ‹‹አደራ አስቀማጭ እንጂ እናት አይደለችም›› የሚባልበት አሠራር ሊኖር እንደሚችል ያሳያሉ:: ረዳት ፕሮፌሰር መሐሪ ረዳኢ ይህንን ሁኔታ ሲገልጹ፣ ‹‹የቤተሰብ ሕጉ የዘመኑን የሳይንስ ግኝት በሚያስተናግድ መልኩ የተቀረፀ አይደለም:: ምክንያቱም የእናትነት ማረጋገጫው መውለድና መውለድ ብቻ እንደሆነ ደንግጓል:: ዘሩ ከየትም ይምጣ ከየት የወለደችው እናት ነች:: ዘር አቅራቢዋ እስካልወለደች ድረስ በኢትዮጵያ ሕግ እናት የምትሆንበት የሕግ መሠረት የለም፤›› ይላሉ::

በእርግጥ የቤተሰብ ሕጉ አውጪዎች የዘመናዊነትን ሐሳብ ‹‹ስለመወለድ›› ከሚገልጸው የሕጉ ክፍል ማስወገድ አልፈለጉም:: በተወሰኑ ጉዳዮች ዘመናዊው ቴክኖሎጂ የሚስተናገድበት ሁኔታ እንዳለ አመላክተዋል:: ለዚህ አስረጂ የሚሆነው ሕጉ ከመካድ (ልጅነትን ከመካድ) ክስ ጋር በተያያዘ በአንቀጽ 178 መሠረት በባልየው ፈቃድ ልጅ በሰው ሰራሽ ዘዴ የተፀነሰ ከሆነ የመካድ ክስ መቅረብ እንደማይችል ይደነግጋል:: ድንጋጌው ሕግ አውጪው በሰው ሰራሽ ዘዴ የሚፀነስበትን ሁኔታ ግንዛቤ ቢወስድም፣ እናትነትን ወይም አባትነትን በተመለከተ ሊኖረው የሚችለውን

በቴክኖሎጂ አጋዥነት የሚወለዱ ልጆችን በተመለከተ ምናባዊ ግምት ከወሰድን አምስት ወላጆች ሊኖራቸው እንደሚችል ነው:: ልጅ እንዲኖራቸው የፈለጉት ጥንዶች፣ የወንድ ዘርና የሴት እንቁላል የሚሰጡ ግለሰቦችና የመፀነስና የመውለድ ግዴታውን የተሸከመችው ሴት:: የምትወልደዋ ሴት ጋብቻ ያላት ከሆነ ደግሞ በሕግ ግምት ባሏ አባት የሚሆንበት ሁኔታ ስለሚፈጠር የወላጆቹን ቁጥር ወደ ስድስት ሊያሳድገው ይችላል:: ይህ የሚያሳየው በዘመናዊው ዓለም የአባትነት ሁኔታ ብቻ ሳይሆን የእናትነትም ሁኔታ እምነት ሊሆን የሚችልበት ሁኔታ ሰፊ ነው:: የእኛ አገር የሕግ ሥርዓት እንዲህ ዓይነቱን አማራጭ ስለማያካትት አነጋገሩ (አባባሉ) አሁንም ጠቃሚነቱ አያጠያይቅም::

በርእሱ የተገለጸው አባባል መነሻ የሚመነጨው ሕግ ውስብስብ የሆነውን የሰዎች ግንኙነት ለመግዛት ከመቸገሩ (አቅም ከማጣቱ) የሚመነጭ ነው:: እናት የፀነሰችውን ልጅ የወለደችው ስለመሆኗ የአደባባይ ሚስጥር በመሆኑ እናትነቷን ማስረዳት አያስቸግርም:: ዘጠኝ ወር መሸከሟና መውለዷ ለልጇ በቀረበ ለመታወቅ፣ በማያሻማ ምስክርነት እናት ለመባል ያስችላታል:: የአባት ታሪክ ግን ከዚህ የተለየ ነው:: ሁሉም ነገር ከእርሱ በአፍዓ (ከአካሉ ውጭ) የሚደረግ በመሆኑ ሕጉ አባትነትን ለማወቅ የሚያስችሉ ዘዴዎችን አካትቷል:: የልጁ አባትነት በሕጉ ግምት፣ ወይም በአባቱ ፈቃደኝነት (መቀበል) ወይም እንደሁኔታው በፍርድ ቤት የሚታወቅ ነው:: በዚህ ጽሑፍም የምንመለከተው ይህንኑ አባትነትን የመወሰንን ፈተና ይሆናል:: በዚሁ መሠረት ሕጉ ያስቀመጣቸውን እናትነትና አባትነት ለማወቅ የሚያስችሉ ዘዴዎችን በመመለከት በተግባር በተለይ አባትነትን በመወሰን የሚስተዋሉ አከራካሪ ነጥቦችን እንመለከታለን:: የጽሑፉ ዓላማ ኅብረተሰቡ ስለ አባትነት አወሳሰን በሕጉ የተቀመጡትን ደንቦች እንዲያውቅ ማስቻል በመሆኑ፣ አልፎ አልፎ ካልሆነ በቀር አከራካሪ ሙያዊ ጭብጦች ላይዳሰሱ ይችላሉ:: ወላጅን የማወቅ መብት

አባትነትና እናትነትን የተመለከቱ ድንጋጌዎች በቤተሰብ ሕጉ የተካተቱ ጽንሰ ሐሳቦች ናቸው:: ልጆች የጋብቻ ውጤቶች በመሆናቸው፣ በጋብቻ ካልተፈጠሩም ወደ እዚህ ዓለም ያለፍላጎታቸው

Page 35: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 35 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታ

ወቂያ

የተሽከርካሪዎች የጨረታ ማስታወቂያ

የሜታ ሠራተኞች ማኅበራዊ ዋስትና አክሲዮን ማህበር እየተገለገለባቸው ያሉትን ዘመናዊ

ተሽከርካሪዎቹ በዝግ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ 1. በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ማናቸውም ተጫራቾች ተሽከርካሪዎቹ ባሉበት

ሀብተጊዮርጊስ በሚገኘው የአክሲዮን ማህበሩ ጽ/ቤት ዘወትር በሥራ ሰዓት በመገኘት

እስከ የካቲት 12 ቀን 2005 ዓ.ም. ማየት ይችላሉ፡፡ 2. ስለ ተሽከርካሪዎቹ አሻሻጥ የተዘጋጀውን ዝርዝር የያዘ ፎርምና ዝርዝር ሁኔታ

የማይመለስ ብር 100.00 በመክፈል እስከ የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም. ሀብተጊዮርጊስ

ድልድይ በሚገኘው የአስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ዋና ክፍል በመቅረብ የጨረታ

ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡ 3. ተጫራቾች መግዛት የሚፈልጓቸውን የእያንዳንዱን ተሽከርካሪዎች ዋጋ በስም በታሸገ

ኤንቬሎፕ በሥራ ሰዓት እስከ የካቲት 19 ቀን 2005 ዓ.ም. ድረስ የአክሲዮን ማህበሩ ጽ/

ቤት ማቅረብ ይችላሉ፡፡ 4. ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ተሽከርካሪ የመነሻ ዋጋ ብር 10% /አስር በመቶ/ የጨረታ

ማስከበሪያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ CPO ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ 5. በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ገንዘብ ወዲያውኑ የሚመለስላቸው ሲሆን

ለአሸናፊዎቹ ካሸነፉበት ዋጋ ላይ ይታሰብላቸዋል፡፡ 6. የሚሸጡት ተሽከርካሪዎች ላይ የሚፈለግ ቀረጥ ታክስና ውዝፍ ግብር ቢኖር አክሲዮን

ማህበሩ ይሸፍናል፡፡ ከተሽከርካሪው የስም ዝውውር ጋር በተያያዝ ወጪውን ገዢው

ይሸፍናል፡፡ 7. ተጫራቾች በጨረታ ያሸነፉትን ተሽከርካሪ ሙሉ ክፍያ በ5 ቀናት ውስጥ መክፈል

ይኖርባቸዋል፡፡ ክፍያውን ካልፈፀመ ተጫራችነታቸው ተሰርዞ ገንዘቡ ለአክሲዮን

ማህበሩ ገቢ ይሆናል፡፡ 8. ሌሎች ተጫራቾች ባቀረቡት ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ ክልክል ነው፡፡ 9. አክሲዮን ማህበሩ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ

መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 10. ጨረታው የካቲት 20 ቀን 2005 ዓ.ም. ከጠዋቱ 4 ሰዓት ተጫራቾች ሕጋዊ ወኪሎች

በተገኙበት ኃ/ጊዮርጊስ በሚገኘው የአክሲዮን ማህበር መዝናኛ ክበብ አዳራሽ ይከፈታል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ በስ.ቁ. 0912 06 80 99 በመደወል ወይም በግንባር መረጃ ማግኘት

ይቻላል፡፡

የሜታ ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አክሲዮን ማህበር

የጨረታ ማስታወቂያሱር ኮንስትራክሽን ኃላ.የተ.የግ.ማህበር ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የሲቪል ኢንዱስትሪያል ፈንጂዎች፡-

S.No. Description UOM Qty

1 Civil Explosive Superdyne 65x540mm

kg 80,000

2 Civil Explosive ANPP Kg 379,049.00

3 Civil Explosive Detonating Cord 10G/M

Mt. 379,049.00

በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ይህንን ማቅረብ የሚችሉ፡-

1. ተጫራቾች ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር አጠናቀው የከፈሉና የቫት ተመዝጋቢ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡

2. ተጫራቾች የጨረታ ዝርዝር መግለጫ የያዘውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ የካቲት 11/2005 ዓ.ም ዘወትር በስራ ቀናት በድርጅቱ ግዥ ክፍል በመቅረብ መውሰድ የምትችሉና ጨረታው የሚዘጋው የካቲት 11/2005 11፡30 ነው፡፡

3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 100,000 /አንድ መቶ ሺህ ብር/ በጥሬ ገንዘብ፣ በባንክ የተመሰከረ ቼክ /ሲፒኦ/ ወይም ባንክ ጋራንቲ ከጨረታው ፓስታ ጋር ማስገባት አለባቸው፡፡

4. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት የካቲት 12/2005 ዓ.ም ጧት 3፡00 ይከፈታል፡፡

5. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ/ በመክፈል ከ2ተኛ ፎቅ ግዥ ክፍል መውሰድ ይችላሉ፡፡

6. ተጫራቾች ዋናውን እና ቅጂውን ቴክኒካልና ፋይናንሽያል ፕሮፓዛል ለየብቻው ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

7. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

አድራሻ፡- ከደምበል ወደ መስቀል ፍላወር በሚወስደው መንገድ ከድሪምላይነር ሆቴል ፊት ለፊት፡፡

ስልክ ቁጥር 011-4-66 83 56

ውጤት በይዘቱ ለመደንገግ አልፈለገም:: የዚህን አመክንዮ ረዳት ፕሮፌሰር መሐሪ በመጽሐፋቸው ሲጠቁሙ፣ ይህ ጉዳይ በሕግ ደረጃ ከመቀረፁ በፊት የፖሊሲ ውሳኔና አቋም ሊወሰድ እንደሚገባ ይገልጻሉ::አባት እምነት

ማንነትን በማወቅ ረገድ አስቸጋሪ የሚሆነው ከእናት ይልቅ የአባት እንደሆነ ይታመናል:: ዘመናዊ ቴክኖሎጂ አባትነትን ለመወቅ የሚረዳ ዘዴ ቢኖረውም በአገራችን ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ችግሩን ሊቀርፈው አይችልም:: ቴክኖሎጂው ተደራሽነቱ አስቸጋሪ በመሆኑ የሚጠይቀውም ገንዘብ ውድ ከመሆኑ የተነሳ ለአብዛኛው የኅብረተሰባችን ክፍል ረብ ላይኖረው ይችላል:: ሕጉ ግን ዘመናዊውን ዘዴ ጨምሮ የተለያዩ አባትነትን ለማወቅ የሚያስችሉ ሁኔታዎችን በዝርዝር ደንግጓል:: በቤተሰብ ሕጉ መሠረት አባትነት በሦስት መንገዶች ሊታወቅ ይችላል:: እነዚህ መንገዶች ከሕጉ ግምት፣ አባትነቱን ከሚቀበለው ሰው ፈቃድ ወይም ከፍርድ ቤት ሊመነጭ ይችላል:: አባትነት በሕግ ግምት

የቤተሰብ ሕጉ በአንቀጽ 125(1) እና 126 አባትነት በሕግ ግምት የሚወሰንበትን ሁኔታ ይደነግጋል:: በዚሁ መሠረት ልጅ በሚፀነስበት ወይም በሚወለድበት ጊዜ በእናትዬዋና በአንድ ወንድ መካከል በሕግ የታወቀ ግንኙነት ካለ የልጁ አባት ነው የሚባለው ባልዬው ነው:: ስለዚህ በሕግ ግምት አባት ለመባል አንድ ሰው በሕግ በታወቀ ግንኙነት ፀንቶ ባለበት ወቅት የእሱ ሚስት ወይም ጓደኛ (Partner in irregular union) ልጅ ልትፀንስ ወይም ልትወልድ ይገባል:: በሕግ የታወቀ ግንኙነት ጋብቻንና ጋብቻ ሳይፈጸም እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖርን (Irregular union) የሚያመለክት ሲሆን፣ ግንኙነቱ መኖሩን የቤተሰብ ሕጉ ባስቀመጣቸው የተለያዩ ዘዴዎች ማስረዳት ይቻላል:: ሌላው ግን አባትነቱን በመወሰን ረገድ ከግንኙነቱ መኖር በተጨማሪ የእርግዝናው ወቅት አስፈላጊ ነው:: ልጅ ጋብቻው ከተፈጸመ ወይም ግንኙነቱ ከተመሠረተ ከ180 ቀናት በኋላ ወይም ጋብቻው በፈረሰ ወይም ግንኙነቱ ከተቋረጠ በ300 ቀናት ውስጥ የተወለደ ከሆነ ልጁ በጋብቻው ወይም በግንኙነቱ ውስጥ እንደተፀነሰ ይቆጠራል::

ይህ አቆጣጠር ሕግ አውጪው አንድ ልጅ መቼ እንደተፀነሰ ለማወቅ ከተወለደበት ቀን ወደ ኋላ በመቁጠር ማወቅ እንደሚቻል ግንዛቤ ወስዶ ሕጉን ደንግጓል:: ሕጉ ባስቀመጠው ጊዜ የእርግዝናው ጊዜ የማይወድቅ ከሆነ ግን የአባትነት እምነት ሊፈተን ይችላል:: በዚህ ጊዜ አባት ከእርሱ እንዳልተፀነሰ እርግጠኛ ከሆነ አባትነቱን መቃወም የሚችለው የመካድ ክስ በማቅረብ ብቻ ነው:: የቤተሰብ ሕጉ በአንቀጽ 168 ‹‹የልጁ አባት ነህ ተብሎ በሕግ አባትነት የሚሰጠው ሰው ልጁ ከመወለዱ በፊት በ300ኛውና በ180ኛው ቀናት መካከል ባለው ጊዜ ውስጥ ከልጁ እናት ጋር የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት ላለመፈጸሙ በማያጠራጥር ሁኔታ ያስረዳ እንደሆነ የተባለው ልጅ ልጄ አይደለም ለማለት ይችላል፤›› በማለት ደንግጓል:: በሕግ የልጁ አባት ነህ የተባለው ሰው የዚሁ ልጅ አባት ሊሆን አለመቻሉን በማያጠራጥር አኳኋን በማስረዳት ለመካድ እንደሚችል ሕጉ በግልጽ ይደነግጋል:: ይህንን ጉዳይ ረዳት ፕሮፌሰር መሐሪ ረዳኢ በምሳሌ ሲያስረዱ እንዲህ ይላሉ::

‹‹አንድ ባል ለሁለት ዓመት የከፍተኛ ትምህርት ለመከታተል ከኢትዮጵያ ውጭ ይሄድና ትምህርቱን አጠናቅቆ ሲመለስ ሚስቱ ከሦስት ወር በፊት ተገላግላ የሦስት ወር ሕፃን ታቅፋ ትጠብቀዋለች:: በዚሁ ሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ሚስት ባለቤትዋን ለመጎብኘት ወደ ውጭ አገር አለመሄድዋ ከታመነና ባልም በትምህርቱ መካከል ወደ አገር ቤት አለመምጣቱ ከታመነ ሕፃኑ የባልየው ልጅ ሊሆን አይችልም:: ምክንያቱም በመጨረሻ የመለያያቸው ቀን እርግዝና ተፈጥሯል ብንል እንኳን እርግዝናው በምንም መልኩ አንድ ዓመት ከዘጠኝ ወር ሊቆይ ስለማይችል ነው::››

በእንዲህ ዓይነት ወቅት ልጁ የተወለደው ጋብቻው ፀንቶ ባለበት ወቅት በመሆኑ ሕጉ ባልዬውን የሕፃኑ አባት እንደሆነ ግምት ይወስዳል:: ሆኖም ባልዬው ሁኔታውን ለፍርድ ቤት በማስረዳት የመካድ ክስ አቅርቦ ከተሳካለት ግን አባትነቱን ሊክድ ይችላል::

አባትነት ሊካድ የሚችልበት ሌላው መንገድ ደግሞ በቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 172 መሠረት ነው:: ይህ የሚሆነው በፍርድ ቤት ፈቃድ መሠረት ሲሆን ፍርድ ቤቱ ክሱን እንዲቀበል የሚያደርገው በቂና አስተማማኝ ከሆነ መረጃ የሚመነጭ የህሊና ግምት ወይም ከባድ ምልክት ሲኖር ብቻ ነው:: እንዲህ ዓይነት ሁኔታዎች በሳይንስ የተደገፉ መረጃዎች ሊሆኑ ይችላሉ:: ለምሳሌ ባል መውለድ የማይችል መካን መሆኑ በሐኪም ከተረጋገጠ በኋላ ሚስቱ አርግዛ ከወለደች ወይም በዘመናዊ የዲአንኤ (DNA) ምርመራ የሕፃኑና አባት ነው የተባለው

ሰው ባዮሎጂካዊ አፈጣጠር የማይመሳሰል ሆኖ ከተገኘ የመካድ ክስ ለማቅረብ የፍርድ ቤት ፈቃድ ለማስገኘት እንደሚያስችል አንዳንድ የሕግ ምሁራን ይገልጻሉ፤ የፍርድ ቤቶችም ተሞክሮ ያሳያል:: ሌላው ሴቲቱ በሰውዬው አባትነት ላይ ጥርጣሬ በማያሳድር አኳኋን የልጁን መወለድ ወይም እርግዝናዋን ከሰውዬው ከደበቀችበት ድርጊት ሊመነጩ ይችላሉ:: ከዚህ ውጭ እናቲቱ በባልዬው ላይ ያደረገችው የሴሰኝነት (የዝሙት) ሥራ ወይም ልጁ የሌላ ሰው ለመሆኑ የምትሰጠው የእምነት ቃል ብቻ እንደ ከባድ ምክንያት ሊቆጠሩ እንደማይችሉ የቤተሰብ ሕጉ በአንቀጽ 173 ደንግጓል::

ሕጉ የመካድ ክስ በተቻለ ፍጥነት መቅረብ እንደሚገባው ይደነግጋል:: በአንቀጹ 176 መሠረት ‹‹የእኔ ልጅ አይደለም የሚል የመካድ ክስ የልጁን መወለድ ካወቀበት ወይም ማወቅ ከሚገባው ቀን በ180 ቀናት ውስጥ መቅረብ አለበት::›› የጊዜውን ገደብ አመክንዮ ሲገልጹ ረዳት ፕሮፌሰር መሐሪ፣ ‹‹ሕፃኑ የአባቱ ማንነት የማወቅ መብቱ ላልተወሰነ ጊዜ በእንጥልጥል መቆየቱ ተገቢም ፍትሐዊም ስለማይሆን ነው፤›› ይላሉ::

ስለዚህ የመጀመሪያው አባትነትን የማወቂያ ዘዴ የሕግ ግምት ሲሆን፣ ይህ ግምት በልዩ ሁኔታ ልጅን በመካድ ሊፈርስ እንደሚችል መታወቅ አለበት:: የሕጉ ግምት መሠረት የሚያደርገው በጋብቻ ውስጥ ያለን መተማመን ሲሆን፣ ልጅ የመካድ ሥርዓት ደግሞ ሕጉ የሚጠብቀው መተማመን በጎደለ ጊዜ የሚፈጠሩ ሁኔታዎችን ለማስተካከል ዓላማ ያደረገ ነው:: የመካድ ክስ በአንድ በኩል የልጁን ጥቅም በሌላ በኩል ደግሞ በሕግ ግምት አባት ነህ የተባለውን ሰው ጥቅም የሚያገናዝብ ነው:: የሕግ ግምቱ ልጁ ያለአባት እንዳይቀር ሰፋ ያሉ መንገዶችን ሲያመቻች የመካድ ክስ ደግሞ ተፈጥሮአዊ አባት ያልሆነ ሰው በሕግ ግምት አባትነት እንዳይጫንበት መፍትሔ ይሰጣል:: አባትነትን በመቀበል

በሕግ የታወቀ ግንኙነት በሌለበት ሁኔታ የሚወለዱ ልጆች አባትነት የሚወሰነው አባትነትን በመቀበል ወይም በፍርድ ቤት ሲነገር ነው:: በሴቲቱና በሰውዬው መካከል በሕግ የታወቀ ግንኙነት ሳይኖር አባትዬው ልጄ ነው ሲል በመቀበሉ ሊታወቅ ይችላል:: አባትነትን መቀበል ከሰውዬው ፈቃድ የሚመነጭ እንደመሆኑ በአባትዬው ብቻ የሚፈጸም ነው:: ቃሉን ሌላ ሰው እንዲሰጥ ማድረግ የሚችለው በፍርድ ቤት የፀደቀ ልዩ የውክልና ሥልጣን በመስጠት ብቻ ነው::

ልጅነትን የመቀበል ሥርዓት በቃል ብቻ

የሚፈጸም አይደለም:: የአባትዬው ፈቃድ የፀናና የማይሻር መሆኑን ለማረጋገጥ ሕጉ አባትዬው ቃሉን በክብር መዝገብ ሹም ፊት እንዲሰጥ ወይም በጽሑፍ በሚያደርገው ኑዛዜ ወይም በሌላ በማናቸውም ሥልጣን በተሰጠው ባለሥልጣን በተረጋገጠ ሰነድ እንዲቀበል ያስገድደዋል::

አባትነትን መቀበል በሰውዬው ድርጊት ብቻ የሚፀና አይደለም:: የእናቲቱም አስተዋጽኦ ወሳኝ ነው:: በዚሁ መሠረት እናት አባትነትን ለመቀበል የተዘጋጀውን ግለሰብ የተሻለ ስለምታውቀው ምስክርነቷ ወሳኝ ነው:: የልጁ አባትነት በአባት ብቻ ሳይሆን በእናትም ሊታመን ይገባል:: የልጁ እናት የተቀባዩን አባትነት እውነትነት ያለው መሆኑን ካላመነች በስተቀር አባት ልጄ ነው ሲል የሚሰጠው ቃል በሕግ ፊት ውጤት አይኖረውም:: (አንቀጽ 136) እናት ከሞተች ወይም ፈቃድዋን ለመግለጽ የማትችል ከሆነች ደግሞ የእምነት ቃሉ ከልጁ እናት ወላጆች በአንደኛው ሊሰጥ ይችላል:: እነርሱም ከሌሉ ወደላይ በሚቆጠር ሌላ ወላጅ ሊሰጥ ይችላል:: ልጅነትን የመቀበሉ ተግባር የተከናወነው ልጁ አካለ መጠን ከደረሰ በኋላ የሆነ እንደሆነ ልጁን መቀበሉ ውጤት የሚያስገኘው ልጁ አባትነቱን የተቀበለ እንደሆነ ነው::

አባትነት በሕግ ግምት ካልታወቀ በመቀበል (Acknowledgment of paternity) የሚታወቅ ይሆናል:: በሁለቱም አባትነትን ማወቅ ካልተቻለ ሕጉ የሚያስቀምጠው የመጨረሻ አማራጭ አባትነት በፍርድ ቤት እንዲታወቅ ማድረግ ነው:: ከሁለቱ አንፃር አባትነት በፍርድ ቤት የሚታወቅበት ሁኔታ ሰፋ ያሉ ምክንያቶችን ስለሚዘረዝር፣ ሰፋ ያለ ሙግት የሚቀርብበትና በተግባርም አከራካሪ ነው:: በዚህ በሦስተኛውና የመጨረሻው አባትነትን የመወሰን ሥርዓት ፍርድ ቤቶች ልጁ ያለአባት እንዳይቀር፤ ማንኛውም መንገደኛ ወይም በጎ አድራጊ አባት እንዳይባል ጥንቃቄ የሚያደርጉበት ነው:: በዚህ ረገድ ሕጉም አተገባበሩም የተወሰኑ ችግሮች ይስተዋሉበታል:: በሚቀጥለው ሳምንት እነዚህን ነጥቦች የምንዳስስ ይሆናል::

ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል::

Page 36: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 36 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ማስታ

ወቂያ

INVITATION TO BID FOR THE SECOND TIME

1. The Ethiopian Red Cross Society (ERCS) invites sealed bid from eligible, qualified contractors of WWGC-6 and above with trade license and registration certificate from the Ministry of Water Resources valid for the current year for furnishing the necessary labor, materials and equipment for the construction and completion of Boji earthen dam rehabilitation project at Moyale Somali.

2. Interested eligible bidders can purchase a complete set of bidding document against a non-refundable payment of ETB 200 (Two hundred birr) from ERCS National Head Quarters Purchasing unit; Addis Ababa, Tel. 0115549471. Additional set of bid document may be purchased at the same price.

3. All tenders must be submitted to Ethiopia Red Cross Society along with a Bid Security (Bid Bond) in acceptaBle formS cpo Specified in the Bidding data Sheet amounting to 2% of the Bid offer, on separate envelope.

4. financial offer shall be produced in separate wax sealed envelopes labelled as original and copy. technical offer shall be made in a separate third wax sealed envelope clearly labelled as technical offer. The three envelopes shall then be sealed in and signed, sealed and waxed outer envelope, addressed to Ethiopia Red Cross Society whose address is mentioned below.

5. Bid will be closed on the 10th working day of this announcement which is Feb22,2013 at 12;00 am local time and will be open on the same day at 2:00pm local time in the presence those bidders on their authorized representatives who are willing to attend the event at ERCS- Head Quarters in Addis Ababa

6. The bid Bidders are advised to read bidding document thoroughly in order to fill all the necessary details requested in the bid document.

7. The construction of the works shall be completed within a maximum of 60 (Sixty) calendar days starting from the commencement of the work Bidders are required to fill all the necessary details requested in the bid document.

8. Ethiopia Red Cross Society reserves the right to accept or reject any or all bids without fixing any reason thereof.

Address:Ethiopian Red Cross Society Head Quarter

tel. 011-554-94-71 or 011-553-76-40p.o.Box: 195

addiS aBaBa, ethiopia

እ ኔ እ ም ለ ውበተስፋዬ ንዋይ

መነሻ

የአገራችንን የአጭር ጊዜ ታሪክ በጥልቀት ለሚመለከት ታዛቢ እጅግ በጣም የሚያሰቅቅና አፍ የሚያሲዘን ጉዳይ የተወሰኑ የዕውቀት ገመዶች የጥፋት ብርሃን ማስተላለፊያ በመሆናቸው ነው:: በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ በተጨባጭ እውነት ላይ የተመሠረተ ሚዛናዊ ትንታኔ በበቂ ሁኔታ የተሰጠ አይመስለኝም:: ይህ መሠረታዊ ሀቅ ንቅንቅ ወደማይል አለትነት የደረሰ ይመስላል:: ይህን ችግር ከመሠረቱ የሚፈጥረው ደግሞ “የኢትዮጵያ ታሪክ” ተብሎ በጽሑፍም ሆነ በቃል የሚተረተረው ሐሳብ እውነታን መሠረት ያላደረገ መሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ ለፖለቲካ፣ ግብዓትና ዓላማ ተብሎ የቀረበ ወይም እየቀረበ ያለ መሆኑ ነው:: ይህ መምታታት አገሪቷን አንድ አስማሚ የሆነ ታሪክ የሌላት የሚያስመስላት ብቻ ሳይሆን የግልን የፖለቲካ ዓላማ ማካሄጃ መድረክ እንዲሆን ዕድል ፈጥሯል::

የአገራችን የታሪክ ሒደትና ውጤት ላይ በእውነት (Authentic) ላይ የተመሠረተ የታሪክ ዕድገት በአገሪቷ ተመዝግቦ ያለመኖሩ አንድ ችግር ሆኖ፣ እነዚህ በእውነት ላይ ያልተመሠረቱ ታሪኮችን ከእውነት በላይ አድርጎ በመውሰድ ምሁራዊ ትንታኔዎችን በእነሱ ላይ መስጠት ሌላው አበሳጭ ጉዳይ ነው:: ይህንን እንድል ያደረገኝ በቅርቡ በገበያ ላይ ውሎ የተሰራጨውን “መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ” የሚል ጥራዝ አንብቤ ከጨረስኩኝ በኋላ ነው:: ይህ ጥራዝ የተጻፈው መስፍን ወልደማርያም በሚባሉ ግለሰብ (እኚህ ግለሰብ ፕሮፌሰር የሚል ማዕረግ የደረቡ ቢሆንም በመጽሐፉ ላይ ስላወለቁት እኔም ትቼዋለሁ) ሲሆን፣ በዚህ አጭር በማይባል ጥራዝ ጸሐፊው ያሉዋቸውን አስተሳሰቦችና ከአስተሳሰቦቹ ጀርባ ያሉትን መነሻዎች በሚገባን ቋንቋ አቅርበዋል:: በዚህ ጥራዝ የታጨቁት ሐሳቦች ዘርፈ ብዙ ቢሆኑም፣ በዚህች አጭር ጽሑፍ ለመመልከት የምፈልገው በጥራዙ ውስጥ በአሁኑ ወቅት ያለውን የፖለቲካ ሁኔታ በሚያጣፍጡ ወይም በሚመርዙ ጉዳዮች ላይ ብቻ ነው::

ኢትዮጵያ ማን ነች? ማን ነበረች? ምን ዓይነት ሥልጣኔ ነበራት?

ኢትዮጵያ ማን ነች? ለሚለው ጥያቄ መልሱ ምናልባትም አገር ነች ይሆናል:: ጥያቄው በአዕምሮ ውስጥ ያለውን የሐሳብ ማስተላለፊያ ገመድ የሚያጨማትርና የሚያጨናንቅ ደረጃ ላይ የሚደርሰው፣ ኢትዮጵያ ምን ዓይነት አገር ነበረች? የሚለውን ጥያቄ ስናክልበት ነው:: ጡዘቱን ለመጨመር ኢትዮጵያ በታሪክ የሚታወቅ ምን ዓይነት ሥልጣኔ ነበራት? የሚለውን እንጨምርበት:: ከዚህ በላይ የተጠቀሰው ጥራዝ

ስለከሸፈው “መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ” ጥራዝ አንዳንድ ነጥቦች

ኢትዮጵያ የብዙ ዘመናት ታሪክ ባለቤት መሆኗን በመግለጽ ሥልጣኔዎቻችን ወይም ጥበቦቻችን አሁን ያሉበትን ደረጃ እንካችሁ ይሉናል:: እንዲህ በማለት፣ “የአክሱም ሐውልት፣ የላሊበላ ከድንጋይ የተፈለፈሉ ቤተ ክርስቲያኖች፣ የጎንደር ቤተ መንግሥት የሠራ ሕዝብ ከደሳሳ ጎጆ ጋር ተቆራኝቶ ለብዙ ምዕት ዓመታት የቆየበት ምክንያት ምንድነው? የድንጋይ ሥራ ጥበብ ከሽፎ የቀረበት ምክንያት ምንድነው?” ገጽ (9) እያሉ ይቀጥላሉ::

ጸሐፊው እነዚህን መሰል ጎርጓሪ የቁጭት ጥያቄዎችን ከደረደሩ በኋላ መሠረታዊ የሚሏቸውን ምክንያቶች በገጽ (23) ላይ ወደ መደርደር ገብተዋል:: ከእነዚህ ምክንያቶች በመጀመሪያ ረድፍ ላይ የመቀመጥ ዕጣ ፈንታ ያጋጠማቸው ከሕግና ሥርዓት አንፃርና በአስተዳደር በኩል ያሉትን ችግሮች ነው:: መፍትሔ ብለው የሚያስቀምጧቸውም ሐሳቦች ከእነዚሁ ጋር የተያያዙ ናቸው::

ጸሐፊው “ኢትዮጵያ” የሚለውን “ታላቅ” ስም ወስደው በብዙ የጥራዙ ገጾች የደረደሩትና የኢትዮጵያ ታሪክ ከሸፈበት ብለው የገለጹት “የድንጋይ ሥራ ጥበብ” ላይ ብቻ የታጠረ ነው:: ይሁንና ጸሐፊው በጥራዛቸው ከገለጹት “የድንጋይ ሥራ ጥበብ” ታሪክ መክሸፍ አንፃር በመጀመሪያ ሌሎች የጥበብ ወይም የሥልጣኔ ውጤቶች አሁንም ሆነ ድሮ በምናውቃት ኢትዮጵያ ውስጥ ስለመኖራቸው ወይም አለመኖራቸው ያለመግለጻቸው፣ ለጥራዛቸው የመጀመሪያው የክሸፈት አረንጓዴ ምልክት መሆኑ ነው:: ይህም ማለት “የድንጋይ ሥራ ጥበብ” ታሪክ ከሸፈ ብለው የሚገልጹት ታሪክ (ከሸፈ ብለን መስማማት ከቻልን) በሰሜኑ የአገራችን ክፍል የሚገኘውን ጥበብ ነው:: ስለዚህ የሰሜኑን “የድንጋይ ሥራ ጥበብ” ታሪክ መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ መክሸፍ መመልከት የተንሸዋረረ ምሁራዊ የታሪክ ትንታኔ ከማለት ውጭ ሌላ ማለት እጅግ አስቸጋሪ ይሆናል::

ሀቁን ወደ ምድር ለማውረድ ያህል እውነት የትኛው የኢትዮጵያ ታሪክ ነው የከሸፈው? የኢትዮጵያ ታሪክ “የድንጋይ ሥራ ጥበብ” ታሪክ ብቻ ነው ወይ? የኢትዮጵያ ታሪክ ብለው ጸሐፊው የበየኑትን ሥልጣኔስ ማን ነው ያከሸፈው? መክሸፉን ከመበየን በፊት አክሻፊውን ማሳየት ይገባል:: በሌላ በኩል የኢትዮጵያን ታሪክ ጸሐፊው እጅግ ከማጥበባቸው የተነሳ ከከሸፈው “የድንጋይ ሥራ ጥበብ” ታሪክ አንፃር ብቻ

ቃኝተውታል:: ጸሐፊው በአገራችን የሰሜኑ ክፍል የነበሩት እሳቸው “የድንጋይ ሥራ ጥበብ” ታሪኮች ብለው የገለጹዋቸው ሥልጣኔዎች መክሸፋቸውን ሲገልጹ፣ በአገሪቱ የነበሩ ሌሎች “የጥበብ ታሪኮች” ለምሳሌ የኦሮሞ የገዳ ሥርዓትና ሌሎችም ስለመክሸፋቸውና አለመክሸፋቸው የነገሩን አንድም ነገር የለም:: ይህ በዚህ ጥራዝ ሳይታቀፍ ለምን ታለፈ? ወይስ የኦሮሞ፣ የወላይታ፣ የሲዳማና የመሳሰሉት የጥበብ/የሥልጣኔ ታሪኮች እንደ ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ታሪኮች አይታዩም? ጥራዙ ለዚህ መልስ የለውም:: ይህም ጥራዙን የከሸፈ ያስብለዋል::

የትኛውን ታሪክ ጸሐፊ/ተንታኝ እንመን?

ይህን ነጥብ ይበልጥ ለማብራራት ከጥራዙ የተወሰኑ ሐሳቦችን እንምዘዝ::

“የታሪክ ባለሙያው የአንድን ኅብረተሰብ ወይም ሕዝብ ታሪክ በሚመዝንበትና የታሪኩን አካሄድ በሚገልጽበት ጊዜ እሱ ራሱ የት ሆኖ ነው? መጀመሪያውኑ እሱ ራሱ የታሪኩ ባለቤትና የታሪኩ ምንጭ የሆነው ኅብረተሰብ ወይም ሕዝብ ክፍል አካል ይሆናል::” ገጽ (53)

“በታሪክ ትምህርት በኩል የኢትዮጵያ ሕዝብ አልታደለም፣ የጥንቶቹ ታሪክ ጸሐፊዎች ታሪክን የሚጽፉበት ቋንቋ ግዕዝ ነበር፣ ሁለተኛም ንጉሠ ነገሥቶችን ለማወደስ ነበር:: ስለዚህ በቋንቋውም ሆነ በዓላማው የነገሥታቱ ታሪክ /ዜና መዋዕል/ የተጻፈው ለሕዝቡ አልነበረም:: ዓላማውም ውስን በመሆኑ ቋንቋውም ውስን ነበርና የኢትዮጵያ ሕዝብ ታሪክ በገዛ ራሱ ታሪክ ጨለማ ውስጥ ነበር ለማለት ይቻላል::” ገጽ (76)

ኢትዮጵያውያን ታሪካቸውን ለማወቅ እጅግ በጣም የሚጓጉ ማኅበረሰቦች ናቸው:: ይህም የመነጨው አገራችን እውነተኛ (Authentic) ታሪክ ያልነበራት ስለሆነ ነው የሚለውን የጸሐፊውን ዕይታ ይህ ጸሐፊም በመጠኑ የሚቀበለው ነው:: ጥያቄው ግን እውነተኛ ያልሆነው የኢትዮጵያ ታሪክ የትኛው ነው? በሚለው ጥያቄ ላይ የሚሰጠው ትንታኔ ነው:: ጸሐፊው በመጀመሪያው ሐሳብ ላይ በግልጽ እንዳስቀመጡት የታሪክ ባለሙያ የመወሰን ወይም አገር የመቅረፅ ሥልጣኑን በመጠቀም የማኅበረሰቡም አባል በመሆኑ ለማኅበረሰቡ መሥራት እንዳለበት አስቀምጠዋል:: ይመስለኛል የእርስዎ የታሪክ ትንታኔም ለታሪክ ጸሐፊው ያስቀመጡትን ገመድ (ለማኅበረሰቡ የመሥራት) በጥሰው የወጡ አይመስለኝም:: ምክንያቱም በኢትዮጵያ የነበሩ የታሪክ

የግዥ ጨረታ ማስታወቂያድርጅታችን ከዚህ በታች በሶስት ምድብ ተከፋፍለው የቀረቡ የተለያዩ ሸቀጦችን ከአገር ውስጥ አምራቾችና አከፋፋዮች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡

ምድብ ሀ. የህንጻ መሣሪያዎች1. ES 95:2001 የሚያሚላ የቆርቆሮ ምስማርና2. ES 95:2001 የሚያሟላና ውፍረቱ ከ3 ሚ.ሜ እስከ 15 ሚ.ሜ የሆነ የግድግዳ ምስማር፣ 3. ES ISO 8179-1 እና 2:2005 የሚያሟላና ስፋቱ ከ1/2 እስከ 6 ኢንች የሆነ የውሀ ቧንቧ፣4. ES 3051 የሚያሟላ ቼይን ሊንክ፣5. ES 94:2012 የሚያሟላ በርብድ ዋየር፣6. ES ISO 2408:2007 የሚያሟላ የማሰሪያ ሽቦ፣7. ES 3742:2012 የሚያሟላ የቤት ክዳን ቆርቆሮ፣ 8. ደረጃቸውን የጠበቁና ዝርዝራቸው በጨረታ ሠነድ ውስጥ የተገለፁ ልዩ ልዩ የብረታብረት

ውጤቶች፣

ምድብ ለ. የምግብ ሸቀጦች1. ES 1055:2005 የሚያሟላ ማካሮኒ፣ 2. ደረጃውን የጠበቀ ሻይ ቅጠል

ምድብ ሐ. ጠቅላላ ሸቀጣ ሸቀጥ1. ደረጃቸውን የጠበቁ የፎም ፍራሾችና ትራሶች፣ 2. ደረጃቸውን የጠበቁ የዱቄት ሣሙና፣

በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስና የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሠርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ አምራቾችና አከፋፋዮች በጨረታው መሣተፍ የሚችሉ መሆኑን እየገለፅን፣ ለዚህ የተዘጋጀውን ዝርዝር የጨረታ ሠነድ የማይመለስ ብር 50.00 (ሃምሣ ብር) በመክፈል ከድርጅቱ ግዥ መምሪያ የሀገር ውስጥ ግዥ ዋና ክፍል በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ፡፡

ተጫራቾች የጨረታ መወዳደሪያ ዋጋቸውንና የሕጋዊነት ማረጋገጫ ሠነዶችን ኮፒ ከ1% የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ጋር በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ እስከ የካቲት 13 ቀን 2005 ዓ.ም. ከቀኑ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብ ይችላሉ፡፡ ጨረታው በዕለቱ በ4፡00 ሰዓት ፈቃደኛ የሆኑ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡

ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 011 155 0700/011 111 1930/011 111 4683/ 011 111 4542 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡

የሸቀጦች ጅምላ ንግድና አስመጪ ድርጅት ዌብ ሣይት www.mewit.com.et

Page 37: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 37 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1

እ ኔ እ ም ለ ውጽሑፎች (ዜና መዋዕሎች) የኢትዮጵያን ሕዝብ ጨለማ ውስጥ ያደረጉና ለነገሥታት ብቻ የተጻፉ የሕዝብ ታሪክ ያለመሆናቸውን በገለጹበት ብዕር፣ አፍታም ሳይቆዩ የተለያዩ አፄዎችን ዜና መዋዕሎች እንደ እውነተኛ ታሪክ በመውሰድ በመጠኑም ምክንያታዊ ይሆናሉ የሚባሉትን ዘመናዊ የታሪክ ጸሐፊዎችን ያለ ርህራሔ በቀለም አርጩሜ ይገርፏቸዋል:: ለምሳሌ ጸሐፊው የፕሮፌሰር ታደሰ ታምራት “Church and State In Ethiopia” መጽሐፍ በተቹበት ነጥብ ላይ፣ አምደ ፅዮንን “ጀግና” ብለው ካሞገሱ በኋላ እኚህ ንጉሥ በዜና መዋዕላቸው እንዲገባላቸው ያስደረጉትን “እንዘ ንጉሥ አነ ላዕለ ኵሉ ተንባላት ዘምድረ ኢትዮጵያ” በመውሰድ ይህም ማለት “ለክርስቲያኑም ሆነ ለእስላሙ ኢትዮጵያዊ ከአምደ ፅዮን በቀር ሌላ ንጉሥ የለውም ማለቱ ነው፤” በማለት፣ “ኢትዮጵያ አንድ አገር ነበረች ማለት ነው” ብለው ከደመደሙ በኋላ፣ “ታደሰ የእስላም አገረ መንግሥት ወይም የክርስቲያን አገረ መንግሥት የሚለውን ከየት አመጣው?” በማለት የዜና መዋዕሉን ትክክለኛነት በማጠንከር የታሪክ ምሁሩን ትንታኔ አፈር ድሜ ያበሉታል:: ይህ የጸሐፊው ትንታኔና አንድምታ ጸሐፊው ዜና መዋዕሎችን (የግራኝ መሐመድ ዜና መዋዕልን ጨምሮ) ለሚፈልጉት ዓላማ እስካገለገላቸው ድረስ ሲጠቀሙበት ትንታኔያቸው በንጉሥ ተነግሮት ዜና መዋዕልን ከሚደርሰው ጸሐፊ ትዕዛዝ ያልተለዩ መሆናቸውን ነው::

በሌላ በኩል የጸሐፊው የመስመር ዘላቂነት ወይም ኢ-ዘላቂነት ግራ የሚያጋባው ስለ ውጭ አገር የታሪክ ጸሐፊዎች ያላቸው ምልከታ ነው:: ጸሐፊው በጥራዛቸው የኢትዮጵያ ታሪክ ማደግ የጀመረው የውጭ ሊቃውንት መግባት ከጀመሩበት ጊዜ ወዲህ መሆኑን መግለጻቸውን ዘንግተው ይመስል በሌላ ቦታ ደግሞ እንዲህ ይላሉ:: “የውጪ አገር የታሪክ ጸሐፊዎች ኢትዮጵያ በመምጣት የተለያዩ ጥናቶችን የሚያደርጉት ለእንጀራ መብያቸው” ገጽ (59) ሲሉ፣ በሌላ ቦታ ደግሞ “… ስለ ቋንቋዎች፣ ስለዘር፣ ስለባህል፣ ስለታሪክ፣ በጠቅላላ በሕዝቡ መሀል ስላለው የሃይማኖትና ቋንቋ፣ የኑሮና ሌላው ልዩነት ላይ የውጭ አገር ሊቃውንት የሚያተኩሩት ለምንድነው?” (ገጽ 56):: እዚህ ላይ ጸሐፊውን መጠየቅ የምፈልገው እነዚህ የተባሉ ልዩነቶች ላይ የውጭ ሊቃውንት ማተኮራቸውን ለምን ጠሉት? ልዩነቶቹ የሉም ለማለት ነው? ወይስ ልዩነቶቹን ለማጥፋት የተደረጉትን አገዛዛዊ ደባዎችና ወንጀሎች ይፋ ያወጡታል ብለው ፈርተው ነው? ዋናው ነገር የውጭም ሆኑ የአገር ውስጥ ሊቃውንት የኢትዮጵያን ሕዝብ ታሪክ ለማንም ሳይሉ ለእውነት ብለው መጻፋቸው ነው እንደ ነጥብ መወሰድ ያለበት።

ጸሐፊው የውጭ ጸሐፊዎችን ከዚህ በላይ ባለው መልስ ቢተቹዋቸውም ሥራዎቻቸውን እንደ አስፈላጊነቱ በመቀያየር ተጠቅመውባቸዋል:: ጸሐፊው ኢትዮጵያ በ11ኛው ክፍለ ዘመን የእስላሙም የክርስቲያኑም አገር ነበረች በማለት ጥንታዊውን የኢትዮጵያ ታሪክ የጻፈውን ትሪሚንግሀም “Islam In Ethiopia” በሚለው መጽሐፍ እንደ ትክክለኛ የታሪክ ጸሐፊ ወስደው፣ በዚሁ ጉዳይ ላይ ፕሮፌሰር ታደሰ ታምራት የወሰዱትን አቋም ለመተቸት እንዲህ ይሉናል:: “ኢትዮጵያዊ ያልሆነ ሰው ከኢትዮጵያዊው የተሻለ ኢትዮጵያዊ አመለካከት ሊኖረው እንደሚችል ጥሩ ማስረጃ ነው፤” ገጽ (100) በሚል ደምድዋል:: እዚህ ላይ ልብ ማለት የሚገባው ፕሮፌሰር ታደሰ ታምራት ይህን ጉዳይ የገለጹበትን መጽሐፍ ከማሳተማቸው ከ20 ዓመታት በፊት የትሪሚንግሃም መጽሐፍ መታተሙ በጉዳዩ ላይ ፕሮፌሰሩ የተሻለ ዕይታ እንዳላቸው ለመገመት ብዙም የሚያስቸግር አይደለም:: ጸሐፊው ግን አንድ ሰው ኢትዮጵያዊ ለመሆኑ፣ ለታሪክ ተመራማሪም ትልቁ ሰርተፊኬት ያልነበረችውን ኢትዮጵያ ነች ብሎ ማቅረብ ነው። እንዲህማ ከሆነ ከመነሻው ዜና መዋዕልን መተቸቱ ለምን አስፈለገ? ዜና መዋዕል ኢትዮጵያን የሚጠቅም ጥራዝ ነው ብለን መስማማት ከቻልን ማለት ነው::

ጸሐፊው የሚፈልጉትን ሐሳብ ትሪሚንግሃም በማጠናከሩ ወጣ ገባ እያሉ ቢያወድሱትም፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ የተለያዩ መጣጥፎችን ያዘጋጀውን ዶናልድ ሌቪንን ከመተቸት ግን አልተዘናጉም:: ይህ ተመራማሪ ባዘጋጀው አንድ የጥናት ውጤት “Wax And Gold:Tradition and Innovation In Ethiopian Culture” ላይ በደረሰበት መደምደሚያ፣ “በስሜት የተሳሰረና አንድነት ያለው የአማራ ኅብረተሰብ የለም” (ገጽ 59) የሚለውን አጥብቀው ኮንነውታል:: እኔ ሌቪን የደረሰበትን መደምደሚያ ባልቀበለውም፣ ጸሐፊው እሳቸው ስለሚያስቡትና ስለሚፈልጉት “የኢትዮጵያ ታሪክ” ቲፎዞ የሚሆኑ የውጭ አገርም ሆነ የቤተ መንግሥት ዜና መዋዕሎችን ሳያኝኩ ውጠው፣ ኢትዮጵያን በሌላ መንገድ የሚያሳዩ ጥራዞችን ደግሞ በተበጣጠሰ መልኩ መተቸታቸው እኛን በጥራዝ ለመጋት የሞከሩት የታሪክ ትንታኔ ስለመክሸፉ እንጂ ስለመተኮሱ አያሳይም::

ኢትዮጵያ መቼ ዘመናዊ አገር ሆነች?

ኢትዮጵያ የብዙ ዘመናት የሕዝቦች አንድነትና ልዩነት ታሪክ ያላት አገር መሆኗ ጥያቄ የሚያስነሳ ጉዳይ አይደለም:: ጉዳዩ ጥያቄ የሚያጭረው ይህ የኢትዮጵያ የብዙ ዘመናት ታሪክ እንደ አገር ለነገሥታት የተጻፈ ታሪክ ነው? ወይስ የተለያዩ ሕዝቦች ታሪክ ነው? እንደ አገር ለነገሥታት የሚል ታሪክና እንደ ሕዝቦች ያለ ታሪክ ይለያል ወይ? የሚሉት ጥያቄዎች መሠረታዊ ናቸው:: በትንሹ ሙቀቱን ለመጨመር ኢትዮጵያ አገር ነበረች ስንል አገር ስለመሆን የሚያሳዩ መስፈርቶችና ምልክቶች ምን ነበሩ? ምንድን ናቸው? ጸሐፊው የአሁኑን ጥያቄ ለመመለስ ዳድቶአቸዋል። እንዲህ እያሉ “አገር” የሚለውን ቃል ወስደው ከዜና መዋዕል ደግሞ “አገረ መንግሥት” የሚለውን ወርሰው ይህም በእንግሊዝኛው (State) ነው ይሉናል:: በዚህም መሠረት “አገር ማለት በአንድ ዓይነት ሕግና በአንድ መንግሥት ጥላ ሥር የሚተዳደሩ

በጦርነት፣ በግጦሽ መሬት ፍለጋ፣ በጋብቻና በመሳሰሉት ምክንያቶች እርስ በርስ በመቀራረብ ባህላቸውንና ቋንቋቸውን የተለዋወጡበት፣ የተወራረሱበትና የነበሩዋቸውንም የማንነት መገለጫዎች ጠብቀው፣ በችግርም ወቅት አብረው አንድ ሆነው የኖሩበት ሁኔታ ነበር:: በዚህም ምክንያት ብዙ የሆኑ አካባቢያዊ መንግሥታት በኢትዮጵያ የነበሩ ሲሆን፣ በአንዱ ማኅበረሰባዊ መንግሥት በተወሰነ የታሪክ ሒደትና አጋጣሚ አንድ ማኅበረሰብ ገዢ ወይም ራሱ ተገዢ የነበረበት ሁኔታ ነበር። እነዚህና ሌሎች ምክንያቶች ተደማምረው ነው እነዚህ ማኅበረሰቦች አሁን በምናውቃት የተከለለች ኢትዮጵያ ውስጥ ለመቆየትና ታሪኮቻቸውን ለመንከባከብ የበቁት::

መንደርተኛ ማን ነው?

ጸሐፊው በጥራዛቸው እንዲህ ይሉናል::

“መንደርተኛ ማለት ከመንደር በማይወጣ አስተያየት፣ ከመንደር በማይወጣ አስተሳሰብና ከመንደር በማይወጣ ስሜት መመራት ነው፤” ካሉ በኋላ መነሻውን ሲበይኑ “የመንደርተኝነት መሠረት ምንድን ነው ዘር ነው፤ ቋንቋ ነው፤ ሃይማኖት ነው፤ ባህል ነው፤ መንደርተኝነት ብሂል ምንድነው ብሎ አይጠይቅም:: መነሻውም መድረሻውም የመንደሩ ቋንቋ፤ የመንደሩ ሃይማኖት፤ የመንደሩ ብሂል ከሌላው ሁሉ የተሻለና የበለጠ ነው የሚል ጠባብ አስተያየት ነው፤ መነሻውም ሆነ መድረሻው ልዩነትን ማጉላት ነው፤” ገጽ (170 እና 171) ይሉናል::

ይህንና መሰል “የመንደርተኝነት” ጥራዝ ጀባ ያሉን ጸሐፊ ሰው የራሱን ዘር፣ የራሱን ቋንቋ፣ የራሱን ባህል ከሌለው አስበልጦ በመመልከቱ “መንደርተኛ” ብለው ይፈርጁታል:: እስቲ አንባቢያን ለራሳችንና ለህሊናችን ለሚቀጥሉት ጥያቄዎች መልስ እንስጥ:: የራሱን ዘር፣ ቋንቋ፣ ባህልና ሃይማኖት ከሌላው አስበልጦ የማይመለከት ማኅበረሰብ በዚህ ምድር ላይ አለ? አለ ከተባለ ለምን እንደዚያ ሊመለከት ቻለ? ሰው በተፈጥሮ የዕድገት ሒደት የእናትና የአባቱ ማኅበረሰብ የሚናገረውን ቋንቋ፣ ያለውን ባህልና ሃይማኖት ለማወቅና ለመተግበር ቅርብ ነው ወይስ የሌላውን? በቅርብ ማወቁ የራሱን እንዲያስበልጥ ያደርገዋል ወይስ የሌላውን? የሌላው ከእሱ ስለመብለጡ መስፈርቱ ምነድን ነው? ከእሱ ስለመብለጡ የመወሰን ሥልጣንስ የማን ነው? የባለቤቱ ወይስ የእኔ ይበልጣል ባዩ? በመወሰን ሥልጣን የኔ የበላይ ነው የሚባል ከሆነ ጉዳዩ የተቀባዩን ባህል ማነስ ሳይሆን የሰጪውን ትምክህት የሚያሳይ ይሆናል::

በኢትዮጵያ ከአሁን በፊት የነበሩት አገዛዞች “መንደርተኝነትን” በማጥፋት አገርን ለመገንባት (Nation Building) ባደረጉዋቸው እንቅስቃሴዎች ሁሉንም “የመንደርተኝነት አስተሳሰብ” እንዳላጠፉት የሚታወቅ ነው:: የኢትዮጵያ ገዢዎች የሌሎች ማኅበረሰቦችን የመንደርተኝነት አስተሳሰብን ለማጥፋት የከፈሉትን ዋጋ ያህል የተወሰነ ማኅበረሰብን የመንደርተኝነት አስተሳሰብ ሕጋዊና ተቋማዊ ለማድረግ ጭምር ከፍለዋል:: ግልባጩ ሲታይ ማኅበረሰባዊ መንደርተኝነት የሚጠላው መንግሥታዊ ድጋፍ ያለውን መንደርተኝነት ለማስፋፋት ተብሎ ነው::

የመንደርተኝነት አስተሳሰብ (የራስን የማክበር የሌላውን ያለማቅለል አስተሳሰብ ልበለው) የግጭት መነሻ መሆን የሚያቆመው መንግሥት ለሁሉም ማኅበረሰብ አስተሳሰቦች ዕውቅና መስጠት ሲችል ነው:: ይህን ማድረግ ባልቻሉ አገሮችና መንግሥታት ይህ አስተሳሰብ የማኅበረሰብን ቅራኔ የሚፈጥር ይሆናል:: ለምሳሌ አሜሪካኖች የመንደርተኝነት አስተሳሰብን ከፖለቲካና ከመንግሥት አስተዳደር ለማራቅ ብዙ መንገድ ቢሄዱም፣ በአሁኑ ጊዜ ይህን አስተሳሰብ ከመንግሥት መዋቅር ማፅዳት አልቻሉም:: ለዚህም ነው በአሜሪካ የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት አስተዳደር ውስጥ ጥቁር ከነጭ እኩል ክብርና መስተንግዶ የማያገኘው::

ጸሐፊው የመንደርተኝነት አስተሳሰብን አምርረው እንደሚጠሉ ቢገልጹም እሳቸው ስለራሳቸው ያነሷቸው ፉከራዎች መንደርተኝነታቸውን ያሳብቃል:: ጠራዡ እንዲህ ይላሉ:: “በአሜሪካ አገር ተማሪ ሆኜ ለአባቴ ስልክ ለማስገባት ወደ ቴሌፎን ኩባንያው ሄድሁ፤ በሥራ ላይ የነበረችው ሴትዮ ሙሉ ስምህን ጻፍልኝ አለችኝና ጻፍሁት:: በቴሌፎን ማውጫው ላይ የሚገባው ስምህ ማርያም ነው አለችኝ ---- ክርክሩ ቀጠለ ---- ስምህ የሚጻፈው ወልደማርያም መስፍን ተብሎ ነው አለችኝ:: ሲስተርዬ ስሜን የማውቀው እኔ ነኝ፤ ማን እንደሆንህና ማን ተብለህ እንደምትጠራ አታውቅም ካልሽኝ እኔ የምነግርሽን አድርጊ ብዬ ክርክሩ ቆመ::” (ገጽ 60) ይሉናል:: ጸሐፊው በሰው አገር ፊደል ለመቁጠር ሄደው ከአሜሪካውያን የስም አጠራር ባህል ውጭ “የኔ ሐሳብ ትክክል ነው” ማለት ለምን አስፈለጋቸው? ሌሎች ኢትዮጵያውያን ይህን ያለማድረጋቸውን ሲኮንኑ “መንደርተኝነታቸውን” አያሳይም እንዴ? በእርግጠኝነት እሳቸው ለአሜሪካዊቷ መንደርተኛ ናቸው::

ጸሐፊው ይህ የመንደርተኝነት አስተሳሰብ ተጣብቷቸው ሳለ መንደርተኝነትን እንድንተው የሚያስገድዱን መሠረታዊ ምክንያቶች እንዳሉ ሊጠቃቅሱልን ሞክረዋል:: እነዚህን ምክንያቶች ሲያስቀምጡ፣ “ትክክለኛው የሰው ልጆች ዕድገትና የታሪክ አካሄድ ትውልድ ከመንደርተኝነት ጠባብ አስተያየት ወጥቶ ወደ ዓለም አቀፍ ኅብረት ለመሸጋገር ያለው ከፍተኛ ጥረት ነው::” (ገጽ 173) ይህንን ትንታኔ በሁለት መልኩ ማፍታታት ያስፈልጋል:: አንደኛው የሰው ልጅ ዕድገት ወደ ዓለም አቀፋዊ ኅብረት እንዲሸጋገር ያደረገው ምንድነው? የተለያዩ ማኅበረሰብ ሐሳቦች ገበያ ላይ ቀርበው ከእነዚህ ውስጥ ማኅበረሰቡ የሚፈልገውን የሐሳብ ቡፌ አንስቶ ነው? ወይስ ይህ የሐሳብ ቡፌ ጥሩ ስለሆነ መመገብ አለብህ። አለበለዚያ! ተብሎ ነው? ለዚህ ነው ትክክለኛ የሰው ልጆች ዕድገትና የታሪክ ሒደት ጸሐፊው ወዳስቀመጡት ደረጃ እስካሁን ያላደረሰን:: ምዕራብ አውሮፓውያን ዘመናዊ አገርን ለመመሥረት ተገጣጣሚ የባህልና የፖለቲካ ማኅበረሰብ

(Nation State) መኖር እንደ ወሳኝ ሐሳብ በመውሰድ አገር የመገንባት ሥራዎችን ከ18ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሄደውባቸዋል:: አሁን ላይ ሆነን ተገጣጣሚ የባህልና የፖለቲካ ማኅበረሰብ መገንባት ችለዋል ወይ? ብለን ስንጠይቅ የምናገኘው መልስ እነዚህ አገሮች እንደዚህ ዓይነት ማኅበረሰብ መገንባት አልቻሉም ነው::

በተለይም ይህን መሰል ተገጣጣሚ የባህልና የፖለቲካ ማኅበረሰብ ለአንድ ዘመናዊ አገር ወሳኝ መነሻ ነው ብላ ብዙ በሠራችው ታላቋ ብሪታኒያ በአሁኑ ወቅት በአራት (አይሪሽ፣ ኢንግሊሽ፣ ዌልሲሽ፣ ስኮቲሽና ብሪቲሽ) በሚባሉ የፖለቲካና የባህል ማኅበረሰቦች ተከፋፍላ ትገኛለች:: ይህን እሳቤ አገር ለመገንባት ተሳክቶላቸዋል በሚባሉት የተወሰኑ አገሮች (ፈረንሳይና ኢጣሊያንን) ማንሳት ይቻላል:: ግንባታው የተፈጸመው የተወሰነ የባህል ማኅበረሰብን በማጥፋት (Ethnocide) ነበር። ይሁንና በአሁኑ ወቅት በመጥፋት ጎዳና ላይ ያሉት ማኅበረሰቦች (ለምሳሌ ባስክ፣ ኦኪታንያንስና ኮሪሲካንስ) ቢሆኑም እያቆጠቆጡ መሆናቸውን የሚያሳየው፣ አገር ለመገንባት ማኅበረሰብ (ጎሳ) መግደል የሚለው ብሂል ጊዜው ያለፈበትና የከሰረ የፖለቲካ ዘዴ መሆኑን ነው:: ሁለተኛው ነጥብ ዓለም ወደ አንድ ማኅበረሰብ እየሄደች ነው:: ስለዚህ እኛም ወደዚያ ለመሄድ እንድንችል የመንደርተኛ አስተሳሰብ እንተው ስንል፣ የእኔ ጥያቄ የማንን መንደርተኝነት ለመቀበል? የነጭ አሜሪካውያንን? ወይስ የቻይኖችን? እነዚህ አገሮች በስልት ወይም በስሌት እያስፋፉ ባሉት መንደርተኛ አስተሳሰብ አይደለም እንዴ ዓለም እየታመሰች ያለቸው? ስለዚህ ጸሐፊው በስድብ መልክ ያስቀመጡት አመለካከት በራሱ መጥፎ አይደለም። መጥፎ መሆን የሚጀምረው የራስን የመንደርተኝነት አስተሳሰብ በኃይልና በንቀት በሌላው ማኅበረሰብ ላይ ለመጫን የሚደረግ እንቀስቃሴ ሲኖር ነው።

ጸሐፊው ሌላው በጥራዛቸው ያነሱት ጉዳይ የመንደርተኝነትን አስተሳሰብ ነፃ አገር ከመመሥረት ጋር በማስተሳሰር ያቀረቡት ትንታኔ ነው:: የሶማሊያ መንግሥትን ጸሐፊው የኮነኑበት አግባብ ይበል የሚያስብል ነው:: በዚህ ላይ ብቻ ቢያቆም ጥሩ ነበር:: ግን እንዲህ ይላል:: “የሶማሊያ መንግሥት የመንደርተኝነት አስተሳሰብን ለሶማሊኛ ተናጋሪዎች ኢትዮያውያን ብቻ ሳይሆን ለኦሮምኛ ተናጋሪዎች፣ ለትግርኛ ተናጋሪዎች፣ ለአፋርኛ ተናጋሪዎች” (ልብ በሉ ኦሮሞዎች፣ ትግሬዎች፣አፋሮች አላሉም) (ገጽ174) ሰብኳል ብለዋል:: በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት እነዚህ ማኅበረሰቦች ለብሔር ጥያቄ ትግል ከሶማሊያ መንግሥት ስለመማራቸው ማረጋገጫው ምንድን ነው? ሶማሊያ አገር ተብላ ከመታወጁ በፊት እነዚህ ማኅበረሰቦች የራሳቸው የማንነት መገለጫ ነበራቸው:: የእነዚህ ማኅበረሰብ የማንነት መገለጫዎች በኢትዮጵያ በነበሩ ገዥዎች ሶማሊያ አገር ከመሆና በፊት ተደፍጥጠውባቸዋል:: እነዚህ ማኅበረሰቦች በቀድሞዎቹ የኢትዮጵያ ገዢዎች የተደፈጠጡባቸውን የማንነት መብቶች ለማስመለስ ሶማሊያ አገር ከመሆኗ በፊት ትግል ጀምረው ነበር:: እነዚህ ማኅበረሰቦች በገዥዎች የተደፈጠጡባቸውን መብቶች ለማስመለስ የንቃተ ልቦና እንክብል ከሶማሊያ መንግሥት ለመቀበል የሚያስፈልጋቸው አይመስለኝም:: ይህ ጉዳይ የእነዚህንና የሌሎችን ሕዝቦች የትግል ታሪክ መሻር ነው፣ አይቻልም እንጂ። በተጨማሪም እነዚህ ማኅበረሰቦች ነፃ አገር ለመመሥረት ካላቸው ፍላጎት ጋር በማገናዘብ ያቀረቡት ጉዳይ አሁን አገሪቷ ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ ያስገባ አይደለም:: በዚህም ምክንያት ጥራዙ የከሸፈ ብቻ ሳይሆን፣ የአሁኑን የአገሪቷን ተጨባጭ ሁኔታ ያላገናዘበና እንዲሁ ወደ ገበያ የተወረወረ ነው::

መደምደሚያ

“መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ” የሚለው ጥራዝ ታሪክን ከፖለቲካ ጋር አላግባብ በማሳከርና በማጋባት ለራስ ዕይታ የሚጠቅምን አለቅጥ ወደላይ በማንሳት፣ የማይበጅን ደግሞ በማንሸራተት ቁንጽል “የጥንታዊት” ኢትዮጵያን “አንድነት” ወይም ዘመናዊ አገርነት በብዕር ለማምጣት የተሞከረበት የጉልበት ሥራ ነው:: ጸሐፊው በጉዳዩ (በሰሜኑ የአገራችን ክፍል ታሪክ) ላይ ያላቸው ዕውቀት ጥልቀት ያለው መሆኑን የሚያሳዩ ምልክቶች እዚህም እዚያም ተወርውረው የሚገኙ ቢሆንም፣ የሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦችን ታሪክ ‘አውቀው በንቀት ወይም ሳያውቁት በትምክህት’ ሳይገልጹት አልፈዋል። ምናልባት ጸሐፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ የችግሮቹ ሁሉ ምንጭ ነው ብለው የጠቀሱትን ሥልጣን የግል መሆንንና የሚገራበትን፣ ሥልጣን የሚሠለጥንበትን ሥርዓት አለማበጀቱ ነው ያሉትን ችግር ለመቅረፍ ሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች (ለምሳሌ ኦሮሞዎች በገዳ ሥርዓት) የነበራቸውን የሥልጣን ምንነትና ዕይታ ታሪክ ቢያጠኑ ለኢትዮጵያ ችግር መነሻው ሌላ እንደሆነ ያገኙት ነበር። በዚህም ምክንያት ጸሐፊው ለኢትዮጵያ ታሪክ መክሸፍ ምክንያት ብለው በቀረቡዋቸው ሐሳቦች እውነተኛ፣ ሚዛናዊ፣ አካዳሚያዊ ብቃት ያለውና አስማሚ (አቀራራቢ) ትንታኔ ግን ሊያቀርቡ አልቻሉም:: በሌላ በኩል ጽሑፉ በተዘጋጀበት ጊዜ በተለይ ስለመንደርተኝነት ጉዳይ የተገለጸውና የታተመበት ወቅት በዓለምም ሆነ በአገራችን ብዙ ለውጦችና ኹነቶች የተስተናገዱበትና የተስተዋሉበት ቢሆንም፣ ጥራዙ በጉልበት የወጣ ይመስላል። በዚህም ምክንያት ጥራዙ የዓለምን የጊዜ አቆጣጠር ወደኋላ መመለስ ካልተቻለ በቀር ይህን ያህል ተጨባጭ ፋይዳ ያለው አይደለም::

በአጠቃላይ ጥራዙ የአገራችንን የታሪክ ዑደት ከተለያዩ አቅጣጫዎች በመመልከት የራሳችንን ግንዛቤ እንድንይዝ ለማድረግ ያለው ዕድል የጠበበ ቢሆንም፣ በጽሑፋቸውና ጥቂት በሚባሉ “ደጋፊዎቻቸው” ውስጥ እየሟሸሽ ያለውን “የገናናዋን” ቁንጽል “ኢትዮጵያ” እሳቤ ለመረዳት በመጠኑ ስለሚረዳ አንብቤ በመጨረሴ ብዙም አልተቆጨሁም::

ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል::

ሰዎች/ሕዝብ ባለመብት የሆኑበት የኑሮአቸው መሠረት የሚያደርጉት በወሰን የተከለለና የማይደፈር መብታቸውን ጨምሮ የሚገልጽ ኅብረት ነው” ይሉናል (ገጽ 80):: ከዚህ ትርጉም አንድ አገር አገር ለመባል የሚከተሉትን ነጥቦች መሟላት አለባቸው::

በአንድ ዓይነት ሕግ የሚመራ ሕዝብ

በአንድ መንግሥት ጥላ ሥር የሚተዳደሩ ሰዎች

ሕዝቦች ባለመብት የሆኑበት/ኑሮአቸውን መሠረት የሚያደርጉበት መብት

የተከለለና የማይደፈር መሬት ያላቸው

ኅብረት ያላቸው ሕዝቦች

ጸሐፊው እነዚህ መስፈርቶች ላይ በመመሥረት ኢትዮጵያ የመንን ለመርዳት በሄደችበት ጊዜ እንኳን አገር ነበረች ይሉናል:: የአገርን ሁኔታ ለመለየት ደራሲው የወሰዷቸው እነዚህ መስፈርቶች በ18ኛው ክፍለ ዘመን ዘመናዊ (Modern State) አገሮችን ለመግለጽ በጀርመናዊው የማኅበረሰብ ፈላስፋ ማክስ ዌበር የተቀመጡ ናቸው:: እነዚህ መስፈርቶች በእንግሊዝኛው “Territory, People/Nation, Soverginity” በመባል የሚታወቁት ናቸው:: ጸሐፊው በስድስተኛው ክፍለ ዘመን በአስቀመጣቸው መስፈርቶች መሠረት ኢትዮጵያ አገር ነበረች የሚያሰኝ አንድምታ ያለው ሐሳብ ያቀርባሉ:: የኢትዮጵያ በዚያ ወቅት የተከለለና የማይደፈር መሬት የቱ ነበር? በዚያ ወቅትስ ኢትዮጵያ በአንድ ዓይነት ሕግ የሚመራ ሕዝብ ነበራት ለሚሉት ጥያቄዎች ማስረጃችን ምን ይሆን? ይህን ያሉትን ሕግስ ማን አወጣው? መቼም ፓርላማ እንደማይሉኝ ተስፋ አደርጋለሁ:: ጸሐፊው በመጽሐፉ ውስጥ ያስገቡዋቸው በተለያዩ ግለሰቦች የተዘጋጁ የተለያዩ ካርታዎች እርስ በርስ የተምታቱ ብቻ ሳይሆን፣ የሚያሳዩት እውነታ ኢትዮጵያ ከ19ኛው ክፍለ ዘመን መባቻና 20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ በፊት የተከለለች አገር (Territional State) አለመሆኗን ነው:: ስለዚህ ጸሐፊው በምን ስሌት ነው ምዕራብ አውሮፓውያን ዘመናዊ መንግሥትን ለመግለጽ የተጠቀሙባቸውን መስፈርቶች ወደኋላ 1,200 ዓመታት በመውሰድ፣ ኢትዮጵያን እንደ ዘመናዊ አገር ለመግለጽ የሞከሩት በውሸት የተጋገረ ታሪክ ከጠቃሚነቱ ይልቅ መርዝነቱ ያይላል።

በዚያን ጊዜ ኢትዮጵያ ባህላዊ አገር (Traditional State) ነበረች:: በዚህም መሠረት አሁን በአገሪቷ ውስጥ ያሉ የተለያዩ ሕዝቦች በሚሰፍሩበት አካባቢ የራሳቸው የሆነ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ መዋቅር ያላቸው ነበሩ:: በንግድ፣

Page 38: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 38 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ማስታወቂያ

Page 39: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 39 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታወቂያ

በአዲስ አበባ ከተማ ለሚኖሩ የመብራትና የውሃ አገልግሎት ተጠቃሚዎች በሙሉ

ድርጅታችን ክፍያ ፋይናንሺያል ቴክኖሎጂ ሃ/የተ/የግ/ኩባንያ ከመገናኛና

ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጋር በጋራ በመሆን በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ 

31 ለሁሉ በመባል በሚጠሩ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት ከጥር 27 ቀን 

2005 ጀምሮ የውሃና የመብራት ፍጆታዎችን ሂሳብ በመሰብሰብ ሥራ

መጀመሩ ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ወቅት ደንበኞችን የመመዝገብና ክፍያ

የመቀበል ሥራ አብሮ በመሰራት ላይ ያለ ሲሆን ከመደበኛ የክፍያ

ጊዜያቸው ቀድመው የሚመጡ ደንበኞችን ማስተናገድ በመሰጠት ላይ

ባለው አገልግሎት ላይ ጫና እየፈጠረ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ደንበኞች ወደ

ለሁሉ የክፍያ ማዕከላት ሲመጡ፤ 

1. ቀድሞ ይገለገሉበት የነበረውን የክፍያ ጊዜ ጠብቀው መሆን ይኖርበታል

2. የክፍያ ጊዜያቸውን ጠብቀው የሚመጡ ደንበኞች ብቻ ይስተናገዳሉ

3. ደንበኞች ለምዝገባ ሲመጡ ከዚህ በፊት የከፈሉበት የቅርብ ጊዜ

ደረሰኝ ብቻ ይዘው መምጣት ይጠበቅባቸዋል

4. ደንበኞች በየትኛዎቹም የለሁሉ ማዕከላት መስተናገድ ስለምትችሉ

መጨናነቅ በሚፈጠርበት ጊዜ በአቅራቢያችሁ ወደ ሚገኙ ሌሎች

ማዕከላት በመሄድ መመዝገብና ክፍያችሁን መፈፀም ትችላላችሁ

5. የክፍያ ማዕከላቱ ከሰኞ እስከ አርብ ከጠኋት 2 ሰዐት እስከ ምሽቱ 1 ሰዐት

እንዲሁም ቅዳሜ ከ3 እስከ  10 ሰአትግልጋሎትይሰጣሉ፡፡ በተጨማሪም

ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ቅዳሜ እስከ ምሽቱ  1 ሰዐትና እሁድ

ከጠዋቱ 3 ሰዐት እስከ 10 ሰዐትአገልግሎት ይሰጣሉ፡፡ 

የኢትዮጵያ አልክትሪክ ሃይል ኮረፖሬሽንና የአዲስአበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ደንበኞች የፍጆታ የክፍያ ጊዜ በሚከተለው መልኩ ተራዝሟል

የኢትዮጵያ አልክትሪክ ሃይል ኮረፖሬሽን የክፍያ ጊዜዎች

ተ.ቁ የክፍያ ጊዜ የተራዘመበት ቀን1 26 - 30 እስከ የካቲት 102 1 – 5 እስከ የካቲት 15

3 6 - 10 እስከ የካቲት 20

4 11 - 15 እስከ የካቲት 25

የኤሌክትሪክ የቅድሚያ ክፍያ (ካርድ) ተጠቃሚዎች በቀድሞዎቹ የኢትዮጵያ

መብራት ሃይል ኮርፖሬሽን የክፍያ ማዕከላት ይስተናገዳሉ

የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ደንበኞች እስከ የካቲት 24 ድረስ

መክፈል ይችላሉ

ለሁሉ አዲስ አበባ ቅርንጫፎች አድራሻቅርንጫፍ አድራሻ

ሽሮ ሜዳ ሽሮ ሜዳ ታክሲ ማቆሚያ /ስፔንኤምባሲ ፊት ለፊት/ኢትዮ ቴሌኮም ግቢ

አራት ኪሎ አራት ኪሎ ቱሪስት ሆቴል ፊትለፊት/ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ህንጻ

ስድስት ኪሎ ያሬድ ሙዚቃ ት/ቤትን አለፍብሎ/ ኢትዮ ቴሌኮም ህንፃ

ፈረንሳይ ፈርንሳይ ለጋሲዮን ታክሲ መናኸሪያ - አቦ ቤተክርስቲያን መንገድ/ ኢትዮ ቴሌኮም ህንፃ

አዲሱ ገበያ አዲሱ ገበያ ታክሲ መናኸሪያ /ኖክ ነዳጅ ማደያ ገባ ብሎ/ኢትዮ ቴሌኮም ህንፃ

አስኮ አስኮ መናኸሪያ ንግድ ባንክ ፊትለፊት/ ኢትዮ ቴሌኮም ህንፃ

ሸጎሌ  ሸጎሌ - ሩፋኤል መንገድ/ ኢትዮ ቴሌኮም ህንፃ

አጠና ተራ አጠና ተራ ዋናው ቀለበት መንገድ ላይ/ ኢትዮ ቴሌኮም ህንፃ

ኮልፌ ኮልፌ 18 ማዞሪያ/ የኢትዮጲያ መብራት ኃይል ግቢ

አየርጤናኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የወረዳ 01 አስተዳደር መ/ቤትፊትለፊት/ ኢትዮ ቴሌኮም ግቢ

መርካቶ መሃል መርካቶ ምዕራብ ሆቴል ጎን/ መርካቶ ንግድ ባንክ ህንፃ

አውቶቢስተራ መርካቶ አዲስ ከተማት/ቤት ጎን/ ኢትዮ ቴሌኮም ግቢ

ተክለሃይማኖትተክለሃይማኖት ንግድ ባንክቅርንጫፍ ገባ ብሎ ኮንዶሚኒየም ቤቶች ፊት ለፊት

ፖስታቤት ዋናው ፖስታ ቤትግ ቢ

ጊዮርጊስከጊዮርጊስ ወደ ሰሜን ሆቴል የሚወስደው መንገድ ላይ/ ኢትዮ ቴሌኮም ግቢ

አቃቂ

አቃቂ የድሮ ባቡር ሃዲድ መዳረሻ /ከንግድ ባንክ 100 ሜ. ገባ ብሎ/ የኢትዮጵያ መብራት ኃይል ግቢ

ለቡ ላፍቶ ቀለበት መንገድ/ የኢትዮጵያ መብራት ኃይል ግቢ

ብስራተገብርኤልብሩክ ክሊኒክ ፊት ለፊት/ የአ.አ ውሃ እና ፍሳሽ  መ/ቤት

ሳሪስ ሣሪስ ዳማ ሆቴል መገንጠያ ላይ/ ንግድ ባንክ ህንፃ

ቴሌጋራዥ  መስከረም ማዞሪያ/ የቀደሞቴሌ ጋራዥ ግቢ

መገናኛ መገናኛ ቦሌ ክ/ከተማ ጽ/ቤት አጠገብ/ የአ.አውሃና ፍሳሽ ዋና መ/ቤት

ጉርድሾላ  ጉርድሾላ/ ኢትዮቴሌኮምግቢቦሌ ሚሊኒየም  ሚሊኒየምአዳራሽፊትለፊት

ሜክሲኮ ሜክሲ ኮአደባባይ የአ.አንግድ ምክር ቤት ፊት ለፊት/ የኢትዮጰያ መብራት ሃይል ግቢ

ለገሀር  ለገሃር/ መድህን ኢንሹራንስ ህንፃ

ወሎሰፈር ሸዋሱፐርማርኬት (100 ሜ. ወደ ቦሌዝቅብሎ)/ ኪራይ ቤቶች ህንጻ

ካዛንችስንግድ ባንክ ካሳንችስ ቅርንጫፍ ፊት ለፊት/ መብራት ሃይል አስቸከይ ጥገና ግቢ

ቤቴል ወይራ ሰኔ ሰላሳ ማህበር መገቢያላይ/ ፖስታ ቤት ህንፃገርጂ ገርጂ ሮባዳቦ ሰንሻይን መኖሪያ ቤቶቸ አጠገብ

ኮተቤኮተቤ ብረታ ብረትፊትለፊት/ የኢትዮጵያ መብራት ሃይል ግቢ

ቃሊቲቼራሊያ ብስኩት ፋብሪካን ወደ ደብረዘይት መንገድ አልፎ በአቢሲኒያ ባንክ 100 ሜ. ገባ ብሎ

ይህንን በሃገሪቱ አዲስ የሆነ አገልግሎት በተሳካ መልኩ ለማቅረብ በትጋት

እየሰራን መሆኑን እየገለፅንላችሁ በዚህ የመጀመሪያ የክፍያ ወር መጠነኛ

መጨናነቅ ሊፈጠር ስለሚችል ደንበኞች በትዕግስት እንድትስተናገዱ

በትህትና እንጠይቃለን፡፡

ክፍያ ፋይናንሺያል ቴክኖሎጂ ሃ/የተ/የግ/ኩባንያ

Page 40: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 40 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቀን የካቲት 7 ቀን 2005 ዓ.ም. ይከበራል:: የካቲት 1 ቀን 2005 ዓ.ም. በኤግዚቢሽን ማዕከል ክብረ በዓሉን አስመልክቶ የመከላከያ ሚኒስቴር ለአገሪቱ ልማት እያደረገ ያለውን አስተዋጽኦ የሚያመላክት ዓውደ ርዕይ በይፋ ተከፍቷል:: በዓውደ ርዕዩ ላይም አገሪቱ በዕቅድ ከያዘቻቸው ሰፊፋ የኢንዱስትሪ ምርቶች መካከል ሠራዊቱ የሚያመርታቸው የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች፣ የኃይል ማመንጫ ተርባይኖች፣ የኢንዱስትሪ ማሽነሪ መለዋወጫዎች፣ የሚገጣጥማቸው ተሽከርካሪዎች፣ እንዲሁም ራሱ የሚያመርታቸውና የሚገጣጥማቸው የጦር መሣርያዎችና ሔሊኮፕተሮች፣ ሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮኖች) ለዕይታ ከቀረቡት መካከል ዋነኞቹ ናቸው:: ከቅዳሜ ጀምሮ በሕዝብ በመጎብኘት ላይ ናቸው:: ፎቶ በሪፖርተር/ናሆም ተስፋዬ

ፎቶ ዜና

Page 41: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 41 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1ማስታወቂያ

ካለፈው የካቲት 1 ቀን ጀምሮ በይፋ በመከበር ላይ ይገኛል::

የመከላከያ ሚኒስቴር በዓሉን ለማክበር ካዘጋጃቸው ፕሮግራሞች መካከል ሚኒስቴር መሥርያ ቤቱን ወይም የሠራዊቱን ቁመና በከፊል የሚያሳይ ዓውደ ርዕይ ባለፈው ዓርብ በኤግዚቢሽን ማዕከል በይፋ ከፍቷል:: እስከ የካቲት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. ድረስ የሚቆየውን ዓውደ ርዕይ በይፋ የከፈቱት የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ዋና አዛዥ አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ሲሆኑ፣ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ካሳ ተክለብርሃንና በበርካታ ሚኒስትሮች፣ እንዲሁም በጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታ ማዥር ሹም ጄነራል ሳሞራ የኑስና በመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ ታጅበው ነበር::

የሠራዊቱ ጄነራል መኮንኖችና መስመራዊ መኮንኖች፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትና በአዲስ አበባ የሚገኙ ዲፕሎማቶችና ወታደራዊ አታሼዎች ዓውደ ርዕዩን የጐበኙ ሲሆን፣ ሁሉም በተመለከቱት ሠራዊቱ በወታደራዊ መስክ በተለይም ለአገሪቱ ኢንዱስትሪ የፈጠረውን አቅም በአድናቆት ሲመለከቱ ተስተውለዋል::

‹‹ሕገ መንግሥታዊ ታማኝነታችንና ሕዝባዊ ባህርያችን እንደተጠበቀ ይኖራል›› በሚል መሪ ቃል መከበር በጀመረው የሠራዊቱ ቀን መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ፣ የዓውደ ርዕዩ ዓላማ የሠራዊቱ ውጤቶችን በከፊል ይፋ ለማድረግና ከመንግሥትና ከሕዝቡ የሚገኘው ግብረ መልስ ለሠራዊቱ ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥርለት በመታመኑ ነው ብለዋል::

በመጀመርያዎቹ ዓመታት ውስጥ የሠራዊቱን የሰው ኃይል መሠረት ያደረገ ሥራ ሲከናወን እንደቆየ፣ በዚህም ከመደበኛ የውትድርና ትምህርት ቤቶች እስከ ዩኒቨርሲቲ ድረስ በርካታ ተቋማትን በመገንባት ሠራዊቱ ከአመለካከት እስከ ክህሎት ሁለንተናዊ ብቃት እንዲኖረው መደረጉን ሚኒስትሩ አስረድተዋል::

በአገር ውስጥ አስተማማኝ ሰላምን ከመፍጠር አኳያ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ በድል እያከናወነ ከመሆኑ ባሻገር፣ በውጭ አገሮች የሰላም ማስከበር ተልዕኮውም የአገሪቱና የሕዝቦቿ ኩራትና የተከበረ ሠራዊት ነው ብለዋል::

ከተጠቀሱት ተልዕኮዎች ጐን ለጐን ደግሞ ለኢንዱስትሪ ሽግግሩ መሠረት እየጣለ መሆኑን

የተናገሩት ሚኒስትሩ፣ የሚመደብለትን በጀት ቆጥቦና አብቃቅቶ የመጠቀም ባህሉን በመከተል፣ የታጠቃቸውን መሣርያዎች በራሱ አቅም ከማደስ ጀምሮ እስከ ማምረት ደረጃ መድረሱን ገልጸዋል::

በብርጋዴር ጄነራል ክንፈ ዳኘው የሚመራውና ከ15 በላይ ኩባንያዎችን በሥሩ የያዘው የኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን በዓውደ ርዕዩ ያቀረባቸው ሥራዎቹ ተልዕኮውን የሚገነዘቡ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ጨምሮ የጐብኚዎችን ቀልብ ይዞ ነበር::

ኮርፖሬሽኑ ቀላል ከሚመስሉ የሠራዊቱ አልባሳት፣ ማዕረጐች፣ የፓራሹት ዣንጥላን ጨምሮ በማምረት ለሠራዊቱ እያቀረበ ከመሆኑም ባሻገር ለጐረቤት አገሮችም ኤክስፖርት በማድረግ ላይ መሆኑ ተጠቁሟል::

በተጨማሪም ለአገሪቱ የግብርና ምርት ዕድገት የሚስማሙ ማሽነሪዎችን መገጣጠምና የማምረት ተግባር ላይ በሰፊው እየሠራ ሲሆን፣ የሚገጣጥማቸውን ትራክተሮችና የሚያመርታቸውን ተጓዳኝ መለዋወጫዎች በአውደ ርዕዩ አቅርቧል::

አገሪቱ ለምታደርገው የኢንዱስትሪ ሽግግር መሠረት ከመጣል ባሻገር፣ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ በየዓመቱ ከውጭ የሚገቡትን እንደ ዳፕና ዩሪያ ያሉ የማዳበሪያ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለማምረት በከፍተኛ ሥራ ላይ መሆኑን፣ ፋብሪካውን ዲዛይን ከማድረግ ጀምሮ እስከ መገንባትና ማጠናቀቅ የኮርፖሬሸኑ ኃላፊነት እንደሆነ፣ በአሁኑ ወቅትም በራሱ ኢንጂነሮች የተጠናቀቀውን የፋብሪካው ዲዛይን ይፋ አድርጓል::

በአምስት ዓመቱ የልማት ዕቅድ የተወጠኑ አሥር የስኳር ፋብሪካዎችን ዲዛይን በማድረግ ግንባታቸውን እያከናወነ ሲሆን፣ ለሚቋቋሙት ፋብሪካዎች የሚውሉ ማሽነሪዎችንም በማምረት ላይ ይገኛል::

ለፋብሪካው የሚያስፈልጉ የአገዳ መፍጫ ማሽኖችንና መለዋወጫዎችን የማምረትና የማሻሻል ሥራዎችን እያከናወነ ነው:: በተጓዳኝም ለኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚጠቅሙ ግዙፍ የሆኑ የድንጋይ መፍጫ ማሽኖችን፣ መደባለቂያ (ሚክሰሮችን)፣ ታወር ክሬኖችንና ዶዘሮችን እየገጣጠመና እየመረተ ይገኛል:: ለሕዝብ ትራንስፖርት የሚሆኑ አውቶቡሶችን፣ ለጨርቃ ጨርቅ፣ ለቆዳና ለሲሚንቶ ፋብሪካዎች የሚሆኑ መለዋወጫዎችንም እያመረተ ነው::

በዓባይ ወንዝ ላይ የሚገነባውን ታላቁን የህዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች የመፈጸም ኃላፊነቱን በተመለከተም፣ በመጀመርያ ታቅዶ የነበረውን 5,250 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም በራሱ ኢንጂነሮች ዲዛይኑን በመከለስ ለግንባታው ተማሪ ወጪ ሳያስፈልግ 6 ሺሕ ሜጋ ዋት እንዲሆን አድርጓል::

በአሁኑ ወቅት ለኃይል ማመንጫው የሚጠቅሙ ትራንስፎርመሮችን፣ የኃይል ማከፋፈያ ሰብስቴሽኖችን መገንባት የሚያስችል አቅም መፍጠሩን በዓውደ ርዕዩ ላይ ያቀረበ ሲሆን፣ ተርባይኖችን የመሥራት ደረጃ ላይም ደርሷል:: ለንፋስ ኃይል ማመንጫ የሚየገለግሉ ተርባይኖችን እያመረተ ሲሆን፣ 300 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያመነጨውን የአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ለመገንባት ዝግጅቱንም አሳይቷል::

ከአዲስ አበባ ጂቡቲ እንዲሁም ወደ ሰሜን የአገሪቱ ክፍሎች የሚዘረጉትን የባቡር መስመሮች የመገንባት ተልዕኮው የተሰጠውም ለዚሁ ኮርፖሬሽን ነው:: ዘመናዊ ባቡሮቹን ለመገጣጠም የሚያስችለውን አቅም መፍጠሩን በዓውደ ርዕዩ ላይ አሳይቷል::

በኢንፎርሜሽን ደኅንነት ተልዕኮ ላይ የተሰማራው የኢንፎርሜሽን ደኅንነት ኤጀንሲ በበኩሉ፣ እስከ ሰው አልባ አውሮፕላን የታጠቀ ሲሆን፣ አውሮፕላኑ በአገር ውስጥ የተገጣጠመ አነስተኛ መጠን ያለው ሲሆን፣ ተልዕኮውም ከከፍተኛ ርቀት ወይም ከዓይን እይታ ውጭ በመዘዋወር የአየር ፎቶግራፎችን ማንሳትና መላክ ነው::

በአሁኑ ደረጃ የደኅንነት ተቋሙ ይህንን አውሮፕላን ለከተማ የካርታ ሥራ እየተጠቀመበት ይገኛል:: ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ከጉብኝቱ ይፋ መሆን በፊት፣ ‹‹በሠራዊቱ የቁጠባ ባህል የመከላከያ በጀት በዓለም ከሚታወቀው የአንድ አገር የመከላከያ በጀት ከጠቅላላ የአገሪቱ ዓመታዊ ምርት (GDP) ሁለት በመቶ መብለጥ የለበትም ከሚለው መርህ አንፃር እጅግ ዝቅተኛ ነው፤›› ብለው ነበር::

ከጉብኝቱ በኋላ ሠራዊቱ በዚህ ውስን አቅም የደረሰበት የዕድገት ደረጃ በጣም ያስገረማቸው መሆኑን በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙ ሪፖርተር ያነጋገራቸው እንግዶች ገልጸዋል::

መከላከያ ሠራዊት የኢንዱስትሪ... በአክሱም ዩኒቨርሲቲ ትምህርት አልቆመም

የሪፖርተር እትም ጥር 26 ቀን 2005 ዓ.ም. ቅጽ 18 ቁጥር 25/1332 አክሱም ዩኒቨርሲቲን አስመልክቶ በፊት ገጽ ያስነበበው ዜና የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቆሙ የሚል ነው:: እንዲህ ዓይነት ጽሑፍ ስለትክክለኛነቱ ለሚመለከተው አካል ጥያቄ ሳይቀርብና ሳይረጋገጥ መጻፉ ከገንቢነቱ አፍራሽነቱ ያመዝናል ብለን እናምናለን:: ለዚህም እንደ ምክንያት የምናቀርበው በአክሱም ዩኒቨርሲቲ ለአንድም ቀን ቢሆን ትምህርት አለመቆሙ ነው::

ይሁን እንጂ አንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ረብሻ ከመነሳቱ ከአንድ ቀን በፊት ረብሻ እንደተነሳ በማስመሰል መዘገባቸው ጉዳዩ ከተማሪዎች ያልመጣ ስውር ሴራ የፈጠረው ሊሆን እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም::

በተመሳሳይ መልኩ የሪፖርተር ጋዜጣም ጥር 25 ቀን 2005 ዓ.ም. ማተሚያ ቤት የሚገባበት ቀን ሆኖ ሳለ ‹‹የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ትምህርት አቆሙ›› ሲል በዕለቱ መዘገቡ የሪፖርተር ጋዜጣ የረብሻው ዕቅድና ዜና ድርጊቱ ከመፈጸሙ በፊት ከደም ብሎ የደረሰው ያስመስለዋል:: ስለዚህ ጋዜጣው በአንባቢዎች ዘንድ ተአማኒነት ለማሳደር የሚጥርና የሚተጋ ከሆነ የበሬ ወለደ ዜና ከማቀናበር ተቆጥቦ ሚዛናዊና በትክክለኛ መረጃ የተመሠረተ ዜና እንዲዘግብ እንጠይቃለን::

የአክሱም ዩኒቨርሲቲ)

ከክፍል-1 ገጽ 1 የዞረ

Page 42: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 42 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ማስታ

ወቂያ

ከክፍል-1 ገጽ 1 የዞረ

Invitation for Consultancy Services

Sky Bus Transport System Share Company would like to invite competent bidder in the following areas:

1. Installation and Implementation of Fuel Logo Management System

2. Automation of Ticket System• Bidders shall collected bid documents from Sky Bus Transport System

S.C. Head Office located at Kera Melka Building upon payment of Birr 100.00 with in ten working days after announcement of on the news paper.

• Bids must be accompanied by a 1% bid security of total bid amount in the form of CPO or cash.

• All bidders are required to provide renewed business license, vat registration certificate and tax identification number and other supporting relevant experience/recommendation

• Bidders must submit Technical and Financial proposal with wax-sealed envelop at or before 5:30 PM on or before February 27, 2013 to the Head Office located at Kera Melak Building.

• Bids will be opened in the presence of bidders and/or their official representatives who wish to attend on February 28, 2013 at 10:00 AM at Company Head Office located at Kera Melak Building.

• Sky Bus reserves the right to accept or reject any or all bids.

Sky Bus Transport System S.C., Tel. (0114) 673331, Addis Ababa

በውድነህ ዘነበ

ኢሕአዴግ በቀጣዩ ምርጫ አዲስ አበባ ላይ እንዲወዳደሩ አምስት ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን በዕጩነት አቀረበ:: ከእነዚህ ዕጩዎች መካከል የትራንስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ድሪባ ኩማ ቀጣዩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ እንዲሆኑ እየተጠየቁ መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል::

ሌሎች አራቱ ባለሥልጣናት የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ተፈራ ደርበው፣ የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ፣ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትሩ አቶ መኩርያ ኃይሌና የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ዳይሬክተር ጄነራል አቶ ወርቅነህ ገበየሁ ናቸው::

ኢሕአዴግ ከእነዚህ አምስት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ውስጥ አቶ ድሪባ ኩማን ለከንቲባነት ማጨቱን፣ ነገር ግን አቶ ድሪባ ከንቲባ ለመሆን ብዙም ፍላጎት እንዳላሳዩ ምንጮች ገልጸዋል::

ኢሕአዴግ አቶ ድሪባን ከንቲባ ለማድረግ የፈለገበትን ምክንያት ምንጮች ሲያስረዱ፣ በትራንስፖርት ሚኒስቴርና ተጠሪ በሆኑ መሥርያ ቤቶች ለውጥ ለማምጣት የሚያደርጉትን ትጋት ካጤነ በኋላ ነው:: በተጨማሪም አቶ ድሪባ የኦሕዴድ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሠሩ በመሆኑም ነው ተብሏል::

አዲስ አበባ ሙሉ በሙሉ ከኦሮሚያ ክልል ጋር የምትዋሰን በመሆኑና ከተማዋ በርካታ ጥቅሞችን ከኦሮሚያ ጋር የምትጋራ በመሆኑ፣ በቀጣዩ የሥራ ጊዜ ስለሚኖረው የተቃና አፈጻጸም የአቶ ድሪባ አስተዋጽኦ የተሻለ ይሆናል የሚል ታሳቢ ተደርጎ መሆኑን ምንጮች ይጠቁማሉ::

የተቀሩት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በዕጩነት የተያዙት በተለያዩ ምክንያቶች መሆኑን ምንጮች ይገልጻሉ:: ምንጮች እንደሚሉት፣ ኢሕአዴግ ምርጫውን እንደሚያሸንፍ ከወዲሁ አመላካች ሁኔታዎች ቢታዩም አማራጮችን ለመያዝ ሲል ነው ይላሉ:: በሌላ በኩል ኢሕአዴግ አዲስ አበባ

ላይ ትልቅ ሥራ እንደሚጠብቀው በማመን በየመሥርያ ቤቶቻቸው ጥሩ የሥራ አፈጻጸም ያላቸውን ባለሥልጣናት ወደ አዲስ አበባ ማዛወር ፈልጓል::

ኢሕአዴግ እነዚህን ባለሥልጣናት ካሉበት መሥርያ ቤት ማዛወር ባይፈልግ እንኳ፣ ለከተማው አስተዳደር ቅርብ ሆነው ሥራዎችን እንዲያግዙ ያደርጋል ይላሉ ምንጮች:: በሚያዝያ ወር አዲስ አበባንና ድሬዳዋን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች የአካባቢና የማሟያ ምርጫዎች ይካሄዳሉ::

ኢሕአዴግ ሙሉ በሙሉ ዕጩዎችን ቢያስመዘግብም፣ መድረክና መኢአድ ከምርጫው ውጭ በመሆን ላይ ናቸው:: ‹‹ኢሕአዴግ በምርጫው ላይ የተቃዋሚውን ሚና ትርጉም አልባ ቢያደርገውም ኢዴፓ በተፅዕኖ ከምርጫ ሥርዓቱ ተገፍቼ ላለመውጣት ስል ብቻ በአንድ ዕጩ ብቻ እወዳደራለሁ፤›› ሲል ኢዴፓ ሰሞኑን አስታውቋል::

በአገሪቱ የምርጫ ፖለቲካ ተሳታፊ ሲሆኑ የቆዩት እነዚህ ፓርቲዎች ምርጫውን በአብዛኛው ለኢሕአዴግ በመተው አፈግፍገዋል::

ምርጫውን ኢሕአዴግ ካሸነፈ ኢሕአዴግ ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረ በኋላ ስምንተኛው ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል:: ምክንያቱም አቶ ድሪባ ለጊዜው ከንቲባ ላለመሆን ቢያንገራግሩም ከፓርቲያቸው ውሳኔ ውጪ ስለማይሆኑ ነው ይላሉ ምንጮች ምክንያታቸውን ሲያስረዱ:: ምርጫው ከመድረሱ በፊት በአሁኑ ወቅት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው አምባዬ ከንቲባ ይሆናሉ የሚል መረጃ ወጥቶ ነበር::

ነገር ግን ያገኘነው መረጃ እንደሚያስረዳው አቶ ጌታቸውና ከንቲባ ኩማ ደመቅሳ በሚያዝያ 2005 ዓ.ም. ምርጫ ተወዳዳሪ አይደሉም::

ኢሕአዴግ ለአዲስ አበባ ምርጫ አምስት ከፍተኛ ባለሥልጣናትን አቀረበ

ሊኖር ይችላል፤›› ብለዋል::

ክትትሉ በተንታኞች መላምት ላይ ሳይሆን በተጨባጭ ማስረጃ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ያስረዱት ዶ/ር ቴድሮስ፣ ከመፈንቅለ መንግሥት ሙከራው በኋላ በአገሪቱ ሁለት ጉዳዮች ሊፈጠሩ እንደሚችሉ መረጃ እየተገኘ ነው ብለዋል:: ‹‹የተወሰኑ ጥገናዊ ለውጦችን አድርጐ ሥርዓቱን ማስቀጠል ሊኖር እንደሚችል እየሰማን ነው፤›› ሲሉ ሊፈጠር ስለሚችለው አንደኛው ጉዳይ ተናግረዋል::

ይህም ለአመራሩ ከባድ ሊሆን የሚችልና ሥልጣን እስከመልቀቅ የሚያደርሱ ሹም ሽሮችን በማድረግ ጥገናዊ ለውጥ ማድረግና ሥርዓቱን

ማስቀጠል ሊሆን እንደሚችል አስረድተዋል:: ‹‹በሌላ ወገን እየሰማን ያለነው ደግሞ ከዚህ የበለጠ ከባድ የሆነ ለውጥ ሊመጣ ይችላል፤ ይህም በአካባቢው ያለመረጋጋትን ሊያስከትል እንደሚችል ነው፤›› ብለዋል::

የገለጿቸው ጉዳዮች ተንታኞች በሚሰጡት መላምቶች ላይ የተመሠረቱ ሳይሆኑ የኢትዮጵያ መንግሥት በሚገነዘበው ደረጃና በተጨባጭ በመረጃ ላይ የተመሠረተ መሆኑን አስረድተዋል:: ክትትሉ በተጠናከረ መንገድ እንደሚቀጥል ይህም የኢትዮጵያን ሰላም ከማረጋገጥ ባለፈ የኢጋድ አባል አገሮችና የአካባቢውን ደኅንነት ባካተተ ሁኔታ ነው ብለዋል::

‹‹ከከሸፈው መፈንቅለ...

በዚህ ገንዘብ 25 ትላልቅ የመንገድ ፕሮጀክቶችን የማካሄድና የማስፈጸም ሥራ ይሠራበታል ይላሉ ምንጮች:: ነገር ግን የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር እንደሌሎች ዓመታት በዚህ ዓመት በመንግሥት ግምጃ ቤት ገንዘብ እንደሌለ በመጥቀስ፣ ለማንኛውም መሥርያ ቤት ተጨማሪ በጀት እንደማይሰጥ አስታውቋል::

የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩ አቶ ሱፊያን አህመድ ይህንን የሚኒስቴር መሥርያ ቤታቸውን አቋም በተገኘው አጋጣሚ ሲገልጹ ቆይተዋል::

‹‹ተጨማሪ በጀት የግድ ያስፈልገኛል›› ሲል በአቋሙ የፀናው የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ገንዘቡን የሚያገኝባቸውን ሁለት አማራጮች ነድፏል::

በመጀመሪያ ጉዳዩን በትራንስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ድሪባ ኩማ ለሚመራው

የባለሥልጣኑ ሥራ አመራር ቦርድ ማቅረብና አቅጣጫ መቀበል:: እንዲሁም ቦርዱ በሚሰጠው አቅጣጫ በቀጣይነት መጓዝ ነው:: ባለሥልጣኑ በሁለተኛ ደረጃ ያስቀመጠውና ገንዘቡን ለማግኘት ተስፋ የጣለው ጉዳዩን ወደ ኢኮኖሚና ፋይናንስ ክላስተር ማስተባበሪያ መውሰድ ነው::

በዚህ ክላስተር መመርያ የሚሰጣቸውና ያሉባቸው ዘርፈ ብዙ ችግሮች የሚፈታላቸው፣ የትራንስፖርት ሚኒስቴርና በሥሩ ያሉ መሥርያ ቤቶች፣ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴርና በሥሩ ያሉ መሥርያ ቤቶች፣ ግብርና ሚኒስትርና በሥሩ ያሉ መሥርያ ቤቶች ተጠቃሾች ናቸው::

ምንጮች እንደሚገልጹት ክላስተሩ ትልቅ ኃላፊነትና ሥልጣን ያለው በመሆኑ፣ ገንዘብ ሚኒስቴር ባለው አቅም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የጠየቀውን ገንዘብ ሊያቀርብ ይችላል::

በገንዘብ ሚኒስቴር ተስፋ የቆረጠው... ከክፍል-1 ገጽ 5 የዞረ

ማስታወቂያ ድርጅታችን ሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር (ኤም.ሲ.ሲ) ፈጣን የኮምፒውተር ፀሐፊዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡

የሥራ መደቡ፡- የኮምፒውተር ፀሐፊ /ሴክሬታሪ/

ተፈላጊ የት/ት ደረጃ፡- በጽሕፈት ሥራ አግባብ ያለው የሥራ

ልምድ ያላት፡፡

ተፈላጊ ችሎታ፡- በአማርኛና እግሊዝኛ ፈጣንና የታይፒንግ

ችሎታ እና በቂ የኮምፒውተር ችሎታ

ያላት፡፡

ደመወዝ፡- በስምምነት

የቅጥር ሁኔታ፡- በቋሚነት

ብዛት፡- 2

ከላይ የተመለከተውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን አንስቶ ባሉት 5 የሥራ ቀናት ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡

አድራሻ፡- ሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር (ኤም.ሲ.ሲ) ቦሌ መድሃኔዓለም ወደ ብራስ በሚወስደው መንገድ ከቦሌ

ኢንተርናሽናል ሆቴል አጠገብ በሚገኘው ሕንፃ 4ኛ ፎቅ፡፡ ፖ.ሣ.ቁ. 7023 አ.አ.

VISITethiopianreporter.com

Page 43: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 43 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1

ከክፍል-1 ገጽ 4 የዞረ ከክፍል-1 ገጽ 4 የዞረ

ከክፍል-1 ገጽ 4 የዞረ

ከክፍል-1 ገጽ 4 የዞረ

ከክፍል-1 ገጽ 4 የዞረ

አግባብ አልነበረም:: በአንድ አገር ውስጥ ሁለት አምባሳደሮች ተሹመው ነበር:: ከእነዚህ መካከል ምክትል አምባሳደሮቹ እንዲጠሩ ተደርጓል ብለዋል:: ‹‹ሥራ ለማቀላጠፍ ተብሎ ለበጐ ዓላማ የተወሰነ ነበር፤ ነገር ግን በአንድ አገር ሁለት አምባሳደር ሊኖር አይችልም፤›› ብለዋል:: ስህተት መሆኑን መንግሥት በመገንዘቡ በተጨማሪም በአሠራርም ጭምር ችግር በመፍጠሩ እንዲመለሱ መደረጉን አብራርተዋል:: እንዲመለሱ የተደረጉት አምባሳደሮች 18 ቢሆኑም ሁለቱ ግን በድጋሚ ወደ ሌሎች አገሮች እንደተመደቡ፣ የተቀሩት ግን እዚህ እንደሚገኙ ዶ/ር ቴድሮስ ለምክር ቤቱ ገልጸዋል::

‹‹እንዲመለሱ ስለተደረገ የግዴታ ወደ ሌላ አገሮች የሚመደቡበት አሠራር የለም፤›› በማለት በአዲስ አበባ ስለሚገኙት የተመለሱ አምባሳደሮች የወደፊት ዕጣ ፈንታ ተናግረዋል:: ወደ ሌላ አገር

ሊመደቡ የሚችሉት በመጀመሪያ ደረጃ በዚህ የዲፕሎማሲ የሥራ ዘርፍ ክፍት ቦታ ሲኖር ነው:: ከዚህ በተጨማሪም የግለሰቡ ፍላጐት እንዲሁም ለሥራ ዘርፉ የሚመጥን የግል ብቃት ሲኖር ብቻ እንደሆነ ተናግረዋል:: ከተመለሱት አምባሳደሮች ጋር መወያየታቸውን የተናገሩት ሚኒስትሩ፣ ከውይይቱም በድጋሚ ሊመደቡ ስለሚችሉበት አግባብ ግንዛቤ እንዳላቸው መረዳታቸውን ገልጸዋል::

ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት 47 የሚሆኑ የውጭ ዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች ሲኖሯት፣ በዚህ ዓመት ውስጥ ሦስት ተጨማሪ ኤምባሲዎችን የመክፈት ዕቅድ መኖሩን ሚኒስትሩ ገልጸዋል:: በመሆኑም ከተመለሱት አምባሳደሮች ጥቂቶቹ ለሚከፈቱት ኤምባሲዎች የሚመጥን ብቃት ካላቸው፣ ይህንን ዕድል ሊያገኙ እንደሚችሉ መገመት ቢቻልም ሚኒስትሩ ግን በዚህ ዙሪያ የተናገሩት የለም::

በአምባሳደርነት...

አባላት መሆናቸውና ቁጥራቸውም 800 መሆኑን ሰብሳቢው አስረድተዋል::

ካህናት፣ ምዕመናንና የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች በሚያቀርቡት የአባልነት ማስረጃ በዕጩ ፓትርያርክ ጥቆማ ከየካቲት 1 ቀን እስከ የካቲት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. ድረስ መሳተፍ እንደሚችሉ የገለጹት ሰብሳቢው፣ ካህናትና ምዕመናን ከየካቲት 1 እስከ 8 ቀን 2005 ዓ.ም. ድረስ አምላካቸውን በጸሎት እንዲጠይቁና ከየካቲት መባቻ ጀምሮ ለአንድ ሱባኤ የሚቆይ የጸሎት ጊዜ መታወጁንም አስታውቀዋል::

የስድስተኛው ፓትርያርክ ምርጫ ሐሙስ

የካቲት 21 ቀን ተካሂዶ በዚሁ ዕለት ከምሽቱ 12 ሰዓት የተመረጠው አባት በመገናኛ ብዙኀን አማካይነት ለሕዝብ ይፋ እንደሚሆን፣ በዓለ ሲመቱም እሑድ የካቲት 24 ቀን በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም ተጠቅሷል:: የመራጮች ቁጥር ባለፉት አምስት ፓትርያርኮች ምርጫ ከታየው በእጅጉ ከፍተኛ መሆኑም ተነግሯል::

ምርጫውን ቅዱስ ሲኖዶስ በምርጫ ሕጉ በወሰነው መሠረት የአራቱ እኅት አብያተ ክርስቲያናት [ግብፅ፣ ሶርያ፣ አርመን፣ ህንድ] የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ማኅበር፣ የአፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ተወካዮችና

በቋሚ ሲኖዶስ የሚመረጡ ምዕመናን እንዲታዘቡ መጋበዛቸውም ታውቋል::

የመጀመርያውን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስን በ1951 ዓ.ም. የመረጠችው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ባለፉት 53 ዓመታት አምስት ፓትርያርኮች ብፁዓን ወቅዱሳን አቡናት ባስልዮስ፣ ቴዎፍሎስ፣ ተክለሃይማኖት፣ መርቆሬዎስ የመሯት ሲሆን፤ አምስተኛው ፓትርያርክ የነበሩት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ (1928-2004) በመንበሩ ላይ 20 ዓመት ከቆዩ በኋላ ያረፉት ነሐሴ 10 ቀን 2004 ዓ.ም. እንደነበረ ይታወሳል::

ለስድስተኛው...

በየደረጃው የተቋቋሙ ኮሚቴዎች በፕሮግራም ግምገማ መመርያ መሠረት ወደሥራቸው የገቡ መሆናቸውና የፕሮግራሞችን ግምገማና ክለሳ የሚያደርጉት የየፕሮግራሞቹ ባለቤቶች መሆናቸው ታውቋል::

ሥርዓተ ትምህርቱና አተገባበሩን፣ የተማሪዎች ፈተናና ግምገማ አሰጣጥ፣ የፕሮግራሞች አደረጃጀትና አመራር፣ ግብዓት፣ ፋኩሊቲና ስታፍ፣ የመማርና ማስተማሩ ሒደት፣ ጥናትና የምሁራን ተሳትፎ የሚሉትን ጨምሮ እያንዳንዱ ፕሮግራም ዘጠኝ በሚጠጉ መስፈርቶች እየተገመገመ ነው::

በዚህ ዓመት ማብቂያ ይጠናቀቃል ተብሎ በሚጠበቀው የፕሮግራሞች ግምገማ ጠንካራ በሆኑ ፕሮግራሞች ላይ የበለጠ የማሻሻያ ሥራዎች ተሠርተው እንዲቀጥሉ፣ በየኮሌጆቹና በየትምህርት ክፍሎቹ ተመሳሳይ ፕሮግራሞች የሚከናወኑ ከሆነ እንዲወገዱና ወደ አንድ ጠንካራ ፕሮግራም እንዲመጡ ይደረጋል ተብሏል::

ፕሮግራሞቹ ሲገመገሙ ጥራት የተጓደለባቸው እንዲሻሻሉና ለአገሪቷ ዕድገት እምብዛም አስተዋጽኦ የማያደርጉ እንዲወገዱ እንደሚደረግ፣ በዚህ ሒደት ለአገሪቷ ልማት ድጋፍ ማድረግ የሚገባቸው ሌሎች ፕሮግራሞች ካስፈለጉ አዳዲስ ፕሮግራሞች የሚጨመሩበት አካሄድ እንደሚኖር ተገልጿል::

የፕሮግራም ግምገማው በአብዛኛው የሚያተኩረው በድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች ላይ መሆኑን፣ 172 የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞችም በግምገማው የሚያልፉ መሆናቸው ታውቋል:: ዩኒቨርሲቲው የጥራት መጓደል ይታይባቸዋል በሚላቸውና በተደራረቡ የቅድመ ምረቃ (የመጀመሪያ ዲግሪ) ፕሮግራሞች ላይም ግምገማ እየተደረገ ይገኛል::

በተያዘው ዓመት የፕሮግራም ግምገማው አልቆ በቀጣዩ ዓመት ፕሮግራሞቹን የማስተካከልና የመተግበር ሥራ ውስጥ ለመግባት መታቀዱን ዶ/ር ጄሉ ገልጸዋል::

በድኅረ ምረቃ 172፣ በዶክትሬት 71 እንዲሁም በሰብ ስፔሻሊቲ 23 ፕሮግራሞች ሲኖሩ፣ በድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ከ10 ሺሕ በላይ ተማሪዎች እንደሚማሩ ተገልጿል::

አዲስ አበባ...ከክፍል-1 ገጽ 4 የዞረ

ለኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ ለየት ያለ የሐቲት (Discourse) መንገድ በማራመድ ይታወቃሉ:: ከሠሯቸው ጥናቶች ሌላ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በማስተማሪያነት የሚያገለግለውን ‹‹አማርኛ በኮሌጅ ደረጃ›› ከሌሎች ምሁራን ጋር በመሆን ያዘጋጁት ይጠቀሳል:: በአማርኛና በእንግሊዝኛ ግጥሞቻቸው የኮሌጅ ቀን ግጥሞችን ጨምሮ የሚታወቁት ዶክተር ዮናስ በአሜሪካ በ1980 ዓ.ም. ‹‹ጉራማይሌ›› የተሰኘ የአማርኛ ግጥሞች መድበልም አሳትመዋል:: ቀደም ሲል የወንድማቸውን የዮሐንስ አድማሱ ‹‹እስኪ ተጠየቁ›› የተሰኘውን የግጥም መድበል አሰናድተው ያሳተሙ ሲሆን፣ የባለቅኔና ጸሐፌ ተውኔት ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ የሕይወት ታሪክና ሥራ የሚያወሳውን የወንድማቸውን ሌላኛውን መጽሐፍ ያሳተሙ ሲሆን፣ ከ10 ቀናት በኋላ ለማስመረቅ በዝግጅት ላይ ነበሩ::

ከአባታቸው አቶ አድማሱ ኃይለ ማርያምና ከእናታቸው ወይዘሮ ጌጤነሽ ቸኮል ኅዳር 6 ቀን 1936 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ የተወለዱት ዶክተር ዮናስ ሥርዓተ ቀብር እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005 ዓ.ም. እንደሚፈጸም ታውቋል::

በሌላ ዜናም በአዲስ አበባ በባህል ሕክምና ታዋቂ የነበሩት ሐኪም ማሞ ኃይሌ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል:: በ1910 ዓ.ም. በሰሜን ሸዋ ቡልጋ የተወለዱት ሐኪም ማሞ በፋሺስት ጣሊያን ወረራ ጊዜ በአርበኝነት ማሳለፋቸው ከዜና ሕይወታቸው የተገኘው መረጃ ያመለክታል:: የሐኪም ማሞ ሥርዓተ ቀብር እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005 ዓ.ም. እኩለ ቀን ላይ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም ታውቋል::

ዕውቁ የሥነ...

ሥራዎችን ዋጋ ትመና በኤጀንሲው አሠርቶ ከሕንፃው መወረስ በኋላ ለማጠናቀቅ የወጣው በዚህ 474,372 ብር ሲሆን፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ግን ለሕንፃው ማጠናቀቂያ 510,211 ብር አውጥቻለሁ በማለት በኤጀንሲው ትመና ላይ ቅሬታውን አቅርቧል:: አስተዳደሩ አወጣሁ ያለው ወጪና የኤጀንሲው ባለሙያዎች ማስረጃ ያገኙለት ወጪ መካከል የ35,839 ብር ልዩነት በማሳየቱም ሕንፃውን ለመረከብ እንደ ክፍተት ሆኖ ጉዳዩ በእንጥልጥል ቆይቷል::

ከውርስ በኋላ ወጣ የተባለውን ወጪ የሕንፃው ባለቤቶች በወቅቱ ለመክፈል የሚያስችለው አቅም ባለመኖሩና በምክር ቤቱና በጫት ላኪዎች መካከል የነበረው አለመግባባት ጉዳዩን ተከታትሎ ለማስፈጸም እንዳላስቻለም ተገልጿል:: ሕንፃው እንዲመለስ ሁለቱ ወገኖች የነበራቸውን ልዩነት አስወግደው መንቀሳቀስ ከጀመሩ በኋላ ግን በፈለጉት ፍጥነት ሕንፃውን ማስመለስ አልቻሉም:: ሕንፃው ይመለስ ከተባለ በኋላ አስተዳደሩ በሕንፃው የተጠቀመበት ጊዜ በኪራይ ተተምኖ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንረከብ የሚለውን አካሄድ መርጠውም ስለነበር ጉዳዩ እንደገና ተጓትቷል::

ካሳለፍነው ዓመት ወዲህ ግን ንግድ ምክር ቤቱ አቋሙን በመለወጥ ለሕንፃው ወጣ የተባለውን ወጪ ሸፍነው ሕንፃውን ለመረከብ በድጋሚ ጥያቄ አቅርበዋል:: በዚህ ጥያቄ መሠረት ባሳለፍነው ሳምንት የሕንፃው ጉዳይ የመጨረሻ ውሳኔ እንዲሰጥበት ለኤጀንሲው ቦርድ መመራቱን ያገኘነው መረጃ ያስረዳል::

የድሬዳዋ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ወንድወሰን ዘለቀ እንደገለጹት፣ ከዚህ በኋላ ሕንፃው የማይመለስበት ምክንያት የለም:: የድሬዳዋ ንግድ ኅብረተሰብ ሕንፃችን ይመለስ የሚለውን ጥያቄ ይዞ እየወተወተ ነው:: ሕንፃው ያልተመለሰበት ምክንያት ግልጽ ባለመሆኑም የንግድ ምክር ቤቱ አባላት ይህንን እንኳን ማስመለስ አትችሉም ወይ? እያሉ ጫና እያሳደሩባቸው መሆኑንም ገልጸው፣ መንግሥት የኢትዮጵያን ንግድ ምክር ቤት ሕንፃን በመለሰለት አግባብ የእኛንም ይመልስ በማለት ጥያቄያቸውን አቅርበዋል::

ባለመኖሩ ሲሆን፣ የሕንፃው ባለንብረት የሆኑት ሁለቱ ተቋማት በመካከላቸው የተፈጠረው አለመግባባትም ጉዳዩ እንዲጓተት ማድረጉ ታውቋል::

የሕንፃው ባለቤቶች እኛ በመሆናችን ሊመስልን ይገባል በማለት ጉዳዩን በመከታተል ላይ የሚገኘው የድሬዳዋ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት፣ ከአገር አቀፍ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ጋር በመሆን ሕንፃው እንዲመለስለት የተደረገው እንቅስቃሴ ለውጥ በማምጣቱ ሕንፃውን የማግኘት ዕድሉ ሰፊ መሆኑም ተጠቅሷል::

በድሬዳዋ የንግድ ኅብረተሰብ የተገነባው ሕንፃ የተወረሰው በ1981 ዓ.ም. መሆኑን መረጃዎች ሲያመላመላክቱ፣ በወቅቱ የተወረሰውም በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ፍቅረ ሥላሴ ወግደረስ ፊርማ ከአዋጅ ውጭ በተጻፈ ደብዳቤ እንደሆነ ያሳያል:: ኅዳር 19 ቀን 1981 ዓ.ም. ተጻፈ የተባለው ደብዳቤ ሕንፃው በድሬዳዋ ራስ ገዝ ለተቋቋመው የሸንጐው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴና ፕላን

ኮሚቴ እንዲሰጥ የሚገልጽ ነበር::

ከደርግ ውድቀት በኋላም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እየተጠቀመበት ይገኛል:: የሕንፃው ባለንብረቶችም የሕንፃውን መወረስ በመረጃ ጭምር በማስደገፍ እንዲመለስላቸው ጥያቄ ያቀረቡት በ1988 ዓ.ም. ነው::

ከአዋጁ ውጭ የተወረሱ ቤቶችን ለመመለስ ሥልጣን ለተሰጠው የኢትዮጵያ ፕራይቬታይዜሽንና የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲም ጉዳዩን በመመልከት፣ የሕንፃው ባለቤቶች መሆናቸውን በማረጋገጥ በመርህ ደረጃ እንዲመለስ የወሰነው ደግሞ በ1994 ዓ.ም. ነበር::

ይሁን እንጂ ኤጀንሲው ከዚህ ውሳኔው ጐን ለጐን ሕንፃውን መንግሥት ከወረሰው በኋላ በመንግሥት በጀት ለሕንፃው ማስጨረሻና ለተሠሩ አዳዲስ ግንባታዎች ወጪ በመደረጉ የሕንፃው ባለቤቶች ይህንን ወጪ መሸፈን አለባቸው የሚል ውሳኔ አስተላልፎ ነበር::

ኤጀንሲው የሕንፃውን የማስፋፊያ

የድሬዳዋ የንግድ...

በድሬዳዋ የንግድ ኅብረተሰብ የተገነባው ሕንፃ

ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የሕግ አማካሪ ዶ/ር ፋሲል ናሆምን ጨምሮ የመጀመሪያዎቹ አምስት ዙር ተመራቂዎች የሕይወት ልምዳቸውን፣ እንዲያካፍሉና ጥናታዊ ሥራዎችን እንዲያቀርቡ ለማድረግ ዕቅድ መያዙንም ዶ/ር ታደሰ ለሪፖርተር ገልጸዋል::

የሕግ ትምህርት...

Page 44: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 44 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ማስታ

ወቂያ

ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ማስታወቂያ

ቁጥር ዘባ/01/2013

ተ.ቁ የተበዳሪዉ ስም

የአስያዥ ስም

የንብረቱ አድራሻ

የሰሌዳ ቁጥር የሻንሲ ቁጥር የሞተር ቁጥር

የተሰራበት ሀገርና ዘመን

የተሽከካሪው አይነት

የሀራጅ መነሻ ዋጋ ሐራጅ የሚከናወንበትŸ}T ¡/Ÿ}T kuK?

¾u?ƒ.lØ`

1

አቶ ግዛቸዉ መኴንንት ገ/የሱስ (ጊዜ ኮንሰትራክሽን)

አቶ ግዛቸዉ መኴንንት

አ.አ ቦሌ 06 725

ኮድ 3-66407

KMJWA37HABU280911 D4BHA037755ኮሪያ 2010 እ.ኤ.አ.

ሃዩንዳ ሚኒባስ

(አዉቶብስ)301,860.00

ቀን ሰዓት

ተሸከርካሪዉ የሚገኘዉ በዘመን ባንክ አ.ማ ግቢ ዉስጥ ነዉ

የካቲት 14 ቀን 2005 ዓ.ም

3፡30-5:30

ማሳሰቢያ1. ተጫራቾች የመነሻ ዋጋዉን 1/4ኛ (አንድ አራተኛ) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተመሰከረለት የክፍያ ማዘዣ /ሲፒኦ/ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፡፡2. አሸናፊ የሆነዉን ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በ15 ቀናት /በአስራአምስት ቀናት/ ዉስጥ አጠቃሎ ካልከፈለ ያስያዘዉ ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ሀራጁ ይሰረዛል፡፡3. አሸናፊዉ ለመጋዘንና ለቢሮ አገልግሎት የሚዉለዉን ህንፃ እና በተሸከርካሪዉ ላይ ባሸነፈበት ዋጋ 15% የተጨማሪ እሴት ታክስ የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡4. ባንኩ ንብረቱን ለገº¬ ስም እንዲዞር ለሚመለከተዉ መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይፅፋል፡፡5. ጨረታዉ የሚካሔድበት ቦታ በሰንጠረዡ ላይ በተመለከተዉ አድራሻ ነዉ፡፡6. የተጫራቾች ምዝገባ ከጠዋቱ 3፡30 - 4፡30 ብቻ ይከናወናል፡፡7. ተጫራቾች ቤቱን ከጨረታዉ ቀን በፊት ባንኩ በሚያወጣዉ ፕሮግራም መሰረት መጎብኝት ይችላሉ፡፡8. ለተጨማሪም መረጃ በስልክ ቁጥር 0115540043/49 የዉስጥ መስመር 200/207 ወይም በሞባይል 0911152490 ደዉለዉ መጠየቅ ይችላሉ፡፡««««

ዘመን ባንክ አ.ማ

ከክፍል-1 ገጽ 3 የዞረ

ማሳደግ መቻላቸውን የሚያሳይ ነው::

ካለፈው ዓመት የስድስት ወራት እንቅስቃሴያቸው ጋር ሲነጻጸር የዘንድሮው ዕድገት አሳይቷል ተብሏል:: በተለይ የተቀማጭና የብድር መጠን ዕድገቱ ከ30 በመቶ በላይ እንደደረሰ ተጠቁሟል::

የ27 በመቶው የቦንድ ግዥ ባይኖር ኖሮ የባንኮቹ ውጤት አሁን ተገኘ ከተባለው የበለጠ ይሆን ነበር:: ባንኮቹ በ27 በመቶው አስገዳጅ የቦንድ ግዥ ያዋሉት ወደ 15 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ መንግሥት ሦስት በመቶ ወለድ የሚከፍልበት ነው:: ባንኮቹ ግን ገንዘቡን ቢያበድሩ በአነስተኛ ተመን በ12 በመቶ ሊያሳድጉት ይችሉ ነበር:: ከዚህ የሚገኘው ትርፍ ከፍተኛ ከመሆኑ ጋር ሲያያዝ 27 በመቶ ጉዳት እንዳለው የሚገልጹ አሉ::

በሌላ በኩል የቦንድ ግዥው የባንኮችን ገንዘብ እየወሰደ ባለበት ጊዜ ባለፉት ስድስት ወራት እንቅስቃሴያቸው ባንኮች የብድር መጠናቸው ሊያድግ የቻለበት ዋና ምክንያት፣ የተቀማጭ ገንዘብ መጠናቸውን ማሳደግ በመቻላቸው መሆኑን የባንክ ባለሙያዎች ይጠቁማሉ::

በዚህ ወቅት የተቀማጭ ገንዘብ ዕድገት መታየቱ ባንኮቹ በ27 በመቶ የቦንድ ግዥ ያጡ የነበረውን ጥቅም በተወሰነ ደረጃም ቢሆን እንዲያረግብላቸው ማድረጉንም ባለሙያዎቹ ጠቁመዋል::

የባንኮች የቦንድ...

ሕክምናዎችን በመፈለግ ወደ ህንድ እንደሚመጡ የገለጹት አቶ መታሰቢያ፣ ‹‹ርካሽ የሕክምና አገልግሎት ለማግኘት የሚመጡት ታካሚዎች እዚህ ከደረሱ በኋላ የሚጠየቁት ዋጋ ከፍተኛ ነው፡፡ የሕክምና ጥራቱም ዝቅተኛ በመሆኑ ዜጐች እየተጉላሉ ይገኛሉ፤›› ብለዋል፡፡

ታካሚዎቹ በህንድ ወዳለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የሚመጡት ችግር ሲደርስባቸው ብቻ በመሆኑ፣ ይህንን የሕክምና አገልግሎት ለመጠቀም ምን ያህል ዜጐች ወደዚያ እንደሚያቀኑ ለጊዜው እንደማይታወቅ አቶ መታሰቢያ አስታውቀዋል፡፡ በመሆኑም ታካሚዎች ለሕክምና ወደ ህንድ መሄድ በሚፈልጉበት ወቅት በቅድሚያ ሆስፒታሎቹ ደረጃቸውን የጠበቁና ታዋቂ መሆናቸውን ማረጋገጥ አለባቸው ብለዋል፡፡ ይህንንም ለማድረግ የጤና ጥበቃን ወይንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን አልያም በኢትዮጵያ የህንድ ኤምባሲን ማማከር እንዳለባቸው አክለው አስታውቀዋል፡፡

‹‹በቅርቡ ሦስት ሰዎች ሦስት ወር ሙሉ ሕክምና ሳያገኙ ቆይተዋል፡፡ በዚህም ከደረሰባቸው እንግልት በተጨማሪ የዜጐች ገንዘብ ያላግባብ ባክኗል፤›› ያሉት አማካሪው፣ አሁን ያለው የሁኔታው አዝማሚያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየባሰ በመምጣቱ ዜጐች እንዲጠነቀቁ አሳስበዋል፡፡

በርካታ ታካሚዎች ወደ ህንድ የሚሄዱት ከሰው በሚያገኙት መረጃ በመሆኑ፣ ከእንግልትና ከአላስፈላጊ ወጪ እንዲድኑ አስቀድመው ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚኖርባቸው መንግሥት አስገንዝቧል፡፡

መንግሥት...ከክፍል-1 ገጽ 3 የዞረ

ከክፍል-1 ገጽ 3 የዞረ

ማለት አይቻልም ሲሉ፣ በሙሉ አቅማቸው በምርጫው ተሳተፊ ያልሆኑበትን ምክንያት ገልጸዋል::

የቀድሞው የኢዴፓ ፕሬዚዳንትና በአሁኑ ወቅት የሥራ አስፈጻሚ አባል የሆኑት አቶ ልደቱ አያሌው ለትምህርት ከሄዱበት አገር ቢመለሱም፣ በምርጫው ሒደት ዘግይተው በመምጣታቸው ተሳታፊ አለመሆናቸው ታውቋል::

ኢዴፓ...

Page 45: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 45 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1

ፎቶ ዜና

የመከላከያ ሠራዊት ቀንን አስመልክቶ ባለፈው ዓርብ በሠራዊቱ የተገጣጠሙ የተለያዩ ዓይነት ተሽከርካሪዎች በዓውደ ርዕዩ ላይ ቀርበው ነበር ፎቶ በሪፖርተር/ናሆም ተስፋዬ

Page 46: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 46 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ስፖርት ስፖርት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ከ31 ዓመታት በኋላ ለ29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቅቶ ተመልክተናል:: በውጤቱም የተለያዩ አመለካከቶች እየተደመጡ ነው:: የቡድኑ አሠልጣኝ እንደመሆንዎ ውጤቱን እንዴት ይገልፁታል?

የኢትዮጵያ ቡድን ከረጅም ዓመታት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ የሚያበቃውን ውጤት ለማግኘት ከቅድመ ማጣሪያ ጀምሮ የተለያዩ ውድድሮች አድርጎ ነው ወደ ደቡብ አፍሪካ ያመራው:: ክንውኑም ከአሁን በኋላ ታሪክ ሆኖ ይቀመጣል:: ታሪክ ደግሞ መቼም ቢሆን በጥሩም ሆነ በመጥፎ ሲነሳ የሚኖር ነው:: የኢትዮጵያ እግር ኳስ ግን ከእንግዲህ በኋላ ወደኋላ ተመልሶ እንዳለፉት ዓመታት ተመልካች እንዳይሆንና ወደ ተሻለ ደረጃ ማሸጋገር ይቻል ዘንድ ጥረት ማድረግ የግድ ነው:: ከሁሉም ወገን ከፍተኛ ርብርብ ይጠበቃል:: በደቡብ አፍሪካ ቆይታችን እኔም ሆንኩ ተጫዋቾቼ እጅግ በጣም ብዙ ነገር ተምረናል:: ቡድናችን በመድረኩ የካበተ ልምድ ካላቸው ቡድኖች ጋር ሲወዳደር ታይቷል:: በእንቅስቃሴው በውጭም ሆነ በአገር ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ያልጣማቸው እንደተጠበቁ ሆኖ ጅምሩን አድንቀዋል:: መንግሥትም ምስጋናውን ሰጥቷል:: ከእንግዲህም መሥራት ከተቻለ የተሻለ ደረጃ መድረስ እንደምንችል፣ በአገሪቱ የተግባር እንጂ የክሕሎት ችግር እንደሌለ አረጋግጠናል::

ውጤቱ አርክቶኛል እያሉ ነው?በፍጹም በውጤቱ አልረካሁም:: ከዚህ በላይ መሔድ

የሚያስችል፣ ነገር ግን በራሳችን ጥቃቅን ስሕተቶች ልጆቹም አቅም እያላቸው መሔድ ሳንችል ቀርተናል:: እግር ኳስ ነውና መቀበል የግድ ነው:: ቁም ነገሩ ካለፈው ስሕተታችን መማሩ ላይ ነው:: ምክንያቱም በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ለዋንጫው ከፍተኛ ግምት ከተሰጣቸው አይቮሪኮስት ትጠቀሳለች:: የእግር ኳስ ባሕሪ ነውና የተመለከትነው በተቃራኒው ነው:: እንደ ኢትዮጵያ በዙሩ ጨዋታ የተሰናበቱ፣ ነገር ግን ጥሩ የተንቀሳቀሱ ዲሞክራክት ኮንጎ፣ ሞሮኮ፣ አልጄሪያ፣ አንጎላና ሌሎችም አልተሳካላቸውም:: ይህ ማለት የእግር ኳስ ባሕሪ የሚፈጥረው ነው:: ከዚህ አንፃር ልጆቻችን ቀደም ሲል እንደገለፅኩት ድክመቶቻችን እንደተጠበቁ፣ ሜዳ ላይ ባሳዩት ብቃት ታላላቅ መገናኛ ብዙሃን ሳይቀር አድናቆታቸውን ቸረዋቸዋል:: በዚህ ረክቻለሁ፣ ነገር ግን ውጤቱ አላረካኝም:: ምክንያቱም ከዚያም በላይ መሔድ የሚችል አቅም ስለነበረን ነው::

ተጫዋቾቼ ከዚህ በተሻለ መሔድ ይችሉ ነበር ካሉ ለተፈጠረው ድክመት ምክንያት የሚሉትን ቢገልጹልን?

ባለፈ ነገር ተብሎ እንዳይተረጎምብኝ እንጂ ድክመቶቻችን ለቡርኪና ፋሶ ከነበረን ግምት ይጀምራል:: ቡርኪና ፋሶ ለፍጻሜ የደረሰ ቡድን ሆኗል:: ገና ወደ ደቡብ አፍሪካ ሳንሔድ ከሚዲያው ሳይቀር የኢትዮጵያ ቡድን ከዛምቢያና ናይጀሪያ ነጥብ ተጋርቶ ቡርኪና ፋሶን አሸንፎ ከምድቡ ማለፍ እንደሚችል የተሳሳተ ግምት ነበር ሲነገር የነበረው:: ያለምክንያትም አልነበረም:: የቡርኪና ፋሶ ተጫዋቾችን በወዳጅነትም ሆነ በሌላ አጋጣሚ አልተመለከትናቸውም:: ለተመለከትናቸው ዛምቢያና ናይጀሪያ መሥራት ያለብንን ሠርተን ቡርኪና ፋሶን ግን በቀላሉ እንደምናሸንፍ ራሳችን እንድናሳምን ሆነ፣ እኔም ሆንኩ ልጆቼ ተመሳሳይ ስሜት ነበረን:: መሥራት ያለብንን ሳንሠራ እምነት መጣል እጅግ በጣም ትልቅ ስሕተት ነው:: ለወደፊቱም ትልቅ ትምህርት ሰጥቶናል::

ከቡርኪና ፋሶ ጋር በነበራችሁ ጨዋታ በመጀመሪያዎቹ 20 እና 25 ደቂቃዎች በኳስ ቁጥጥር ተሽላችሁ ነበር:: ነገር ግን መዝለቅ አልቻላችሁም?

እውነት ነው:: ጨዋታው ሲጀመር ቀለውን ስለነበር ልጆቻችን መከፋፈት ጀመሩ:: እንደተመለከትነው ሺመልስና ሳላዲን ሰይድ በቀላሉ ጎል መሆን የሚችሉ ኳሶች አምልጧቸዋል:: ለተጨማሪ ሙከራ ጫና ማድረግ ነበረብን:: በክፍተቶቻችን ሊጠቀሙብን ቻሉ::

ክፍተቱን ማስተካከል የማን ድርሻ ነበር?ምክንያት ለማቅረብ ሳይሆን፣ ድክመቱ ከእኔ

ጀምሮ የሁላችንም ነው:: ማስተካከል አልቻልንም፣ ቀላል ኳሶች ሳይቀር እየተነጠቁ ጎል ተቆጥሮብናል:: ማስተካከል ያለብን ድክመት ነው:: ተጫዋቹም በሒደት ዓለም አቀፍ ልምድና ተሞክሮን እያጎለበቱ ሲሔዱ የሚቀረፍ ነው:: ጥሩ ትምህርት ሰጥቶን እንዳለፈ ክስተት ነው የምወስደው::

ዓለም አቀፍ ልምድ እጦት ለድክመታችን መንስዔ ሆኗል እያሉ ነው?

ግልፅ ነው:: ለምሳሌ ከናይጀሪያ ጋር በነበረን ጨዋታ፣ በጨዋታ ተበልጠን አልነበረም ጎል

የተቆጠረብን:: ጨዋታውን እንደተመለከትነው እስከ 80ኛው ደቂቃ ድረስ 0ለ0 ነበርን:: ጎል ማስቆጠር ካልቻልን አቻ አይጠቅመንም:: ጎል ለማግባት ደግሞ ሰዓቱም በመጠናቀቅ ላይ ስለነበር የተጫዋቾቻችን በስሜት መሳብ ለጎሉ መቆጠር ምክንያት ሆነ:: ናይጀሪያውያን በልምድ የተሻሉ ስለነበሩ በክፍተቶቻችን ተጠቀሙ:: ልብ ብለን ከሆነ እስከ 80ኛው ደቂቃ ሳላዲን ሰይድን ለሦስት ሲይዙት ነበር:: የእኛ ልጆች እየተነገራቸው ቦታቸውን ማስጠበቅ ተስኗቸው ነበር:: የእኛ ተጫዋቾች ናይጀሪያውያኑን ከጨዋታ ውጭ ለማድረግ የቦታ አጠቃቀማቸው በራሱ ከፍተኛ ችግር ነበረበት:: እነዚህ ሁሉ ከልምድ ማነስ የመጡ ናቸው እንጂ ልጆቻችን መጫወት ተስኗቸው አልነበረም:: እነዚህና ሌሎችም በርካታ ድክመቶቻችንን በቀጣይ በምናደርጋቸው የወዳጅነትና መደበኛ ውድድሮች የሚቀረፉ እንደሚሆኑ የፀና እምነት አለኝ::

የኢትዮጵያ ቡድን በውድድሩ ሦስት ጨዋታዎችን አድርጓል:: በሦስቱም ጨዋታዎች የመጀመሪያ ተሰላፊ ተጫዋቾችን ከመምረጥ ጀምሮ የጨዋታውን አጠቃላይ ድክመትና ጥንካሬ እንዴት ይገልፁታል?

ሲጀመር ዛምቢያ ያለፈው ዓመት የአፍሪካ ሻምፒዮን ነው:: ጠንካራ ቡድን መሆኑን እናውቃለን፣ ክብደትም ሰጥተንዋል:: ጨዋታው ከባድ እንደሚሆን ግምት ነበረን:: እንቅስቃሴያችንም ጥንቃቄ የተመላበት ነበር:: ጀማል ጣሰው (በረኛው) በቀይ የወጣው ጨዋታው 40 ደቂቃ እየቀረው ነው:: በአሥር ልጆች የአሰላለፍ ሽግሽግ ተደርጎ በጥሩ የኳሱ ቅብብል ውጤቱን አስጠብቀን መውጣት ችለናል:: በወቅቱ የነበረው የሙቀት መጠን 35 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ ነበር:: በዚያ ላይ ልጆቻችን የነበራቸውን ሁሉ አሟጠው ተጠቅመዋል:: ብዙዎቹ ልጆች ወደ አቋማቸው ለመመለስ 48 ሰዓት መጠበቅ ነበረባቸው:: እኛ ደግሞ በየቀኑ ለአንድ ሰዓት ያህል ልምምድ ማድረግ የግድ ነበር:: በዚህ የተነሳ ክፍተቱን ለማስተካከል ለቡርኪና ፋሶ ጨዋታ የግድ የተወሰኑ ልጆችን መለወጥ ነበረብን:: ያስገባናቸው ልጆችም ቢሆኑ ኳስ ተቆጣጥሮ መጫወት የሚችሉ ለመሆናቸው በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች ተመልክተናቸዋል:: ነገር ግን ቀደም ሲል ለመግለጽ እንደሞከርኩት ሳናሸንፋቸው እንደምናሸንፋቸው አምነን የገባንበት ስለነበር ውጤቱ በታየው መልኩ ሊጠናቀቅ ችሏል:: ሦስተኛውንና ከናይጀሪያ ጋር ያደረግነውን ጨዋታ በተመለከተ ብዙዎቹ ተጫዋቾች ከድካማቸው አገግመው ስለነበረ ጨዋታውን ቢያንስ 1ለ0 ለማጠናቀቅ ተነጋግረን ነው የገባነው:: ናይጀሪያውያኑም የታክቲክ ተጫዋቾች በመሆናቸው ተቆጣጥረን ለመጫወት አልከበዱንም:: በኳስ ዓለም ከባዱ ከታክቲክ ውጭ እንደ ጎርፍ የሚመጣ ቡድን ለመቆጣጠር አስቸጋሪ ነው:: ነገር ግን ማን የት እንደሚጫወት ከታወቀ አያስቸግርም:: በዋናነት ደግሞ ልጆቹ በቡርኪና ፋሶ ላይ የሠሩት ስህተት ስላስቆጫቸው ለናይጀሪያ ጥንቃቄ አድርገው የገቡበትና ጥሩም የተንቀሳቀሱበት ነበር የነበረው::

የኢትዮጵያ ቡድን በሥነ ልቦናውም ሆነ በአካል ብቃቱ

ረገድ ብዙ እንደሚቀረው ለዚያም ቡድኑ የግጥሚያ ቡድን እንዳልሆነ ማሳያው በቡርኪና ፋሶ ጨዋታ፣ ጨዋታውን በጀመረበት ትንፋሽ ሊጨርስ አልቻለም:: ሌላው ደግሞ ጎል ሲቆጠርበት ተረጋግቶ ከመጫወት ይልቅ ሲደነባበር ታይቷል:: ይህስ እንደመከራከሪያ ሊቀርብ አይችልም?

ክርክር የሚወድ መከራከሪያ አያጣም:: ማንም ሰው የሚመስለውን መናገር ይችላል:: ነገር ግን የሚመስለውን ስለተባለ ብቻ ፍሬ የማይቋጥር መከራከሪያ ማቅረብ ትርፉ ጊዜ ማጥፋት ነው:: ወደ ጥያቄው ስመለስ ሥነ ልቦና ስለተባለው ባለሙያ አብሮን ተጉዟል:: ባለሙያው በየጊዜው ከተጨዋቾቹ ጋር እየተገናኘ ማድረግ ያለበትን አድርጓል:: ዋናውና ለድክመቱ መፈጠር የዛምቢያን ጨዋታ ተከትሎ አድናቆት መብዛቱ ነው:: ከአቅም በላይ መካብ ይዞት የሚመጣው ችግር አደገኛ ነው:: እውን ሆኖ ያየነውም ይኼው ነው::

የአድናቆቱ ትርጉም ገብትዎት ከሆነ ተጫዋቾቹ ጥንቃቄ እንዳያደርጉ ማዘናጊያም ሊሆን ስለሚችል የማስረዳት ኃላፊነት አልነበረብዎትም?

በሚገባ ተናግሬያለሁ:: ሠርተናል ብለን እንዳንኩራራ መድረክ ፈጥረን አውርተናል:: መኩራራት የሚገባን ለሕዝባችን ቃል የገባነውን አሳክተን ስንገኝ ሊሆን እንደሚገባው ተነጋግረናል:: ምክንያቱም ተጋጣሚያችን የተቻለውን ሁሉ ለማድረግ ጥርሱን ነክሶ ስለሚመጣ ማለት ነው::

በሦስት ጨዋታ ሙሉ 23 ተጫዋቾችን የተጠቀመ የመጀመሪያው አሠልጣኝ የሚሉ አሉ:: እውን እርሶ የመጀመሪያ ተመራጭ አሥራ አንድ ምርጥ ነበረዎት ማለት ይቻላል?

ያለኝን ኃይል መጠቀሜ አሪፍ ያስብለኛል እንጂ አያስተቸኝም:: ምክንያቱም አሥራ አንድ ልጆች ሲፋለሙ የተቀረው አብሮ የተጓዘው ሸሚዝ ሊገዛ ነው? አዳነ ወይም አስራት ሲጎዱ ሁለቱን ተጫዋቾች ተክተው የሚገቡ ተጫዋቾች ተጠባባቂ ነን ብለው እንዲያስቡ ፍላጎት የለኝም:: አዳነም ሆነ አስራት አልያም ምንያህል ከ23ቱ ተጫዋቾች እኩል ናቸው:: ተክተው የሚጫወቱ ልጆች የ23ቱ ልጆች አባላት ናቸው:: እንዲያውም ሁሉንም መጠቀም መቻል ጉልበት ለመቆጠብ አማራጭ ነው:: መታየት ያለበት የ23ቱ ልጆች አባል የተደረገው ተጫዋች ብቃት ሳይኖረው ከሆነ መነጋገር ይቻላል:: ችሎ የተመረጠ ከሆነ ግን ለምን ተሰለፈ ማለት ከሆነ እቸገራለሁ:: ዋናው ነገር የገቡት ሁሉ ኃላፊነታቸውን በሚገባ ተወጥተዋል አልተወጡም የሚለው ስለሆነ በቀጣይ የተሻለውን ይዞ ለመቀጠል ጠቃሚ ነው:: ጥያቄው መነሻ አለው፣ ምክንያቱም በርካታ አሉባልታዎች እሰማለሁ:: አሥራ አንድ ምርጥ የለውም የሚባል ነገር አለ:: ምን ማለት እንደሆነ ግልፅ አይደለም:: ከዛምቢያ ጋር የተጫወተው ቡድን ምርጥ አሥራ አንድ አይደለም? ጉዳትና ድካም ሲፈጠርስ መቀየር የለበትም?፣ የገቡትስ ምርጥ አሥራ አንድ አይደሉም?፣ ካልሆኑ የቡድኑ አባል ሆነው መሔዳቸው ስህተት ነበር ማለት ነው:: አዳነ

ግርማና አስራት መገርሳ ተጎዱ፣ ጀማል ጣሰው በቀይ ወጣ መተካት የለባቸውም? ወይስ በሽተኞቹን በመርፌ ማስገባት ነበረብኝ?

ሙያተኞች መከራከሪያ አላቸው?ይህን ያሉት ሙያተኞች ከሆኑ መድረክ ፈጥሮ

መነጋገር ይቻላል:: በዚህ ጉዳይ ተጨባጭ መከራከሪያ ይዞ የሚነግረኝ ካለ የምቀበለው በደስታ ነው:: በጓሮ ከሆነ ግን ጥቅም የለውም:: ስሕተት ከሆነ መተራረም ክፋት የለውም:: ከፊት ለፊታችን ታላላቅ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ይጠብቁናል:: ተቀራርበንና በግልፅ ተነጋግረን የሚጠቅመውን ሐሳብ ይዘን መሔድ ወቅቱ የሚጠይቀውና ተመራጭም ነው::

መከራከሪያ ሐሳቡ ለፍፃሜ የቀረቡትን ናይጀሪያንና ቡርኪና ፋሶ ከአምስት ጨዋታ በላይ ሲያደርጉ የተጠቀሟቸው ተጫዋቾች አሥራ አምስት የህሉን ነው:: ተጫዋች ሲጎዳ የሚቀየሩ እንደተጠበቁ ሆኖ፣ ነገር ግን የተቀሩት አብሮ የመጫወት ተደጋጋሚ ዕድል ባገኙ ቁጥር የበለጠ እየተግባቡ የሚሄዱበት ሁኔታ የበለጠ ጥቅም እንዳለው ነው::

አባባሉ እውነትነት ቢኖረውም፣ ነገር ግን እኛ የቀየርናቸው ልጆች መቀየር ያለባቸውን ነው:: ለምሳሌ ሳላዲንን አልቀየርንም:: አቅም የነበራቸውን ምንያህልና ሌሎችንም ያሳረፍነው ለተወሰኑ ደቂቃዎች ነው:: ከዚህ ውጭ ሙሉ ለሙሉ እንዲቀየሩ የተደረጉ ልጆች በቢጫና ቀይ ካርድ እንዲያርፉ የተደረጉ ናቸው:: ሌሎቹም ቢሆኑ መቀየር ስላለባቸው የተቀየሩ እንጂ የተለየ ፍልስፍና ኖሮኝ አይደለም:: ክፍተቶችን ለመድፈን ታስቦ የሚደረግ አማራጭ ነው:: ተቀይረው የገቡ ተጫዋቾች ውጤታማ ሲሆኑ ማጨብጨብ፣ ካልተሳካላቸው ደግሞ የትችት ስለት መምዘዝ ዕድገት አያመጣም:: ዕድገት የሚመጣው ቀና በሆነ አመለካከት ደካማና ጠንካራ ጎኖችን በስታስቲክስ ተደግፎ ተነጋግሮ ወደ ሚበጀው አቅጣጫ በመሔድ ነው::

አሠልጣኙ ተጫዋቾችን መቀያየር ያበዙት ጫና ስለሚፈሩ ነው የሚሉ አሉ::

በፍፁም ያመንኩበትን ካልሆነ የሰዎችን ጫና ፈርቼ ለሰከንድ አላደርገውም:: ለወደፊቱም ቢሆን የማደርገው አይደለም:: ሲጀምርም ጫና ያደረገብኝ አካል የለም:: ያደረግኩት ማድረግ ስለነበረብኝ ብቻ ነው:: ምክንያቱም ልጆቼን ከመነሻው ጀምሮ እንቅስቅሴያቸውንና ወቅታዊ ብቃታቸውን የማውቀው እኔ ነኝ:: ባየሁትና ይጠቅመኛል ባልኩት መሠረትና ድክመት በተመለከትኩት ቦታ ደግሞ ቀይሬ የማስገባውን ተጫዋች ማንነት መወሰን የእኔ ነው:: አሠራሩም ይኼው ነው::

ቡድኑ በዲሲፕሊን ረገድ እጅግ በጣም ብዙ ጉድለቶች እንደነበሩበት ግልፅ ነበር:: ይቀበሉታል ወይስ….?

ትክክል ነው፣ የዲሲፕሊን ጉዳይ ከፍተኛ ዋጋ ካስከፈሉን ድክመቶቻችን ዋነኛው ነው:: በዚህ ረገድ ብዙ መሥራት አለብን:: በአፍሪካ ዋንጫ የተመለከትነው በአዲስ አበባ ስታዲየም ያዳበርነውን ተሞክሮ ነው:: ስለዚህ ተጫዋቾቻችን ሁሉም የዳኛን

“የምንነታረከው መሠረት በሌለው እግር ኳስ ላይ ነው”አሠልጣኝ ሰውነት ቢሻው

ከ31 ዓመታት በኋላ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በምድብ ማጣሪያው ተሰናብቶ ተመልሷል:: የቡድኑን ውጤት ተከትሎ የተለያዩ አስተያየቶች እየተደመጡ ነው:: በ29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ያደረገውን እንቅስቃሴ መሠረት በማድረግ፣ የአገሪቱ እግር ኳስ የመንግሥትንና የሚመለከታቸውን አካላት ትኩረት ካገኘ ተስፋ እንዳለው ብዙዎች የተስማሙበት ሆኗል:: በሌላ ወገን ደግሞ ከአሠልጣኝ ጋር በተገናኙ ድክመቶች እንጂ ቡድኑ የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግብበት አቅም

እንደነበረውም የሚናገሩ አሉ:: አሠልጣኝ ሰውነት ቢሻውስ ምን ይላሉ? ደረጀ ጠገናው እነዚህንና ሌሎችንም ተያያዥ ነጥቦችን በማንሳት አነጋግሯቸዋል::

Page 47: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 47 | እሑድ |የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-1

ማስታ

ወቂያ

ስፖርት ስፖርትውሳኔ በፀጋ ከመቀበል ይልቅ መክበብና ማመነጫጨቅ ነበር:: ድርጊቱ በአዲስ አበባ ስታዲየም ተቀባይነት ኖሮት ይሆናል:: ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ግን አላስኬደንም:: በአዲስ አበባ ስታዲየም ፍፁም ቅጣት ምት ክልል ተቃራኒ ተጫዋችን አፈር ከድሜ የሚቀላቅል ተከላካይ በተመልካች ጩኸት የዳኛ ቀይና ቢጫ ካርድ ሰለባ ከመሆን ሲያመልጥ የኖረ መጥለፍ ቀርቶ መነካካት በማይቻልበት መድረክ መጋለጡ አይቀርም:: የገጠመን ይኼው ነው:: በዚህ በኩል ዳኞቻችን ሕጉን በመተግበር ተጫዋቾችን መስመር ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል:: የሙያ ግዴታቸውም ነው:: የክለብ አመራሮች፣ አሠልጣኞችና ደጋፊዎች ለሕጉ መተግበር አጋር መሆን ይጠበቅባቸዋል:: ካልሆነ ግን ጉዳቱ ለአገር ነው:: እያንዳንዱ ተጫዋች የዲሲፕሊኑ ሁኔታ መታየት ያለበት በክለቡ ነው:: ሰውነት ጋር ሲመጣ አይደለም:: ምክንያቱም ተጣሞ እንዲያድግ የተደረገ ዛፍ ከጠነከረ በኋላ ለማቃናት እንደማይቻል ሁሉ ወደ ብሔራዊ ቡድን የሚመጡ ተጫዋቾችም በሁሉ ነገር ተስተካክሎ ነው መምጣት ያለባቸው:: ለአፍሪካ ዋንጫ የመጨረሻ ማጣሪያ የተጫወትነው ከሱዳን ብሔራዊ ቡድን ጋር መሆኑ ይታወቃል:: በዚያን ወቅት የቡድኑ ዋና በረኛ ሲሳይ ባንጫ ነበር:: ሲሳይ በሱዳኑ ጨዋታ ቢጫ ካርድ እንዳይመለከት በሚገባ ተነጋግረን ነው ወደ ሜዳ ያገባው:: ሲሳይ ግን የተነጋገርነውን ሁሉ ዘንግቶ የቢጫ ካርድ ሰለባ ሆነ:: እንዲህ ዓይነቱን ነገር የዳኞች ኮሚቴ ለሚመድባቸው ዳኞች የማያዳግም ምክርና ተግሳፅ መስጠት መቻል ይኖርበታል:: ክለቦችና ደጋፊዎች ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ መሥራት አለበት:: ምክንያቱ አሠልጣኝ ሰውነት ሱቅ ሔዶ ያለቀለት ኮትና ሱሪ መግዛት ሲገባው የጎደለ ነገር ይዞ ከሔደ ችግሩ የራሱ ነው:: በአፍሪካ ዋንጫ ከዲሲፕሊን ጋር በተያያዘ የተመለከትናቸው ጥፋቶች የራሳችን ድክመቶች ናቸው:: የብሔራዊ ቡድኑ ተጫዋች ሲመጣ ሁሉን ነገር በልኩ ጨርሶ መምጣት አለበት:: ሰውነት እንዲገራው የሚጠብቅ ካለ ተሳስቷል::

በዚህ ረገድ ዋጋ ከፍለናል ብለን እንቀበል?እጅግ በጣም::ኃላፊነትን ለመሸሽ ሆን ብለው የሚያደርጉ ተጫዋቾች

እንዳሉ ይነገራል?ውሸት ነው:: እኔ እስከማውቀው ድረስ ገብቶ

መጫወት የማይፈልግ የለም:: ድርጊቱ የሚፈጠረው በውስጣቸው ይዘውት የቆየው በእንቅስቃሴ ወቅት

ባልጠበቁት መንገድ ስለሚወጣ ነው:: ይህ ግን እናቴ በእንቁላሉ ጊዜ… እንደሚባለው ቀደም ብሎ እርምት ተደርጎበት ቢሆን ግን አንቸገርም:: የእኛ ተጫዋቾች ከተቀሩት የአፍሪካ አገሮች ተጫዋቾች ጋር ሲነጻጸሩ የልምዱ ጉዳይ እንዳለ ሆኖ እስከ መጨረሻው ደቂቃ ድረስ በዲሲፕሊን ረገድ ከፍተኛ ድክመት ነበረባቸው:: እግር ኳስ በስሜት አይሆንም:: ከአደጋ ቀጣና ኳስ መውጣት ባለበት ሰዓት ኳስ እንዲያወጣ የሚነገረው ተጫዋች የተባለውን የማድረግ ግዴታ አለበት:: ይህንን ማድረግ ካልቻልን ግን ልጆቻችን በፍፁም ከማንም ጋር ቢገናኙ እንደማያንሱ ማረጋገጥ እፈልጋለሁ:: ናይጀሪያዊው ጆብ ኦቢ ሚካኤል ምን ያህልን የበለጠው በቁመት እንጂ ኳስን በተገቢው መንገድ አደራጅቶ ለጓደኛ በማድረሱ አይደለም:: በእርግጥ የአየር ኳስ በጭንቅላት በመግጨት ይበልጠዋል:: ለዚያም መፍትሔ ያልነው ኳስ በመሬት ካልሆነ የሰማይ ኳሱ እንዳንጠቀም ነው፣ ተግብረነዋልም:: አንድ ሳላዲን ብቻውን ባለበት የክንፍ ኳስ ሴንተር እንዲደረጉ አልፈቀድንም:: የጨዋታውን ስታስቲክ ስንመለከት ከሦስት ጨዋታ ለሳላዲን ክሮስ የተደረገው በናይጀሪያው ጨዋታ ላይ አንድ ጊዜ ብቻ ነው::

የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋችንን ተከትሎ የተለያዩ አስተያየቶች እየተደመጡ ነው:: እግር ኳሱ ከመንግሥት ጀምሮ እስከ ክለቦችና ሌሎችም የሚመለከታቸው አካላት መሠረታዊ የሆነው ሥራ መሥራት ከተቻለ የክሕሎት ችግር እንደሌለ ነው::

እግር ኳስ ተጨዋች የለም የሚሉ ካሉ ከተጠያቂነት መሸሽ እንዳይሆን እሰጋለሁ:: ምክንያቱም አሁን በአፍሪካ ዋንጫ ከተመለክተናቸው ተጨዋቾቻችን ለአንድ እግር ኳስ ተጨዋች የሚደረግለት ተደርጎለት ያደገ ካለ መወቀስ እችላለሁ:: እውነቱ ግን ማናቸውም በአጋጣሚ ካልሆነ ደረጃውን በጠበቀ ፕሮጀክት ወይም ተመሳሳይ ነገር እገዛ ተደርጎለት እዚህ ደረጃ የደረሰ የለም:: እነዚህ ልጆች በአጋጣሚ እግር ኳስን እየተጫወቱ አድገው ነው፣ ሁሉ ነገር ተሟልቶላቸው ካደጉ አገሮች ጋር ተገናኝተው የተሻለ መንቀሳቀስ እንደሚችሉ ካሳዩን በአገሪቱ በክለቦችም ይሁን በሌላ አጋጣሚ ነገሮች ተሟልተው ለታዳጊ ተጨዋቾች ትኩረት ቢሰጥ የት መድረስ እንደሚቻል ለመገመት ነቢይ መሆንን አይጠይቅም:: ፕሮጀክት ተነድፎ፣ በዚያ መሠረት ታዳጊ ወጣቶች በዕድሜያቸው ማግኘት የሚገባቸውን ሥልጠና አግኝተው እንዲያድጉ ቢደረግ፣ ክለቦቻችን በእግር ኳስ ከውድድር ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት ዓላማ ካላቸው መሆን ይቻላል:: ስለሆነም አደረጃጀቶቻቸውን ሕዝባዊ መሠረት አሲዘው

ከፕሮጀክት ጀምሮ ‹‹ሲ›› እና ‹‹ቢ›› ቡድኖቻቸው ላይ ጠንክረው ቢሠሩ ዓለምን የሚያስደምሙ አስራ አንድ ምርጦችን ቀርቶ፣ አምስትና ስድስት ምርጥ ብሔራዊ ቡድኖች ማፍራት ይቻላል፣ በቂ ክሕሎት አለ:: መንግሥት በአሁኑ ወቅት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ እየተንቀሳቀሰ ነው:: በገርጂ አካባቢ እየተገነባ ያለው የወጣቶች አካዴሚ ሥራ ከጀመረ ችግሩን ሙሉ ለሙሉም ባይሆን ለውጦችን እናያለን የሚል እምነት አለኝ:: የክልል መንግሥታትም ተመሳሳይ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ መንግሥት የበኩሉን ድርሻ መወጣት ይኖርበታል:: ክለቦቻችን በተመሳሳይ ራሳቸውን መፈተሽና ወደ ትክክለኛው መስመር እንዲገቡ መደረግ አለበት:: ምክንያቱም በአገሪቱ ከጥቂት ክለቦች በስተቀር አብዛኞቹ በመንግሥት በጀት የሚንቀሳቀሱ ናቸው:: እያንዳንዳቸው በዓመት አኃዙን በትክክል መግለጽ ባልችልም፣ የዓመት በጀታቸው ከ10 ሚሊዮን ብር እንደማያንስ ነው:: በፕሪሚየር ሊጉ ብቻ የሚወዳደሩ 14 ክለቦች አሉ:: የሁሉም ሲደመር 140 ሚሊዮን ብር ማለት ነው:: እውን እግር ኳሱ ከውድድር ባለፈ ለሚወጣበት ገንዘብና ሕዝቡ የሚፈለገውን ለውጥ አምጥቷል?፣ እውነቱን እንነጋገር ከተባለ ለውጥ ማምጣት ቀርቶ አቅጣጫውን ያገኘ አይመስልም:: ከዚህ ውስጥ የተወሰነውን ቀንሶ ለታዳጊ ወጣት ፕሮጀክቶች ቢውል በግሌ እመርጣለሁ:: ምክንያቱም መሠረት በሌለው ነገር የትም ልንደርስ አንችልም::

እግር ኳሱን ወደ ገንዘብ ከመለወጥ አንጻርስ?ቀደም ሲል ለመግለጽ እንደሞከርኩት እግር

ኳሱን ለመለወጥ አደረጃጀቶች ሲለወጡ እግር ኳሱም የግድ የፋይናንስ አማራጭ መሆኑ የማይቀር ነው:: ምክንያቱም በአሁኑ ወቅት በዓለም ላይ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ከተመለከትን በቂ ነው:: ከዚያ በፊት ግን መሠረቱ ላይ የግድ መሥራት ይጠይቃል:: እየተንገታገትን ያለው በሌላና መሠረት በሌለው ነገር ነው:: ክለቦቻችን የታዳጊ ወጣት ፕሮጀክቶች ቀርቶ ‹‹ሲ›› እና ‹‹ቢ›› ያላቸው ስንቶቹ ናቸው? የራሳቸው ሜዳስ ያላቸው ብለን ስናነሳ መሬት ላይ የምናገኘው ስሌት ዜሮ ነው:: እሩቅ ሳንሔድ የሱዳን ክለቦች ሜሪክና አልሂላል የራሳቸው ሜዳ አላቸው:: በዚያ ላይ ታዳጊዎቻቸውን የሚያሳድጉበት የሥልጠና ተቋም አላቸው:: ለምን እኛስ? ትላልቅ ገቢ ያላቸው ኩባንያዎችና ድርጅቶች አሉን:: በአገሪቱ የሥርዓትና የዕቅድ ችግር እንጂ የገንዘብ ችግር እንደሌለባት፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለአፍሪካ ዋንጫ ዝግጅት ወቅት የተገኘውን ገንዘብ መመልከቱ በቂ ነው:: ወጣቶች ላይ ኢንቨስት የማድረጉ ጉዳይ እንደተጠበቀ

ሆኖ ማለት ነው::

በተጨዋቾቻችን የዕድሜ ችግር ተጨማሪ ችግር ተደርጎ እየተነገረ ነው፤

ምንም ዓይነት ሥርዓት በሌለበት፣ ታዳጊዎች በዕድሜያቸው የሚሠሩበት ተቋም በሌለበት የዕድሜ ችግር ባይኖር ነው የሚገርመኝ::

የአፍሪካ ዋንጫን ተከትሎ ገንዘብ ተገኝቷል:: ይህ ለፌዴሬሽኑም ሆነ ለክለቦች ምን ትርጉም አለው?

ፌዴሬሽኑ እስከዛሬ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ገንዘብ ማግኘት የቻለው የብሔራዊ ቡድኑን ውጤት ተከትሎ ነው:: ስለዚህ ፌዴሬሽኑም ሆነ ክለቦች ከዚህ የተሻለ ቢሠሩ አሁን ከተገኘው በበለጠ ተጠቃሚ የሚሆኑበት አጋጣሚ እንደሚኖር ነው:: ለዚህ ነው የታየውን የእግር ኳስ ጭላንጭል ለማስቀጠል ከመሠረቱ መሥራት ይኖርብናል የምለው::

ለ2014 የዓለም ዋንጫ ኢትዮጵያ ምድቧን እየመራች ነው:: ምን እንጠብቅ?

ተጨዋቾቻችን ከአፍሪካ ዋንጫ ብዙ ተምረዋል:: ከእንግዲህ ማንንም የሚፈሩበት ወቅት አብቅቷል:: በሚገባ ማጣሪያውን አልፈን ወደ ብራዚል እናመራለን::

ዝግጅት የሚጀመረው መቼ ነው?

ከሚቀጥሉት ሁለት ሳምንት በኋላ ተጨዋቾቹ ይሰባሰባሉ:: ምክንያቱም በአፍሪካ ዋንጫ የተመለከትናቸውን ድክመቶቻችንን ማረም የምንችለው በሚኖረን የዝግጅት ጊዜ ነው:: የተሻለ ቡድን ለመሥራት የተሻለ የዝግጅት ጊዜ የግድ ነው::

በአፍሪካ ዋንጫ ስኬትዎ ፌዴሬሽኑና መንግሥት የተለያዩ ማበረታቻዎችን አበርክቶልዎታል?

ከማስበው በላይ ነው፣ ቃላት ያጥረኛል::

ከዚህ በፊት እንደተነገረው፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያበረከተልዎት ሽልማት ሊፋን የቤት መኪና መሆኑን ነው:: በሌላ በኩል ግን የፌዴሬሽኑ ሽልማት መኪና ሳይሆን፣ ለመኪና መግዢያ የሚውል የገንዘብ ሽልማት እንደሆነ ነው::

ገንዘቡ መኪናዋን መግዛት ከቻለ ምን ችግር አለው? የሆነ ሆኖ ግን ፌዴሬሽኑ የሰጠኝ ገንዘብ 520 ሊፋን የቤት መኪና መግዣ የሚሆን 288.000 ብር ነው:: መኪናዋ ትንሽ ስለሆነች ከእሷ የተሻለ ሞዴል ለመግዛት ከሊፋን ጋር ተነጋግሬ ጨርሻለሁ::

Page 48: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 48 | እሑድ የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-1

ዲዛይንና ዝግጅት በሚዲያ ኮምዩኒኬሽን ሴንተር አሳታሚ የሚዲያና ኮምዩኒኬሽን ሴንተር አታሚ፡ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ክ/ከተማ፡ አራዳ ቀበሌ፡ 17 የቤት ቁጥር፡ 984

+32+64 (144)

Page 49: Reporter Issue 1334

ገጽ 1 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2

ደላላው

ክፍል 2 ገጽ 2

ማህበራዊ

ክፍል 2 ገጽ 21

አስተያየት

ክፍል 2 ገጽ 6

ዳያስፖራ

ክፍል 2 ገጽ 20

ሰላም! ሰላም! እስኪ ደግሞ እንደተለመደው የሆድ የሆዳችንን እንጫወት። ሲሉ ብሰማ ነው እንጂ የዘንድሮ ሆድ እንኳን ተርፎት የሚያወራው የሚፈጨው ምን አለው? ለዚህም መሰለኝ ብዙዎቹ ወገኖቼ ነገር ሲገባቸው ‹‹ሆድ ይፍጀው›› እያሉ የሚያልፉት።

የዛሬ 31 ዓመት «ላይፍ መጋዚን» በተባለ መጽሔት በዚህ ርእስ አንድ ጽሑፍ ወጥቶ የአንባቢያንን ስሜት ስቦ እንደነበረና ብዙ አስተያየቶች ቀርበውበት እንደነበር የዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ ያስታውሳል:: መልዕክቱ ለአገራችን ወጣትም አስፈላጊ ቢሆንም የዛሬ 31 ዓመት ለማቅረብ ሲሞከር «የትኛው አርበኛ?» የሚል ጥያቄ ማስነሳቱ ስለማይቀር መተው ያለጥርጥር አማራጭ አልነበረውም::

ታዲያስ መጽሔት እንደዘገበው፣ ዲዛይነር ሔኖክ የ‹‹አራዳ ፋሽን›› ሥራውን የጀመረው በ2001 ሲሆን ዓላማውም በአሜሪካ በሚገኙ ኢትዮጵያውያንና በሌሎች ዜጎች ዘንድ ፍላጎቱ እየጨመረ የመጣውን የኢትዮጵያን ባህላዊ ልብስ ፍላጎት መድረስ ነው:: ዲዛይኑን ከምዕራባውያኑ ዲዛይን ጋር በማጣመር የገበያውን ፍላጎት መሙላትና የአገሩን ባህል ማስተዋወቅም እንዲሁ::

የወንዙ ውኃ የተፈጥሮ ቀለሙን ቀይሮ የቀለጠ ሬንጅ ወይም የተቃጠለ የሞተር ዘይት ይመስላል:: አለፍ አለፍ ብሎም የወየበ አረፋ ደፍቆ ይታያል:: ከስፍራው የሚፈሰው መጥፎ ጠረን አፍንጫን ይሰነፍጣል:: የቤት ጥራጊ፣ የተለያዩ ደረቅ ቆሻሻዎች፤ ፌስታሎችና የፕላስቲክ ጠርሙሶች፣ የሞተ ዶሮና ድመት የጨርቅና የወረቀት ቅዳጆች በወንዙ ላይ ተጥለው ይታያሉ::

በአስፋው ብርሃኑ ልዩ ዘጋቢ ከሐዋሳ

ከአዲስ አበባ 250 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ወደምትገኘው ሻሸመኔ ከተማ ሲደርሱ ቀኙን ትተው ወደ ግራ ሲታጠፉ አንድ አረንጓዲያማ አካባቢ የሚያደርሰውን አስፋልት ያገኛሉ:: ከዚያም 11 ኪ.ሜ እንደተጓዙ በአገራችን የመጀመሪያው በደን የተሸፈነ ስፍራና በአገሪቱ ብቸኛው የደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ይደርሳሉ:: ቀጥሎም በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች መዳረሻ ወደሆነው ዋቢሸበሌ መዝናኛ ሆቴል ከሦስት ኪ.ሜ ጉዞ በኋላ ያገኛሉ:: በአሳብ ይዤአችሁ የምወስዳችሁ ሥፍራ ወንዶ ገነት ይባላል:: እነዚህን ከላይ የዘረዘርኳቸው ስፍራዎች ከ30 ዓመታት በፊት በነበሩበት ማራኪ የተፈጥሮ ውበታቸው ጋር ማየት በእርግጥ የማይቻል በመሆኑ የሰነድና የስው አስረጅ ካላገኙ የቀድሞውን ታሪክ ማወቅ አስቸጋሪ ይሆንቦታል:: በአገሪቱ በደን ሽፋንና በተፈጥሮ መስህብ የማንንም ቀልብ የመግዛት አቅም የነበረው ስፍራ ዛሬ ትዝታ የመሆኑ ምስጢርና ተያያዥ የሥነ ምህዳር ችግሮች ሰለባ ሆኗል::

ወንዶገነትና የአረንጓዴው ዘመቻ በ1970ዎቹ መጀመሪያ በደርግ የሥልጣን ዘመን

የአረንጓዴው ዘመቻ ደን ሠርቶ ማሳያ ማዕከል የነበረው ወንዶገነት ከተፈጥሮ ጫካ በተጨማሪ የባሕር ዛፍና ጥድ እንዲሁም ሌሎች ዛፎች የተሸፈነ እጅግ ማራኪ ስፍራ ነበረ:: በወቅቱ በስዊድናውያን ዕርዳታ የተቋቋመው የደን ኮሌጅ ዓላማም ከአካባቢው ባለፈ በአገሪቱ የደን ሀብትን ማስፋፋት ስለነበረ የወረዳው ዙርያ በዛፎች እንዲሸፈን ተደርጓል:: ከነዚህም አካባቢዎች ዛሬ የጫት ማሳ ሆነው የቀሩትንና የቀድሞውን መላጌ ወንዶ ሥጋ ፋብሪካ (አሁኑ ኤልፎራ) የሚገኝባቸው ቀበሌዎችን ያካትታል:: የደን ኮሌጅ ከሚገኝበት ሆሻ ከተማ ዙሪያውን ስድስት ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘውን ሌላ ትንሽ ከተማ ኬላና በለጬ አካባቢዎች እንዲሁም የወረዳው ዋና ከተማ ጩኮ (በቀድሞ ስሙ ባሻ) የላይኛው መረቦና ባጃ አካባቢዎች ታይቶ የማይጠገብ ደንና በአስገራሚ የዱር እንስሳት የተሞሉ ስፍራዎች ነበሩ:: በአረንጓዴው ዘመቻ አረንጓዴ ሆነው የቆዩት ዛሬ በትዝታ የሚነሱ አካባቢዎች ሆነዋል::

የወንዶገነት የቀድሞ ደን ፀጋዎች ሲታወሱ ወንዶገነት ከሃያ አመታት በፊት በሰው ሠራሽ ደንና

የተፈጥሮ ጫካዎች የተሸፈነ አካባቢ ስለነበረ ዱኩላ፣ ሚዳቆ፣ ቀበሮ፣ ከርከሮ፣ የጦጣና ዝንጅሮ መንጋዎች፣ እጅግ አስገራሚ ተፈጥሮ ያላቸው አዕዋፋት፣ ጅብና የነብር ዝሪያዎች ጥሪኝና ሌሎች የዱር እንስሳት በስፋት ይገኙበት ነበር:: በተለይ በወረዳው ዋና ከተማ በባሻ አካባቢ የቀድሞው ሥጋ ፋብሪካ የእንስሳት እርድ ያደርግ በነበረ ጊዜ ተረፈ ምርት ለጅብ ይጣል ስለነበረ የቤት እንሳስትና ሰውን ያን ያህል አይተናኮልም:: ዛሬ የጅብ መንጋ ጨለማን ትቶ በቀን እየወጣ ሰውን መተንኮስ ከጀመረ ዓመታት ተቆጥረዋል:: ከወንዶገነት ጥቅጥቅ ደን ጋር

የወንዶገነት ደንና አሳሳቢ የሥነ ምህዳር ቀውሶችበሚሰብ ድምፅ የሚፈሱት የኪላ፣ ጩኮ፣ ቡሳ (ወዲሳ) አቦሳ ወንዞች የሚነሱባቸው ተራራማ አካባቢዎች በደን ፈንታ በጫት ተክል በመሸፈናቸው መጠናቸው በክረምት እንኳን ዝቅተኛ ነው:: ላይኛው መርቦ ለኤልፎራ እርሻ የመስኖ አገልግሎት የሚሰጥ ከበጃ ቀበሌ የሚነሳው ወዴሳ ወንዝ መጋቢ የቁላባ ወንዝ ነው:: አካባቢዎቹ በጫት ምርት ገቢ የሚተዳደሩ በመሆናቸው በበጋ ከሌላ አዝመራ ይልቅ ለጫት መስኖ ይጠቀማሉ:: የፈረቃ አጠቃቀም እምብዛም ባለመለመዱ አንዳንድ ጊዜ የፍጥጫ ምክንያት ይሆናል::

የወንዶገነት የደን ልብሷ የት ገባ? የወረዳው ሕዝብ ቁጥር ዕድገትን ተከትሎ የመሬት

እጥረት ቀዳሚው ለደን ጥፋት መንስኤ መሆኑን የወረዳው የልማት ሠራተኛ አቶ ሽንኮሩ ተሰማ ይናገራሉ:: ‹‹የተላጨ ፀጉር እንኳን ይበቅላል፣ የወንዶገነት ደን ግን እንዳያቆጠቁጥ ሆኖ ነው የጠፋው፤ ሁለተኛው መንስኤ የጫት ዋጋ በየጊዜው እየናረ መሄድ የደን መሬቱ በጫት ማሳ መተካቱ ነው፤ ሌላው ይቅርና ለአካባቢው የምግብ ዋስትና ትልቅ ፋይዳ ያለውን የእንሰት እርሻ ጫት እየያዘው ነው::›› በአንድ ወቅት የተከሰተው ሰደድ እሳት በተለይ ለዋናው ደን መራቆት አስተዋዕፆ እንዳለውም ባለሙያው ይጠቅሳሉ:: የእርሻ መስፋፋትና የቤት መሥሪያ እንጨት ፍላጎት መጨመር ለወንዶገነት ደን መሳሳት ምክንያት ነው:: ያለምትክ መቆረጡ አሉታዊ ሚና እንዳለው የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ::

የደኑ መመናመን ያስተከተለው የሥነ ምህዳር ተፅዕኖየሰው ልጆች መጠለያ ቤት እንደመሆኑ የዱር

አራዊት ቤታቸው ደን መሆኑ አሌ አይባልም:: እናም መኖሪያቸውን ያጡ ብርቅዬ እንስሳት ከመጥፋት ሌላ አማራጭ አይኖራቸውም:: በእርግጥ ደኑ መኖሪያቸው ብቻም ሳይሆን የመኖ ምንጫቸውም ስለሆነ እነዚያ የሚማርክ ተፈጥሮ ያላቸው እንስሳት ታሪክ ሆነው እየቀሩ ነው:: ወንዶገነት በደንና የተፈጥሮ ጫካ ተሸፍና በነበረች ጊዜ እንደዛሬው የውሃ እጥረት አልነበረባትም:: ምክንያቱም ክረምቱ ወቅቱን ጠብቆ ይከሰታል፣ በበጋም እርጥበትና የወንዞች መጠን ከክረምቱ ብዙም አያንስም:: መሰል ሁኔታ አካባቢው አረንጓዴና ለምለም ሆኖ እንዲቀጠል አድርገውት ነበር:: በዛሬዋ ወንዶገነት በጋና ክረምት ተዘበራርቀዋል:: ሚያዝያና ግንቦት ሐሩር ጥቅምትና ኅዳር ደግሞ የሐምሌና ነሐሴ ዝናብ ይከሰትበታል:: ይህም የሥነ ምዳህር እና የአየር ንብረት ለውጥ መከሰቱን አመላካች ነው::

ወንዶገነት ዋቢሸበሌ መዝናኛ ሆቴል አካባቢ /ወሻ ከተማ/ ነዋሪ የሆኑ አቶ መተኪያ ሰይፉ ከአስርና አስራ አምስት ዓመት በፊት ይመጡ የነበሩት የውጭና የአገር ውስጥ ጎቢኚዎች ቁጥርን ከዛሬው ጋር ማወዳደር አይቻልም ይላሉ:: ‹‹በሳምንቱ የዕረፍት ቀናት እንኳን በጣት የሚቀጠሩ ቱሪስቶችን ማየት ዘበት ነው፤›› በማለት የሚገልጹት አቶ መተኪያ ‹‹አይፈረድባቸውም ዛሬ ምን ሊያዩ ይመጣሉ? ወንዶገነት ታሪካዊ የውበቷ መገለጫ

የነበረው አረንጓዴ ሽፋን ላይበቅል ተላጭቷልና›› ሲሉ በቁጭት ይናገራሉ::

የቀድሞዋን ወንዶገነት ማየት ይቻል ይሆን?በእርግጥ የወንዶ ገነት ደንና የተፈጥሮ ጫካ

ከመጥፋት ጋር አብረው ታሪክ የሆኑ በርካታ የዛፍ ዓይነቶች ነበሩ:: እነሱን መተካት ምናልባት ለኮሌጁም የቀለለ አይመስልም:: በርካታ የዱር እንስሳትና አዕዋፋት ዛሬ የሉም:: በጣም የሚገርመው ለወንዶገነት መታወቂያ በመሆኑ እስከ ዛሬ ድረስ ለመዲናችን አዲስ አበባ ነዋሪዎች የሚቀርበው የአቮካዶ ዛፎች እንኳን ተገንድሰው አልቀዋል:: በተለይ በኤልፎራ እርሻ ልማት ዙሪያ ያሉት የላኛው መርቦ ነዋሪዎች በጥፍጥና የሚታወቀው ምርት የአቮካዶ ዛፎችን ለማገዶ ሸጠው ጨርሰዋል:: መሸጣቸው አልከፋም ደግመው አለመትከላቸው እንጅ:: እና ይህ ዛፍ በብዛት የሚገኘው በኤልፎራ እርሻ ውስጥ ብቻ ነው::

ኩባንያው ከአቮካዶ በተጨማሪ በርካታ የዛፍ ዓይነቶችን በመትከል የሥነ ምህዳር ሚዛን ለመጠበቅ ጥረት እያደረገ ይገኛል:: በእርግጥ በኮሌጅ አካባቢ የባሕር ዛፍ ደን ቢወገድም ሌሎች ዛፎች በስሱ አሉ:: ጥቅጥቅ ደን የሚባል አይደለም:: በመሠረቱ በረሃን እንኳን አረንጓዴና ለምለም ለሰውና ለአራዊት ምቹ ማድረግ እየተቻለ ነው:: የቀድሞው ወንዶ ገነት ሙሉ በሙሉ ማምጣት ባይቻልም የሥነ ምህዳር ቀውሶች እንዳይበረክቱ የዛፍ ተከላ ፕሮጀክቶችን በማስፋፋት ችግሩን መቅረፍ ይቻላል:: ለዚህ ደግሞ ትልቁ ኃላፊነት ያለው የወንዶገነት ደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅና ማኅበረሰብ ላይ ነው::

ወንዶገነት ዛሬ እንደቀድሞዋ አይደለችም:: የውበቷ አካል የሆኑ በርካታ የተፈጥሮ ፀጋዎቿ የሉምና:: ምናልባትም ከሃያ ዓመት በፊት የነበረችው ወንዶገነት መልሶ ለማየት ሌላ የአረንጓዴ ዘመቻ ወይም የዛፍ ተከላ ፕሮጀክት ያስፈልግ ይሆናል:: ምንጮችና ወንዞች እንዲሁም የደን ሥፍራዎች በቀድሞ ይዞታቸው ማየት ከባድ ነው:: የዱር እንስሳት ተሰድደዋል፤ ዕፀዋት ከጫካ ጠፍተዋል:: ይልቅ ኑሮው በጉድጓድ ውስጥ የተመሰረተው ጅብ ብቻ ነው ማታ ማታ ወደ ባሻ ከተማ ቄራ አካባቢ እየተሯሯጠ ሕይወቱን ያስቀጠለው:: ወንዶገነት የደን ልብሷ ዛፎች መሆናቸው ቀርቶ በጫት እየተሸፈነ ይገኛል:: ጫት ለአካባቢው ማኅበረሰብ ዓይነተኛ የገቢ ምንጭ ነውና::

ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ለመጀመሪያ ጊዜ ወንዶ ገነትን ሲጎበኟት ‹‹ወንዶ›› ትባል እንደነበረና ለምለምነቷን አይተው ‹‹ምን ወንዶ ብቻ ገነትም ነው እንጅ›› ማለታቸውን ተከትሎ ወንዶ ገነት መጠሪያዋ መሆኑ ይነገራል:: ዛሬ ያንን ስሟን ከነውበቷ ማየት ከባድ ነው::

ኢትዮጵያ ከካርቦን ልቀት ነፃ የሆነ ኢኮኖሚ ለመገንባት ማቀዷ ምናልባት ለወንዶ ገነት ዳግም ትንሣኤ ሊያመጣ የሚችልበት አጋጣሚ ስለሚኖር ለደን ኮሌጁና ለአካባቢው ማኅበረሰብ መልካም ዜና ነው ማለት ይቻላል::

ከሚነሱ ፀጋዎች ከያቅጣጫው የሚፈሱ ምንጮችና ወንዞች ተጠቃሾች ነበሩ:: ይሁንና ደኑ ሲመናመን የምንጮቹ ቁጥር መቀነስ፣ ወንዞቹ መጠን በእጅጉ ወርዶ በትዝታ ቀርተዋል:: ይህን እውነታ ወንዶገነት ዋቢ ሸበሌ መዝናኛ ሆቴል በተለያዩ ጊዜያት የመጎበኘት ዕድል የነበረው ሰው ማስታወስ ይቻለዋል:: ከወንዶገነት ደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ተንስተው ወደ ወረዳው ድንበር እስከሚደርሱ ለጆሮ

Page 50: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 2 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

ማስታ

ወቂያ

የጨረታ ማስታወቂያዘመን ባንክ አ.ማ. ከዚህ በታች የተመለከቱትን ቋሚ እና ተንቀሳቃሽ ንብረቶች በዝግ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡

ተቁ የንብረቱ አይነት ብዛት ንብረቱ የሚገኝበት ቦታ የአንዱ ንብረት የጨረታ መነሻ ዋጋ

ጨረታው የሚከፈትበት ቀን እና ሰዓትቀን ሰዓት

1. አዳዲስ አውቶሞቢል (Brand New Faw Automobile zero mileage) እ.ኤ.አ. 2008 የተመረቱ 25

ኮሜርስ ፊትለፊት በሚገኘው ባንኩ ለግንባታ የተረከበው ግቢ ውስጥ

301,665.00 የካቲት 9 ቀን 2005 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት

2 ቶዮታ ሚኒባስ (Toyota Minibus)እ.ኤ.አ. 1999 የተመረተ 1 ኮሜርስ ፊትለፊት በሚገኘው ባንኩ

ለግንባታ የተረከበው ግቢ ውስጥ244,800.00 የካቲት 9 ቀን

2005 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት

3 ሚትሱቡሺ ፓጃሮ (Mitsubishi Pajaro) እ.ኤ.አ. 1997 የተመረተ 1 ኮሜርስ ፊትለፊት በሚገኘው ባንኩ

ለግንባታ የተረከበው ግቢ ውስጥ339,264.00 የካቲት 9 ቀን

2005 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት

4 የመኖሪያ ቤት (315 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ) 1 በኦሮሚያ ክልል ፊንፊኔ ዙሪያ የቡራዩ ልዩ ዞን ልዩ ስሙ ሳንሱሲ ቀበሌ ለኩ 01

403,500.00 የካቲት 9 ቀን 2005 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት

ማሳሰቢያ፡-

1. ተጫራቾች የመነሻ ዋጋውን 1/10ኛ (አንድ አስረኛ) የጨረ¬ ማስከበሪያ በባንክ በተመሰከረለት የክፍያ ማዘዣ (ሲፒኦ) በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፡:2. አሸናፊ የሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በ30 (በሰላሳ) ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ካልከፈለ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታው ይሰረዛል፡፡ ላላሸነፉት

ተጫራቾች ያስያዙት ገንዘብ ወይም ሲፒኦ ይመለስላቸዋል፡:3. አሸናፊው በተራ ቁጥር 1 ለተጠቀሱት ንብረቶች የ15% ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ይከፍላል፡፡4. ተጫራቾች ለአንድ ተሽከርካሪ/ንብረት ወይንም ለተወሰኑ ተሽከርካሪዎቸ/ንብረቶች ወይንም ለሁሉም ተሽከርካሪዎች/ንብረቶች መጫረት ይችላሉ፡፡ በተጨማሪም ባንኩ

በተራ ቁጥር 1 ላይ ለተጠቀሱት ተሽከካሪዎች በብዛት ለሚገዙ ቅድሚያ ይሰጣል፡፡5. ባንኩ ንብረቱ በገዢው ስም እንዲዞር ለሚመለከተው መንግስታዊ አካM ደብዳቤ ይፅፋል፡፡6. የባንኩ የብድር ፖሊሲን ለሚያሟሉ የጨረታ አሸናፊዎች ከ50% እስከ 70% /ከሃምሳ እስከ ሰባ በመቶ/ ብድር ሊያመቻች ይችላል፡፡ ሆኖም ይህ ከላይ በቁጥር 2

የተጠቀሰውን ግዴታ አያስቀረውም፡፡7. ተጫራቾች ንብረቶቹን የሚገዙበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ በባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት 6ኛ ፎቅ የሠው ኃይል እና ጠቅላላ አገልግሎት መምሪያ እስከ

የካቲት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በሥራ ሰዓት ማቅረብ ይችላሉ፡፡8. የጨረታው ሳጥን ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪላቸው በተገኙበት በሰንጠረዡ ላይ በተገለፀው ቀን እና ሰዓት በባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት 6ኛ ፎቅ ይከፈታል፡፡9. ተጫራቾች ከጨረታው ቀን በፊት ንብረቶቹን በሚገኙበት ቦታ በሥራ ሰዓት መጐብኘት ይችላሉ፡፡10. ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይንም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡11. ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0115540043/49 የውስጥ መስመር 200 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

ዘመን ባንክ አ.ማ.

ደ ላ ላ ው

ወደ ክፍል 2 ገጽ 3 ዞሯል

ሰላም! ሰላም! እስኪ ደግሞ እንደተለመደው የሆድ የሆዳችንን እንጫወት። ሲሉ ብሰማ ነው እንጂ የዘንድሮ ሆድ እንኳን ተርፎት የሚያወራው የሚፈጨው ምን አለው? ለዚህም መሰለኝ ብዙዎቹ ወገኖቼ ነገር ሲገባቸው ‹‹ሆድ ይፍጀው›› እያሉ የሚያልፉት። ‹‹ማርክስና ኤንግልስ ልዩ ምልክታቸውን ‘እጅ’ አድርገው ለወዝአደሩ መበልፀግ ሲጮኹ የነበረው . . . ›› እያለ የባሻዬ ልጅ ይህንኑ ሲደጋግምብኝ ሰነበተ። እኔ ደግሞ፣ ‹በዚህ ዘመን የተቀላቀለ ርዕዮተ ዓለም የሚያራምዱ ስለበዙ አርፈህ ተቀመጥ፤›› አልኩት:: ኑሮ ጫናውን የሚደጋገምብን ብሶ ነገርና ዓረፍተ ነገር ሲደጋገምባችሁ እስኪ አስቡት። ‹‹ምንድነው የምትለኝ? እስኪ ግልጽ አድርገው?›› ስለው፣ ‹‹ሁሉም ዜጋ በተቀራራቢ የሀብት ልዩነት ማደግ ስለሚችልበት ሥርዓት ነው የማወራህ፤›› እያለ ስለ‘ሶሻሊዝም’ እና ‘ኮሙዩኒዝም’ ይነዘንዘኝ ጀመረ። ‹‹ደሃው ጀርባው መጉበጡ ሀብታሙም እያደር ወደ ላይ መተኮሱ የነፃ ገበያ ሥርዓት መገለጫ ከሆነ በአፍንጫችን ይውጣ፤›› እያለ ክፉኛ ሲብሰለሰል ከረመ። ታዲያ አንዳንድ በአብዮቱ ዘመን እላይ ታች ሲሉ ያልተሳካላቸው ሰዎች ሲሰሙት፣ ‹‹ይህቺ ጠጋ ጠጋ ዕቃ ለማንሳት ነው። ለእኛም አልተሳካ!›› ሲሉት፣ እንደኔ ምኑንም የማያውቅ አልፎ ሂያጅ ደግሞ፣ ‹‹ወንድሜ ምናለበት አርፈህ ብትቀመጥ? እኛም አርፈን መበዝበዛችንን ብናጣጥም?›› ሲለው ሰነበተ። እንግዲህ ልባም ከሆናችሁ እዚህች ምስኪን አገር ስለተመቻቸውና ያልተመቻቸው ሰዎች ልዩነት በደንብ የሚታያችሁ አሁን ነው። የደከመውና የታከተው ‘አይቶ እንዳላየ’ የሚባል ጥበብ ከእንጀራ ይልቅ ዕድሜ ሲያረዝምለት፣ ትኩሱን ወጣት ብስጭትና ተስፋ መቁረጥ ዕድሜውን ወደሚያሳጥርበት የሱስ ዋሻ ሲመራው ማስተዋል ግድ ይላችኋል። ድሮስ ከዚህ ውጪ መሰንበት ምን ፈየደልን አትሉም? ወይም ‹‹የባሰ አለና አገርህን አትልቀቅ›› የማለት ምርጫው የእናንተ

ነው!

ሸሽቶ ላይሸሽ ርቆ ላይርቅ የመኖርን እንቆቅልሽ ስንገፋ እንከርማለን። አቤት! ምን የማንገፋው የተራራ ዓይነት አለ? የሕይወት ግዴታ ነውና ግድ ይለናል:: እኔም ቁጭ ብዬ ‹‹እህህ›› ከማለት እያልኩ ስኳትን አይደክመኝም። በሳምንቱ መጀመርያ አንድ ገና አዲስ የገባ ያለጠፈ ‘ላንድ ክሩዘር’ አየር ባየር ልሸጥ እንዴት ስቃዬን እንዳየሁ አይነገርም። መጀመርያ ‘ለመሆኑ ይኼን ውኃ የመሰለ ‘ላንድ ክሩዘር’ ማን ሊገዛ ይችላል?’ ብዬ ስጠይቅ ፈጥነው የታሰቡኝ በሥልጣናቸው አማካይነት የሚበለፅጉ አንዳንድ ሹማምንት ናቸው። እንጀራ ነውና ልቤ ጮቤ እየረገጠ አቅራቢያዬ ወዳለ አንድ ተቋም መጓዝ ጀመርኩ። ይኼኔ አንድ ደላላ ወዳጄ መንገድ ላይ አግኝቶኝ፣ ‹‹ተሸጠ እንዴ?›› ብሎ ስለመኪናው ሲጠይቀኝ እንዳልተሸጠ ነግሬው ወዴት እየሄድኩ እንደሆነ አስረዳሁት። ‹‹አይ አንበርብር ሞኙ። እንዴ በፊት ለፊት በር ገብተህ ልታሻሽጥ ታስባለህ? ያውም የንብረት ምዝገባና ቁጥጥር በዓይነ ቁራኛ በሚያስተያይበት ዘመን?›› ሲለኝ ምን ነክቶኝ ነው ብዬ መለስ አልኩ። የባለሥልጣኖቻችን የሀብትና ንብረት ምዝገባ ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍልን፣ ተጠያቂነትንና ግልጽነትን ያሰፍናል የሚል አንድምታ እንደነበረው የባሻዬ ልጅ ያጫወተኝ ትዝ አለኝ። እኔም ይኼንን ለዚሁ ወዳጄ ባነሳለት፣ ‹‹ከቴም ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል? ኧረ ተወኝ አንተ ሰውዬ! ምናለ ተፈጥሮ የቸረችንን አየር መጀመርያ እኩል መከፋፈል ብንችል?›› ብሎ ወደሚቸኩልበት ጉዳዩ ጥሎኝ ፈረጠጠ። ያው እንደምታውቁት ውስጣችን ምን ቢቋጥር አርፎ ለመቀመጥ ሕይወታችን አትፈቅድልንምና ስንሮጥ እንውላለን። ‘የሚሮጡት ብዙዎች የሚሸለሙት ጥቂቶች’ ሲባል ወይ ሲሆን ያልሰማ አለ? አንዳንዶች በአርባ ቀን ዕድል እያማረሩ ሲቆዝሙ፣

ዕድል መኖሩን የማያውቁት ደግሞ ላባቸውን ጠብ አድርገው ጣዕረ ሞት ከሚመስለው ኑሮ ጋር ይተናነቃሉ:: የደላቸው ደግሞ የተኙበትና ጎዝጉዘው የተቀመጡበት ሥፍራ ድረስ በረከቱ ይፈስላቸዋል:: ‹‹የገንዘብ ማተሚያ ማሽን መኝታ ቤታቸው ወስጥ የተከሉ አሉ እንዴ የሚያሰኝ ጊዜ ላይ ነው ያለነው፤›› ያለኝ የባሻዬ ልጅ ነው::

አስቤ አስቤ እኔ ቆቁ አንበርብር ምንተስኖት ማን ዘንድ የሄድኩ ይመስላችኋል? ለነገሩ አገሩ በሙላ በቻይና ተወርሮ ከእነርሱ ውጭ ማን ዘንድ እሄዳለሁ? ከቀናት በፊት አንድ ቻይናዊ መኪና ሲያፈላልግ ተገናኝተን ስለነበር የሚሠራበት ‘ሳይት’ ቀጥ ብዬ ሄድኩ። በሥራ ተጠምዶ ወዲያ ወዲህ ሲል አላናግረኝ ማለቱን ያየ አንድ ሐበሻ የቀን ሠራተኛ ወደኔ ተጠጋና ቆመ። የእኛ ነገር በአገራችንም በሰው አገርም የሚቀናን መቀጠር እንጂ መቅጠር አይደለም። ኧረ ሥራ ተገኝቶ ሠርቶ ማደሩም ወግ ነው። ይኼው የቀን ሠራተኛ ቀስ ብሎ ተጠጋኝና፣ ‹‹አይዞህ ጠጋ ብለህ ጥራና አናግረው። አማርኛ አቀላጥፎ ይናገራል፤›› አለኝ። ማስጠንቀቂያ! ዘንድሮ ሰው መልኩና ፀባዩ ብቻ ሳይሆን ቋንቋውም አልያዝ አልጨበጥ ብሏል። አደራችሁን አይሰማኝም ብላችሁ ፈረንጅ ማማት ይቅርባች እላለሁ እኔ ደላላው አንበርብር ምንተስኖት። ‘የመናገር ነፃነት በተረጋገጠበት ዘመን ሰማኝ አልሰማኝ ምን አስጨነቀኝ?’ የምትሉ ካላችሁ ቻይናውያን የታላቁ የኮሙዩኒስት ፓርቲ ልጆች መሆናቸውን በጊዜ ልብ ብትሉ የሚሻል ይመስለኛል። ገባችሁ? የገባችሁ እባካችሁ ያልገባቸውን አስረዱልኝ? አመሰግናለሁ!

‹‹ለመሆኑ እንዲህ በአጭር ጊዜ ቋንቋችንን ለማጥናት የሚያጣድፋቸው ነገር ምን ይሆን?›› ብዬ ጠየቅኩት። ልጁ የወሬ ሱሱን ለማርካት ሲቁነጠነጥ መቆየቱን ከአነጋገሩ እያስተዋልኩ ተገረምኩ። ‹‹ቀን

ይኼው እንደምታያቸው እነሱም ላባቸውን እየፈሰሱ ሲያሠሩን፣ ሲያስቆፍሩንና ሲያስንዱን ይውላሉ። ሲመሽ እኛ አገር ሥራ አልተለመደም። እንደ ታዳጊ አገር ሳይሆን እንደ አደገ አገር መዘባነን ያስመኘናል። ታዲያ ያኔ ምን ይሥሩ? ቋጣሪ ሆነን ያስመረርናቸውን ‘ቺኮቻችንን’ ለማደን በምሽት ሲወጡ በምን ይግባቡልህ?›› ሲለኝ የወደፊቱ ‹‹ኢትዮ ቻይኒዝ›› ትውልድ ውልብ አለብኝ። ጉድ ነው አትሉም? አቤት ያኔ ተቀላቅሎ የሚበላውና የሚጠጣው ዓይነት ብዛቱ? ያኔ ስምን የሚያወጣው እውነትም ‹‹መላዕክ›› መሆን ይገባዋል።

በዚሁ ስሜት ውስጥ ሳለሁ ራሴን እንዲህ ስል ጠየቅኩት። ‘ቻይና እየሠራችልን ነው እየረዳችን?’ በነገራችን ላይ እንዲህ ያለ መንታ ጥያቄ ሲገጥማችሁ እንደድሮው አንዱን መምረጥ አይሠራም። እንዴት ሆኖ ይሠራል? እስኪ ስታስቡት በዚህች ተለዋዋጭ ዓለም ምን ወጥ ነገር ኖሮ ነው ወጥ መልስ የምንመልሰው? ሳይንስ እንኳ ዓይኑን በጨው አጥቦ ትናንት እውነት ያለውን ዛሬ ሐሰት ብሎ እየሸመጠጠን

ይመቻችሁ!

Page 51: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 3 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2

INVITATION TO BID No. LITB-2013-9105296

For Long-Term Procurement

UNICEF Ethiopia Office wishes to enter into a Long-Term Agreement to procure various types of plastic items (jerry cans 20 and 10 liters capacity, plastic basins, plates, cups, jugs, 30 and 40 liters capacity hand washing containers with fixed metal tap, buckets 10, 15 and 20 liters capacity)Interested and eligible bidders are invited to collect the complete tender document at the address below starting from 07/02/2013. Formal offers return dates are indicated on the bid documents for each of the above listed items.

UNICEF reserves the right to accept or reject any part or the entire bid.

For further information and queries, please contact TegestZeleke

UNICEF ETHIOPIA,Kasanchisnext to Intercontinental Hotel, adjacent to German

House (GTZ)(New building, Supply Section 1st floor, Room No. 108)

P.O.BOX 1169TEL: 011 518 41 61 , 011518 40 00,

e-mail: [email protected] ABABA, Ethiopia

ማስታ

ወቂያ

የሜታ ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አ/ማ የባለ አክሲዮኖች የስብሰባ ጥሪ

የሜታ ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አክሲዮን አ/ማ፣ 10ኛ መደበኛ

ጠቅላላ ጉባዔውን የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ

ሰበታ ከተማ ቀበሌ 02 ከብሔራዊ አልኮል ፋብሪካ አጠገብ በሚገኘው

በአክሲዮን ማህበሩ ሕንፃ አዳራሽ ያካሄዳል፡፡ ባለ አክሲዮኖች በዕለት

እንዲገኙ ቦርድ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

የስብሰባው አጀንዳ፡-1. የዳይሬክተሮች ቦርድ የሥራ ሪፖርት ይቀርባል፣

2. የውጭ ኦዲተር ሪፖርት ይደመጣል፣

3. የ2003 እና የ2004 ዓ/ም የሥራ አፈፃጸም ሪፖርቶች ላይ መወያየት፣

4. የ2005 እና 2006 ዓ/ም የሥራ አፈፃጸም እቅድና ፕሮግራም ላይ

ተወያይቶ ማጽደቅ፣

5. ስለ ትርፍ ድርሻና የአክሲዮን ሽያጭ መወሰን፣

6. አዲስ ቦርድ አባላት መሰየም ክፍያቸውንና አበላቸውን መወሰን፣

7. የዕለቱን ቃለ-ጉባኤ ማጽደቅ፣

8. በጉባዔው ላይ በግንባር መገኘት የማይችሉ ባለአክሲዮኖች በወኪል

አማካኝነት መሳተፍ ይችላሉ፡፡

የሜታ ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አ/ማ የዲሬክተሮች ቦርድ

ለበለጠ መረጃ አድራሻ፡- ሃብተ ጊዮርጊስ ሜታ ቢራ ማከፋፈያና መዝናኛ ክበብ

ስልክ ቁጥር 0911928600

ከክፍል 2 ገጽ 2 የዞረ

አይደል እንዴ? እሱስ አንደኛውን መረጃውን ይዤ ነው ይላል። ሌላ ሌላው ነገር ነው እንጂ። ለምሳሌ ‘ኢትዮጵያ እያደገች ነው ወይስ እያደግኩ ነው እያለች?’ ብትባሉ መልሱ ሁለቱንም ነው። አያድርስና ‘እንዴት?’ ባይ አፋጣጭ ከገጠማችሁ ‘ለአንዳንዶች አድጋለች ለአንዳንዶች አድጌያለሁ ትላቸዋለች’ ብላችሁ መመለስ ግዴታ ሆኗል። ሌላ ምሳሌ፣ ‘አፍሪካ እየሠራች ነው እያወራች?’ ተብላችሁ ብትጠየቁ አሁንም ‘ሁለቱንም!’ ብላችሁ መመለሳችሁን አደራ። መቼም ለዚህ እንዴት? ባይ አስጨናቂ ጠያቂ የሚኖረው አይመስለኝም። ምክንያቱም አኅጉራችን የአኅጉራት ቁጥር ማሟያ እንጂ ሌላ እንዳልሆነች ሁሉም ጠንቅቆ የሚያውቀው ጉዳይ ስለሆነ ነዋ። የአፍሪካ ኅብረት ተጎልቶ ፈረንሳይ በማሊ ምድር ላይ ምን እየሠራች እንደሆነ እናውቃለና:: ‹‹አይ ዘመን! ሁሉም በተናጠል የሚሮጥበት ጊዜ!?›› ይላሉ ባሻዬ እንዲህ ነገርን በነገር እያነሳን ስንጫወት። እናም ቻይና እየሠራችልን ነው እየረዳችን ብዬ ጠይቄ ራሴው ለራሴው ‘ሁለቱንም’ ስል መለስኩኝ። ሁሉንም ነገር ‘እንዲህ ነው! የለም እንዲያ ነው!’ ለማለት እየከበደን ሲመጣ ግርም አይላችሁም? ለነገሩ እውነትና ሐሰቱ፣ ዘይትና ውኃው ተቀላቅሎና ተመሳስሎ እየኖረ ነጥሎ ጠይቆ ነጥሎ መመለስ ቢከብደን ምን ይገርማል? ምንም!

በቆምኩበት የሄድኩበትን ረስቼ ስለቅልቅልና ሚስቶ ሳስብ ሆዴ ክፉኛ ጮሆ አነቃኝ። ውስጤ አንጀት የሚያርስ አሪፍ ምግብ መብላት አማረው። ‘አማረኝ’ ማለት የሁላችንም ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብት ከሆነ ውሎ አድሯል። ድሮስ? ድሮማ ኃላፊነቱ የተወሰነ የእርጉዝ ሚስቶቻችን ብቸኛ ምልክት ነበረ። አንድ የሰማሁትን ቀልድ ጣል ላድርግላችሁ። ሁለት ባልና ሚስቶች ትንሽ ቀደም ባለው ጊዜ

የመጀመርያ ልጃቸውን ሊወልዱ ሚስት እርጉዝ ነበረች:: ተኝተው በእኩለ ሌሊት ሚስት ባሏን ትቀሰቅስና ‹‹ክትፎ አማረኝ!›› ትለዋለች። ተሯሩጦ ከየትም ከየትም ብሎ አምጥቶ ያበላታል። ለሁለተኛውም ልጅ እንዲሁ። ዘንድሮ ነው አሉ። ሚስት ሦስተኛዋን አርግዛ (ኑሮ ምን ቢከብድም ወልዶ መክበድ የሚቆም አይመስልም) እኩለ ቀን ላይ ‹‹ክትፎ አማረኝ!›› ስትለው፣ ‹‹አሁንስ እኔንም አምሮኛል፤›› ብሏት አረፈው! ባልም ሚስትም በአምሮት ተሰቃይተው የሚወልዱት ልጅ ትንሽ ከፍ ሲል በአምሮት ዙሪያ ምን ይል ይሆን? አደራ ደግሞ አንበርብር ጠይቆናል ብላችሁ ወልዶ ለመስማት እንዳይከጅላችሁ። መቼም የዛሬ ሰው ጥያቄ መመለስን በሽልማት ለምዶ ለመሸለም የማይሆነው ነገር የለም።

ቶሎ ብዬ ጉዳዬን ለመጨራረስ ስላሰብኩ ሥራውን አቋርጦ እንዲያነጋግረኝ ቻይናውን በዓይኔ ጠቀስኩት። አጠር ወፈር የሚለው ቻይናዊ በትናንሽ ዓይኖቹ አፍጥጦ ሊያየኝ እየሞከረ ከቀረበኝ በኋላ እንዳስታወሰኝ ነገረኝ። እውነትም የአማርኛ ቃላት አደራደሩ ግሩም ነው። እኔማ ከሩቅ ምሥራቅ ሳይሆን ከመንዝ አካባቢ የመጣ ነበር የመሰለኝ:: የመጀመርያ ቀን በሩቁ ስለተያየን በደንብ አልተዋወቅንም እንጂ መገረሜ ቀደም ብሉ ይታወቅ ነበር። ወዲያው የመጣሁበትን ጉዳይ ስነግረው ከታች ብቻ ታጥቆ እጅጌዎቹን ወገቡ ላይ ያሰረውን ቱታ ወዲያው ፈትቶ አወላለቀና ‹‹አሁኑኑ አሳየኝ!›› አለኝ። ወስጄ ከባለቤቱ ጋር አገናኝቼው መኪናውንም ካየ በኋላ ስልክ ቁጥሬን ተቀብሎ ተመልሶ ወደ ሥራው ሄደ። እኔም ምሳዬን ልበላ ቤቴ ጎራ አልኩ። ውዷ ማንጠግቦሽ ቡናውን አቀራርባ ወጡን ሞቅ ሞቅ አድርጋ የጎዳደለው እንዳያስታውቅ ያለውን በባለሙያ እጇ አጣፍጣ ሠርታ ጠበቀችኝ። እውነት ለመነጋገር እኮ የሌለንን ስናስብ

ይመቻችሁ!ያለንን ማጣፈጡን ከረሳነው ዘመን የለንም። ስለባቡር እያሰብን ታክሲና አውቶቡሱን በፍጥነት ማቀራረቡን፣ ስለዓባይ ግድብ እያሰብን በየአካባቢያችን እየፈነዱ ያስቸገሩንን ትራንስፎርመሮች መጠጋገንን፣ ስለማኅበር ቤት ግንባታዎች እያለምን የኮንዶሚኒየም ቤቶች የኪራይ ዋጋ ንረትን ማቃለልን (ባለቤትነቱንማ እርሱት)፣ ወዘተ አቅቶናል:: መቀየር፣ ማሻሻል፣ ማስታገስ የሚባል ነገር አላውቅ ብለናል። ‘ብልጥ ልጅ እየበላ ያለቅሳል’ እንዲሉ እኛስ ያየዝነውን ይዘን ብናለቅስ አይበጀንም ትላላችሁ?

ከማንጠግቦሽ ጋር ስለውሎና ሥራ እያወራን ቆየንና ድንገት ዓይኔ ወደ እግሯ ተመለከተ። ባዶ እግሯን ወዲያ ወዲህ ስትካለብ መዋሉዋን ያን ጊዜ አስተዋልኩ። ‘ወይ ዕዳ! አሁን አፍ አውጥታ ጫማ ግዛልኝ ማለት ከብዷት ነው? በአሽሙር መነገሩ ይሆን?’ እያልኩ ሳወጣ ሳወርድ ቆይቼ፣ ‹‹ማንጠግቦሽ! አሁን እኔን ለማሳጣት ነው እንዲህ የምትሆኝው? ምናለበት በግልጽ ጫማ ግዛ ብትይኝ?›› ስላት ከት ብላ ሳቀችብኝ:: ከዚያም ‹‹አይ አንተ። የቁልቢውን ስለት ስላለብኝ ነው አዲስ ጫማ ፈልጌም አይደለም፤ አንተንም ለማሳጣት አይደለም፤›› ብላ መልሳ መላልሳ መሳቋን ቀጠለች። የወጪ ነገር እንዳንገፈገፈኝ ታዝባኛለች መሰለኝ? እኔም ማንም ሰው የፈቀደውን እንደፈቀደው የማመንና የማግኘት መብት እንዳለው ጠንቅቄ ስለማውቅ ስለተሳለችው ስለት አስጨንቄ ሳልጠይቃት ቀረሁ። ‹‹ጉዳያችንን ሁሉ ከእግዜሩ ጋር አዛምደን መኖራችን እንዴት ጠቅሞናል መሰለህ አንበርብር? ለብዙ ጥፋትና ስህተት ሰፊ ትዕግስት ያገኘነው ከየት ይመስልሃል?›› የሚሉኝ ባሻዬ ናቸው። እኔም አንዳንዴ ‘እውነታቸውን እኮ ነው ባሻዬ። ሰው የሰው ብቸኛ ተስፋው ቢሆን ኖሮ በዚህ መጨካከንና ለራስ ብቻ ማሰብ በገነነበት ጊዜ ምን ይውጠን ነበር?’ እላለሁ። እውነት ምን ይውጠን ነበር? አንዳንዴ እኮ ፈጣሪ የሰጠንን አየር ቆጣሪ ሊያስገቡለት የሚፈልጉ እንዳሉ ሳስብ ‹‹እባብ ልቡን ዓይቶ እግር ነሳው›› የሚለው አባባል ይመስጠኛል::

እስኪ እንሰነባበት። ስልክ ቁጥሬን

ቢቀበለኝም የውኃ ሽታ ሆኖ የቀረውን ቻይናዊ እየተጠባበቅኩ በጎን ሌሎች ተባራሪ ሥራዎችን ስሠራ ውዬ አደርኩ። አንድ ቀን አመሻሽ ላይ ከባሻዬ ልጅ ጋር የተለመደው ግሮሰሪያችን ልንሰየም በሩ አጠገብ ከመድረሳችን የጥሪ ድምፅ ሰማን። ከአስፓልቱ ጠርዝ ቻይናው የገዛውን ‘ላንድ ክሩዘር’ መኪና አቁሞ በሰው ሲያስጠራኝ አየሁት። ‘ከመቅረት መዘግየት’ እያልኩ ስጠጋው ጋቢና ጠይም አሳ መሳይ ኢትዮጵያዊት ‹‹ልዕልት›› መቀመጧን ጨምሬ ታዘብኩ። (ከባለትዳር እንዲህ ይጠበቃል? ሃሃሃ) ቆንጆ መኪና ባለበት ቆንጆ ሴት አልጠፋ ያለችበት ምክንያት ግን ምን ይሆን? ብላችሁ ሞኝነቴ ገዝፎ ይታያችኋል:: መኪናውን ገና የዚያን ቀን መቀበሉንና ዝም ያለኝ አውቆ እንደሆነ በተቀላጠፈ አማርኛው አስረድቶኝ ሞቅ ያለ ‘ኮሚሽኔን’ ሸጎጠልኝ። ከባሻዬ ልጅ ጋር ወደ ግሮሰሪው ተያይዘን ዘለቅንና አንድ አንድ አዝዘን ወግ ጀመርን። ‹‹አየህልኝ ቻይናን?›› ስለው ‹‹ምን ታደርገዋለህ? ቁመታቸው ቢያጥርም ልባቸው ግዙፍ ነው፤›› ሲል ተሳሳቅን። ‹‹ለመሆኑ ዕድገታችን ከ11 በመቶ ወደ 8.5 በመቶ ዝቅ ማለቱን ሰምተሃል?›› አለኝ ከተቀዳው ቢራ እየተጎነጨለት። እኔም እንዳልሰማሁ ስነግረው ‹‹ለነገሩ ሰማህ አልሰማህ ዋናው ማደጉ ነው። አነሰም በዛም አድገናል ነው ጨዋታው!›› ብሎኝ ልገምተው ባልቻልኩት የሐሳብና የትካዜ መስመር ጭልጥ ብሎ ተጓዘ። ‘አነሰም በዛም አድገናል!? ወይ አማርኛ?’ እያልኩ በልቤ በገዛ ሐሳቤ ውስጥ ጭልጥ ብዬ ጠፋሁ። በሐሳብ ባህር ውስጥ ሆኜ የደጋገምኩት ቢራ ሞቅታ መፍጠር ሲጀምር ምቾት ውስጥ ያለሁ አስመሰለኝ:: እንጀራ የሚባለው ነገር ከላይ ታች የሚያካልበኝን ረስቼ ለራሴ በፈጠርኩት የምቾት ባህር ውስጥ ሰጠምኩ:: ‹‹አንዳንዴም በዋልድባ ይዘፈናል›› ያለው ማን ነበር? በገሐዱ ዓለም ያጣነውን ምቾት በምናብ ስናመጣው እንዴት ይመቻል? እናንተንም ይመቻችሁ! መልካም ሰንበት!

Page 52: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 4 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

ማስታወቂያ

የጭነት ተሽከርካሪዎች ሽያጭ ጨረታድርጅታችን 3(ሦስት) በጣም ጥሩ ይዞታ ላይ የሚገኙ ኢሮ ትራክ የጭነት

ተሽከርካሪዎችን ከነተሳቢዎቻቸው በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ፣ ይህ ማስታወቂያ በሪፖርተር ጋዜጣ

ከወጣበት ዕለት ጀምሮ፣ ዘወትር በሥራ ሰዓት፣ የማይመለስ ብር 50.00

(ሃምሳ ብር) በመክፈል በድርጅቱ ዋና መ/ቤት፣ ቃሊቲ ኖክ ማደያ ፊት ለፊት

የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ በሚገኝበት ህንፃ ሁለተኛ ፎቅ በመቅረብ

መግዛትና ተሽከርካሪዎቹን መመልከት ይችላሉ፡፡

ተጫራቾች አንዱንም ሆነ ሁሉንም ተሽከርካሪዎች ከነተሳቢዎቻቸው

የሚገዙበትን ዋጋ 15% የተጨማሪ እሴት ታክስ በማከል፣ ለዚሁ ሲባል

በተሰጣቸው የጨረታ ማቅረቢያ ሰነድ ላይ ብቻ በመሙላት፣ እስከ የካቲት

12 ቀን 2005 ዓ.ም. ከቀኑ 10፡30 ድረስ በዋናው መ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ

ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ

ቦንድ ብር 100,000.00 (አንድ መቶ ሺ ብር) በሲፒኦ ቼክ ከጨረታው ሰነድ

ጋር አንድ ላይ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው የሚከፈተው የካቲት 13

ቀን 2005 ዓ.ም. ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ላይ በዋናው መ/ቤት በሥራ አስኪያጅ

ቢሮ ይሆናል፡፡

ድርጅቱ ለተሽከርካሪዎቹ ሽያጭ የተሻለ ዘዴ ካገኘ፣ ጨረታውን በሙሉም

ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብት አለው፡፡

ሞባይል 0911-52-22-21

የቢሮ ስልክ 0114-39-49-59

0114-39-13-89

0114-39-24-10

INVITATION TO BID FOR EXTERNAL AUDIT

Cooperazione Internazionale (COOPI) is an international independent Italian based non-governmental organization founded in Italy in 1965. Since then COOPI has been undertaking activities to help and empower the poor and needy in different countries. COOPI Ethiopia started its operation in 1994 and re-registered under charity and society (CSA) number 0981 on November 25,2009. COOPI Ethiopia would like to invite interested bidders to perform General Audit of the accounts of the Organization for three consecutive years commencing from the year ended on 31 December 2012. The external audit includes accounts of COOPI Ethiopia Head office and all projects during the periods. The Audit engagement for the year ended on 31 December 2012 shall be commenced within ten days after notification of the winner at COOPI Ethiopia Head office, Addis Ababa.

Requirements; The Audit firm should

1. Have Certificate of professional competence issued by the Office of Federal Auditor General

2. Provide evidence of paying current profit tax TIN and VAT certificate and renewed business license for the current year

3. Have experience in auditing Non-Governmental Organizations (NGO)

Therefore, Interested and competent bidders fulfilling the above requirements are invited to submit their technical and financial proposal, and the time needed to complete the audit within seven working days of this announcement in a sealed envelope to the office located near Imperial Hotel or send their sealed envelope to the following address;

COOPI EthiopiaP.O.Box 2204Addis Ababa

For further information please contact us on 0116-293149 or 0116-298528.

Page 53: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 5 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2ማስታወቂያ

Page 54: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 6 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

ማስታ

ወቂያ

አ ስ ተ ያ የ ት

በተሾመ ብርሃኑ ከማል

የዛሬ 31 ዓመት «ላይፍ መጋዚን» በተባለ መጽሔት በዚህ ርእስ አንድ ጽሑፍ ወጥቶ የአንባቢያንን ስሜት ስቦ እንደነበረና ብዙ አስተያየቶች ቀርበውበት እንደነበር የዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ ያስታውሳል:: መልዕክቱ ለአገራችን ወጣትም አስፈላጊ ቢሆንም የዛሬ 31 ዓመት ለማቅረብ ሲሞከር «የትኛው አርበኛ?» የሚል ጥያቄ ማስነሳቱ ስለማይቀር መተው ያለጥርጥር አማራጭ አልነበረውም:: ስለሆነም አቅጣጫውን በመቀየር የካቲት መጽሔት ቁጥር 2 (1981) «ፈጠራና የፈጠራ ሰዎች» በሚል ርእስ በዓለም የታወቁ የፈጠራ ሰዎችና የፈጠራ ሥራዎቻቸውን የሚዳስስ ጽሑፍ ለንባብ ቀረበ:: «ከዛሬ ነገ ይቀርባል» በሚል በመካከሉ ብዙ ዓመታት አለፉ:: እነሆ ዛሬ ጊዜው ሆኖ ግን ከጊዜው ጋር ተጣጥሞ ለመቅረብ በቃ:: በመሠረቱ «አዲስ ዓይነት አርበኞች ያስፈልገናል» በሚል ርዕስ የዛሬ 31 ዓመት ለንባብ ያበቁት ራልፍ ኔደር መሠረታዊ መልዕክታቸው «አርበኞች አባቶቻችን ከጠላቶች ጋር በመፋለም ነፃነታችንን፣ ሰላማችንና ዳር ድንበራችንን አስከብረውልናል:: ዛሬ ወጣቱን ትውልድ አርበኛ ለማድረግ ምን ማድረግ አለብን?» ከሚል የሚነሳ ነው::

ልክ እንደ አሜሪካዊው ጋዜጠኛ እኛም «አርበኞች አባቶቻችን ከጠላቶች ጋር በመፋለም ነፃነታችንን፣ ሰላማችንና ዳር ድንበራችንን አስከብረውልናል:: ዛሬ ወጣቱን ትውልድ አርበኛ በተለይም የልማት/የሕዳሴ አርበኛ ለማድረግ ምን ማድረግ አለብን?» ብለን እንጠይቅ:: መልሱን በትክክል ለመገንዘብን የአገራችንን ወጣት በዓይነ ሕሊናችን እንመልከት:: ከግማሽ በላዩ ወጣት ነው:: «ይህ ወጣት ትውልድ ዓለምን ለመጨበጥና እንደምትመቸው አድርጎ ለመግራት ብርቱ ፍላጎት ያለው ትውልድ ነው፤» ብለን እንውሰደው:: በባሕሪያቸው ቦዘኔነት ለሚያጠቃቸውም ቢሆን ትንሽ ቦታ እንተውላቸው:: በመጀመሪያ ግን «አርበኝነት ምንድነው?» አርበኝነትን ለጊዜው «የጦር መሣሪያ ትግል» እና «የልማት አርበኝነት» ብለን በሁለት እንክፈለው::

የጦር መሣሪያ ትግል የተደረገበት አርበኝነትበአማርኛችን «አርበኛ» የሚለው ቃል «አርነት/

ነፃነት በእኛ እውን ይሆናል» እንደ ማለት ነው:: ከጣሊያን ጋር አምስት ዓመት የተዋጉ ኢትዮጵያውያን «አርበኞች» ተብለው ይታወቃሉ:: እነዚህ አርበኞች ቅኝ አገዛዝን አንቀበልም፣ ጭቆናን አንሻም፣ ፍትሕ የሌለው ሥርዓትን እንቃወማለን በማለት ጣሊያን ለመውጋት፣ በመውጋትም ድል ለማድረግ ቆርጠው ጫካ የገቡ ናቸው::

«ጥራኝ ጫካው፣ ጥራኝ ዱሩ፤ ላንተም ይሻልሃል ብቻ ከማደሩ» ብለው ሚስትና

ልጆቻቸውን ሀብት ንብረታቸውን ትተው የሸፈቱ ናቸው::

ዘመኑ የአርበኝነት ዘመን ስለነበርም ላልዘመተው‹‹ባትዋጋ እንኳ በል እንገፍ እንገፍ::ያባትህ ጋሻ ትኋኑ ይርገፍ::እምየ ምንሽር፣ እምየ እናት አልቤን አለቀሰ

እንደሰውእመደብ ላይ ሆኖ ትኋን እየላሰው›› ተብሎ

ቅስቀሳ ተደርጎላቸዋል:: ሌሎችም ወኔ የሚቀሰቅሱ ፉከራዎችና ሽለላዎች የነበሩ ቢሆንም ለጊዜው እንተዋቸው::

ከዚህም በተጨማሪ «የጦር ሜዳ አርበኛ»፣ «የውስጥ አርበኛ» አለ:: የጦር ሜዳው አርበኛ ጣሊያን ከገባበት ጊዜ ጫካ ገብቶ የጦር መሣሪያ ትግል የጀመረ ሲሆን አገልግሎቱም ከአንድ ቀን እስከ አምስት ዓመት ሊደርስ ይችላል:: የውስጥ አርበኛው ደግሞ የጦር መሣሪያ ትግል ባያደርግም የጣሊያን ደጋፊ መስሎ ወይም ሳይመስል አርበኞቹን በልዩ ልዩ መንገዶች የሚረዳና ለመርዳቱ በምስክር የተረጋገጠለት ነው:: ከነዚህም የውስጥ አርበኞች መካከል የታወቁ የኢጣሊያ ባንዳዎች የነበሩ ነገር ግን ውስጥ ለውስጥ ይረዱ ነበር ተብለው የሚታሰቡ ናቸው:: ዕርዳታውም አርበኛውን በጨለማ ተቀብሎ ማስተናገድ፣ ልብስ መላክ፣ ኬላ አልፎ እንዲሄድ መፍቀድ፣ ቢታሰር መፍታት፣ ቤተሰብ መርዳት፣ መረጃ ማስተላለፍ ሊሆን ይችላል:: ለምሳሌ «የጣሊያን ወታደሮች ዛሬ

በዚህ በኩል ስለሚያልፉ ዘወር በሉ» ወይም «ይህን ያህል ጦር ይዞ ስለተንቀሳቀሰ ጠብቃችሁ ግጠሙት» የሚል ሊሆን ይችላል::

በሌላ በኩል ደግሞ አርበኞችን ሲወጉ ከቆዩ በኋላ ነፃነት ሲመለስ «በውስጥ አርበኝነት›› ስም፣ በጉቦም በዘመድም አርበኞች ሆነው ግራዝማች፣ ቀኛዝማች፣ ፊታውራሪ፣ ደጃዝማች የሆኑ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ:: በተቃራኒው ደግሞ አርበኞች ቢሆኑም አርበኝነታቸው ሳይታወቅላቸው የቀሩ፣ ካሣ ሳያገኙ የቀሩ፣ ወደ አርበኝነት ሲወጡ የነበራቸው ንብረት መሬታቸው ጭምር በባንዳዎች ተበልቶ የቀረባቸው፣ አምስት ዓመት ሙሉ በረሃ ለበረሃ መንከራተት ሳያንሳቸው ከነፃነት በኋላ ፍትሕ አጥተው ሲንገላቱ የሞቱት ብዙዎቹ ናቸው:: ለዚህ ነው «እምዬ ኢትዮጵያ ሞኝ ነሽ ተላላ፤ የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ» እየተባለ የተዘፈነው:: ለነገሩ ብዙ ጊዜ ተጠቃሚ የሚሆነው ለዓላማው የሞተውና ለዓላማው የቆመው ሳይሆን ዓላማውን የሚገድለውና ከሀዲው እንደሚሆን ብዙ ማብራሪያ አያስፈልገውም::

ከዛሬ ሰባ ዓመት ወዲህ የታየው አርበኝነት በግድ የጣሊያን አርበኛ መሆን አያስፈልግም:: የአርበኛ ልጅም አርበኛ የሚሆንበት ሁኔታ ስለሚስተዋል ትርጉሙን ማስፋት እንገደዳለን:: ይህ የሆነው ያለ ምክንያት ላይሆን ይችላል:: በአምስቱ የጣሊያን ወረራ በጫካ ውስጥ እናቱና አባቱ ሲዋጉ የተወለደ ሕፃንም አርበኛ ስለነበር ትልቁ አርበኛ ከሆነ ከነፃነት በኋላ የተወለደም አርበኛ ቢባል ስለማይጎዳ ምናልባትም አርበኛ ሆኖ መቆየቱ ሌላ ጦርነት ቢነሳ በቀላሉ ለማዝመት ስለሚቻል ሊሆን ይችላል:: ጦር ሜዳ የዘመተው እግሩ እስኪቀጥን በመመላለስ ደጅ እየጠና ሳያገኝ፣ ያልዘመተው የግራዝማች፣ የቀኛዝማች፣ የፊታውራሪ፣ የደጃዝማች ማዕረግ የሚያገኝበት ሁኔታ ነበር:: ለመሆኑ የአሁኖቹ የአርበኞች ማኅበር አባላት እነማን ናቸው? ከዚህ ቀጥሎስ የኅብሩ ዕጣ ፋንታ ምን ይሆን? አርበኝነት በልጅ ልጅ ይተላለፍ ይሆን? ይህ ከሆነ አርበኝነት ከምን ሊጀምር ይችላል? ከአብርሃ ወአጽብሃ እስከ አፄ ኃይለ ሥላሴ ወይስ እስከ ኢሕአዴግ አርበኞች ይቀጥል?

አዲስ ዓይነት አርበኞች ያስፈልጉናል

Page 55: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 7 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2ማስታ

ወቂያ

ወደ ክፍል 2 ገጽ 28 ዞሯል

አ ስ ተ ያ የ ት

በበኩሌ አርበኞች ምን እንደሚሉና እንደሚሰማቸው አላውቅም:: መንግሥትም እንደ አንድ ጉዳዩ አድርጎ አያየውም የሚል ግምት የለኝም:: ዳሩ ግን ነገርን ነገር ያነሳዋል በሚል ነገሩን ለማንሳት ያህልና ወጣቱም ትውልድ እግረ መንገዱን ስለዱሮ አርበኞች ጥቂት አሳብ እንዲኖረው በማሰብ እንጂ የጦር ሜዳ አርበኞች ጉዳይ አንገብግቦኝ ስላልሆነ ወደ ልማት አርበኞች ላተኩር::የልማት አርበኞች

የልማት አርበኞች ስንል ምን ማለት እንደሆነ ለማብራራት እንችል እንደሆን አንዳንድ ሊሄዱ የሚችሉ መሠረታዊ ጉዳዮችን እናንሳ:: በመግቢያው ላይ አርበኛ ማለት «አርነት/ነፃነት በእኛ እውን ይሆናል» የሚል አንድምታ እንዳለው ለመግለጽ ተሞክሯል:: አርበኝነትንም ሆነ ነፃነትን ቅኝ ገዥ ጠላትን ተዋግቶ ከአገር ማስወጣት ማለት እንደሆነም ለማሳየት ጥረት ተደርጓል:: ነገር ግን አርነት/ሐርነት የሚያስፈልገው ከጠላት ጋር ለመዋጋት ብቻ ነው? የአሁኖቹ ሊቃውንት በዚህ አይስማሙም:: የልማት አርበኛ በመሆንም ከፍተኛ ሰላም፣ ዲሞክራሲና ፍትሕ ማምጣት ይቻላል::

ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከነፃነት በኋላ በተቀዳሚ መሥራት የጀመሩት ትምህርት ቤቶችን በማቋቋምና በማስፋፋት ላይ ነበር:: ያኔ ለመማር የነበረው ፍላጎት ዝቅተኛ ስለነበር እስከ 1953 ዓ.ም. ድረስ ልብስ እየተሰጠ፣ ደብተርና እርሳስ እየተሰጠ ሁለተኛ ደረጃ ሲሆኑም አዳሪ ትምህርት ቤት እየገቡ ነው:: እስከ ስድስተኛ ክፍል «የተማረ ያስተምር» በሚል መፈክር ለአስተማሪነት ሥራ መቀጠር ይቻል ነበር:: የቢሮ ኃላፊዎች በአብዛኛው ያልተማሩ ስለነበሩ ፀሐፊዎቻቸው አንደኛ ክፍልም ሁለተኛ ክፍልም ሊሆኑ ይችላሉ:: ኃላፊዎችም ለፀሐፊዎቻቸው የሚፅፉትን ይነግሩና አንድም ስም መሰል ነገር በመጻፍ ይህም ካልሆነ የአውራ ጣት አሻራቸውን በማስቀመጥ፤ ተለቅ ተለቅ ያሉት ደግሞ በስማቸው የተቀረፀላቸውን ማህተም በማተም ደብዳቤ ወጭ ያደርጉ ነበር:: ቆጥሮም ቢሆን የሚያነብ የአንደኛና የሁለተኛ ክፍል ተማሪ ተፈልጎና ተለምኖ ይመጣና ትዕዛዙን ያነባል:: ካለበለዚያም የአንድ ቀን መንገድ ተጉዞ ማስነበብና ማፃፍ ሊጠይቅ ይችላል:: ከተገኘ ከተነበበ በኋላ በመላሹ እየተነገረው መልስ ይጽፋል:: በመጻፉም ሳንቲምም፣ (አምስት አስር) ይሰጠዋል:: ወይም ምሳውን በጌታ ቤት ግጥም

አድርጎ ይበላል:: ከ1953 ዓ.ም. ወዲህ ማለትም 25 ዓመት ያህል የትምህርት አርበኝነት ዘመቻ ከተካሄደ በኋላ ዩኒቨርሲቲ ለመቋቋም በቃ:: ስለዚህ ለ25 ዓመታት የተካሄደው የአርበኝነት ዘመቻ የአሁኑን ትውልድ ከሞላ ጎደል ካለማወቅ ነፃ አወጣ::

ከ1953 - 1966 የነበረው ዘመን በአገሪቱ ተንሰራፍቶ የነበረውን ፊውዳላዊ ሥርዓት ለማስወገድ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ፣ «የዲሞክራሲ አርበኝነት ዘመቻ ተካሂዷል» ይህም እውን ይሆን ዘንድ ከፍተኛ መስዋዕትነት ተከፍሏል:: በተከፈለው መስዋዕትነትም ፊውዳላዊው ሥርዓት ተወግዶ በኢትዮጵያ ውስጥ የተለያዩ ፓርቲዎች ተመሥርተው የተለያየ ርዕዮተ ዓለም አራምደዋል:: ለ17 ዓመታት ዲሞክራሲን እውን ለማድረግ በተደረገ ዘመቻም አገራችን አንድ ጊዜ ወደ ምሥራቅ ሌላ ጊዜ ወደ ምዕራብ እየተናጠች ጊዜውን አሳልፋዋለች:: ከእዝ ኢኮኖሚ ወደ ነፃ ገበያ ኢኮኖሚ ለማሸጋገር የተካሄደው ትግል እንዲህ በዋዛ የሚገለጥ አይደለም:: ከግራም ከቀኝም ያለው ታሪክ በጣም ሰፊ ነው:: ለማንኛውም የልማት አርበኝነቱን ታሪክ መጀመር ያለብን ካለንበት ስለሆነ ስለሱ እንነጋገር:: ይህ ጉዳይ መነጋገር የማይፈልጉትን ተቃራኒ አርበኞችን ላይመለከት ይችላል:: የሚመለከታቸው የተጀመረው ልማት ወደፊት መቀጠል አለበት ብለው የሚያምኑትን ብቻ ነው:: ስለሆነም የልማት አርበኝነትን ከምን እንጀምር? ምናልባት ከአገር ፍቅር አርበኝነት? ይሁን!የአገር ፍቅር አርበኝነት

አገርን አርበኛ ሆኖ ለማልማት ከሁሉ አስቀድሞ የሚያስፈልገው ጥልቅ የአገር ፍቅር ነው:: ወጣቱን ትውልድ በአሁኑ ጊዜ በግንባር ቀደምትነት ከሚያስፈልጉት ነገሮች አንዱ የአገር ፍቅር ስሜትና የአገር ፍቅር ወኔ ነው:: የአገር ፍቅር ስሜትና የአገር ፍቅር ወኔ ከራስ ወዳድነት ስሜት ተላቆ «እኔ ለአገሬ ዕድገት እሠራለሁ፤ ወገኖቼን ከረሃብ ከእርዛት ነፃ ለማውጣት ቆርጨ ተነስቻለሁ:: ይህም ብርቱ ዓለማዬ ግብ እስኪደርስ ኃላፊነትና የሞራል ግዴታ ኖሮኝ አስፈላጊውን መስዋዕትነት እከፍላለሁ፤» ከሚል የሚመነጭ ነው:: «አገሬ በድህነቷ ምክንያት ተዋርዳለች፣ ዝቅ ብላ ታይታለችና ከወደቀችበት አነሳታለሁ፤» የሚል ቁርጠኛ ውሳኔ በራስ ላይ ማስተላለፍንም ይጨምራል:: በተወለድንባት፣ እየተጫወትን ባደግንባት፣ በተማርንባት ከጓደኞቻችን ጋር በጨፈርንባት አገራችን ፍትሕና ዲሞክራሲ እንዲለመልም ተግቼ እሠራለሁ ብሎ መነሳትን

ይጠይቃል:: በአካባቢው ሕዝብ ከልማት ጎዳና እንዲወጣ፣ እርስ

በርስ እንዲናቆር፣ በጎ ነገር ሁሉ እንዳያይ፣ የሚያደርጉ እነማን እንደሆኑ ለይቶ በማወቅ ከነዚህ ኃይሎች ጋር ያለምሕረት ይታገላል:: እየታገለም የእርሱን ጥልቅ የአገር ፍቅር እምነት ምን እንደሆነ ያሳውቃል:: አገር ከግል ፍላጎት ጀምሮ የሁሉም ነገር የበላይ እንደሆነ ያስተምራል:: የአገር ፍቅር ስሜት ከልብ መንጭቶ ሲንቦገቦግ የወዳጅን ልብ የበለጠ ሲያበራ የጠላትን ልብ እንደሚያርድ በተግባር ያሳያል:: ጥሪውን እንዲሰሙ ሰምተውም እንዲቀበሉ በፍፁም ቅንነት ይሠራል:: የመቻቻል አርበኝነት

አገራችን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ የመቻቻል አርበኛ ያስፈልጋታል:: የአገር ፍቅር ስሜቱ ሊጎለብት የሚችለውም የእርስ በእርስ መቻቻልና መፈቃቀር ሲኖር እንደሆነ አያጠያይቅም::

መቻቻል በግለሰብ ወይም በተወሰኑ የኅብረተሰብ ክፍሎች ብቻ የሚወሰን ሳይሆን በኅብረተሰብም ሊንፀባረቅ የሚገባው ዓቢይ ጉዳይ ነው:: መቻቻል ብዙ አመለካከት፣ አስተሳሰብ፣ ፍልስፍና፣ ሃይማኖት፣ እምነት በሚስተናገድባት ዓለማችን በዓለማችን ዛሬ የምናያቸውን እጅግ አስቀያሚ ነገሮችን፣ ጠባብ አመለካከቶችንና የእርስ በእርስ ጥላቻን ድል እንደምናደርግ አያጠያይቅም::

አንድ ሰው ጠባብ የጎሳ፣ የብሔር ብሔረሰብ፣ የሕዝብ፣ የዘር፣ የሃይማኖት፣ የእምነት፣ የቋንቋ፣ የቀለም ጠባብ አመለካከት ሲኖረው በጠባብ ዓለሙ ውስጥ በብቸኝነት እንደሚኖር አያጠያይቅም:: የዚህ ሰው ዓለምም እንደ አመለካከቱ ጠባብ ብቻ ሳይሆን ሰዎችም እንደ እርሱ በጠበበች ዓለም የሚኖሩ ይመስለዋል:: በአንድነት ላይ የተመሠረተ ብዝኀነት በተቃራኒው የመቻቻል መሠረት ሲሆን የሌሎቹ መኖር ሐቅነትን፣ የነሱ መኖር ለእርሱ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ሲቀበል ይልቁንም በአንድነት ላይ የተመሠረተ ብዝኀነትን ማስወገድ የማይችል መሆኑን ሲገነዘብ ራሱንም ሌሎችንም መጥላት ይጀምራል:: በተቃራኒውም በአካባቢው ከእሱ ጋር ተመሳስሎ፣ ተቻችሎ፣ የሚኖር መሆኑን ሲረዳ ያኔ አዲስና አብሮ ለመኖር የሚያበቃ ሀቅ ይኖረዋል::

ኸሊል ጂብራን ዕውቅ ሊባኖሳዊ ደራሲ (1883-1931) ብዙ መጻሕፍት በመጻፍ የታወቀና ለዓረብ ሥነ ጽሑፍ በዘመናዊ መንገድ መዳበር አስተዋጽኦ ያደረገ ሲሆን «አንተ ወንድሜ ነህ፤ እኔም እወድሃለሁ:: በቤተ ክርስቲያን መቅደስ ውስጥ ተንበርክከህ

ስታመለክ አፈቅርሃለሁ:: አንተም ወንድሜ በመስጊድ ውስጥ ፀሎት የምታደርሰውን እንደዚያው:: የገናናው ፈጣሪያችን የፍቅር ጣቶች የተዘረጉት ለሁሉም ስለሆነ ለሁሉም ምሉዕነት መንፈስ እየሰጡ ስለሆነና ሁላችንም ለመቀበል በጉጉት የሚጠብቅ ስለሆነ እኔና አንተ ሁላችንም የአንድ ሃይማኖት ልጆች ነን::

የጥቁር አሜሪካውያን ታሪክ ሲነሳ ግንባር ቀደም ሆነው የሚጠቀሱት ማርቲን ሉተር ኪንግ የሰው ልጅ ጥቀር፣ ነጭና ሌላ ቀለም ሳይል አብሮ እንደሚኖር «ሕልም አለኝ» በሚል ጥቅሳቸው በመላዋ ዓለም ይታወቃሉ:: «አመፅ በሌለበት ሁኔታው ውስጥ የፍቅር መርህ አለ፤» በማለትና «ሁልጊዜም ሊባል በሚችል፣ የፈጠራ ችሎታና ሕልማቸውን እውን ለማድረግ ቆርጠው የተነሱ ዉሑዳን ዓለምን የተሻለ ያደርጓታል፤» በማለት የሚታወቁት ማርቲን ሉተር ኪንግ የተሰዉት በሰው እጅ ቢሆንም «አንድም እንደ ወንድማማች በአንድ ላይ መኖርን ማወቅ አለብን፤ ይህ ካልሆነ እንደ ቂሎች አብረን እንጠፋለን፤» በማለት ጥቁርና ነጭ አሜሪካውያን ተቻችለው እንዲኖሩ አበክረው ሲመክሩ እንደኖሩ የሕይወት ታሪካቸው ይመሰክራል:: ማርቲን ሉተር ኪንግ አስተምረው ያለፉት «ጨለማ፣ ጨለማን ሊያባርር አይችልም:: ጨለማን ሊያስወግድ የሚችለው ብርሃን ብቻ ነው:: ጥላቻንም ጥላቻን ሊያስወግድ አይችልም ያንን ማድረግ የሚችለው ፍቅር ብቻ ነው፤» በማለት ነበር::የልማት አርበኝነት

በአሁኑ ጊዜ በአገራችን ከፍተኛ የልማት ሥራዎች እየታዩ ነው:: እነዚህን የልማት ሥራዎች ለማፋጠን የፖለቲካ አመለካከት፣ የሃይማኖት፣ የዘር፣ የጎሳ ወይም የሌላ ልዩነት አያግደንም:: በተጠቀሱትና ባልተጠቀሱት ጉዳዮች ልዩነታችን እንደተጠበቀ ሆኖ አገራችንን ማልማት ያለብንም በአንድ ላይ ሆነን መሆን ይኖርበታል:: በአሜሪካ ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሃይማኖቶች እንዲሁም ዘሮች አሉ:: ቅራኔያቸው ግን ሥርዓቱን እኔ የተሻለ አንቀሳቅሰዋለሁ ከሚል ነው:: ያም ቢሆን በሕዝብ ድምፅ አሸናፊዎች ሲሆኑ ነው:: አብርሃም ሊንከን የተባሉ ፕሬዚዳንቷ አገራቸው እርስ በርስ ጦርነት ስትናጥ በነበረበት ጊዜ የተናገሩት አንድ ትልቅ ቁም ነገር «የመርከቧን መሪ ጨብጠን ወደ ፈለግነው አቅጣጫ ልንመራት የምንችለው ከሁሉ አስቀድሞ መርከቧ ስትኖር ነው፤» በማለት ሕዝብ

Page 56: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 8 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

ማስታወቂያ

Page 57: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 9 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2ማስታወቂያ

Page 58: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 10 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

የሚሸጡ ቤቶች ዝርዝር1. ለቡ አካባቢ ኢንዱስትሪ መንደር ቦታው 5000 ካሬ ስቶሩ 1500 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ያለው

2. የቡና መሬት ሚዛን ተፈሪ ውስጥ 991 ሄክታር መሬት እና በ540 ሄክታር ላይ ተተከለ የ1፣

የ2፣ እና የ3 ዓመት እድሜ ቡና ያለው ማስፋፊያ 1000 ሄክታር መሬት ጋር

3. ጂ+3 ቦታው 250 ካሬ የሆነ አሚቼ አካባቢ

4. ሮፓክ ቪላ ቤት ያለው ቦታው 500 ካሬ የሆነ

5. ቦሌ ሆምስ ግቢ ጂ+1 አዲስ ቤት ያለው ቦታው 500 ካሬ ሜትር የሆነ

6. ሃይሌ ገ/ስላሴ መንገድ ከለም ሆቴል ከፍ ብሎ መንገድ ዳር ቦታው 450 ካሬ የሆነ

በመከራየት ላይ ያሉ ሱቆች ያሉት

7. ገላን ስቶር 500 ካሬ ላይ የዋለ ፊኒሺንግ የቀረው ቦታው 3000 ካሬ የሆነ በጥሩ ዋጋ

8. ቀበና ከእንግሊዝ ኤምባሲ አልፎ መንገድ ዳር ጂ+1 ፎቅ ቦታው ከ650 ካሬ

9. ዱከም ቦታው 5000 ካሬ 1000 ካሬ ላይ የዋለ መጋዘን ያለው ለፋብሪካ የሚሆን መብራት

የገባለት

10. ገላን አካባቢ የካርቶንና የሶፍት ወረቀት ፋብሪካ በመስራት ላይ ያለ ቦታው 10000 ካሬ ስፋት

1200 ካሬ ሜት መጋዘንና ጂ+2 ቢሮ በተጨማሪ 300 ካሬ ስቶር ያለው በሽያጭ ወይም

በጋራ ለመስራት የተመቻቸ

11. ሰበታ የከብት ርቢ በመስራት ላይ የሚገኝ ከሃያ በላይ ላሞች ያሉት

ማሳሰቢያ፡- ከእነዚህ ሌላ በተለያዩ አካባቢዎች የሚሸጡ ሆቴል፤ እንግዳ ማረፊያ (ገስት ሀውስ) አሉን

በሚፈልጉት አካባቢ የሚሸጡ መኖሪያ ቤቶች መንገድ ዳር ለፎቅ የሚሆኑ ቦታዎች ስላሉን

የሚከራይም ሆነ የሚሸጥ ቤት ካሎት ይደውሉ፣

አድራሻ፣ ስልክ፡- 0911 21 12 67 ወይም 0911 22 08 22

ኢ-ሜይል፣ [email protected] or [email protected]

ማስታወቂያ

Call for External AuditNational Network of Positive Women Ethiopians (NNPWE) is an umbrella organization of 22 positive women associations operating in all regions of Ethiopia. The overarching goal of the Network is to make a genuine contribution to mitigate the multifaceted effects of HIV/AIDS through greater and meaningful involvement of women living with HIV/AIDS and their association. NPWE is a non- profit local NGO based in Addis Ababa. Registered and licensed with a license no 1434 on February 2, 2010 as an Ethiopian residence charity consortium in accordance with the charities and societies Proclamation No. 621/2009 of the country.

NNPWE invites auditor firms with the following criteria. • Be VAT registered

• Have renewed license

• International affiliation

• Well experience in auditing NGO’s

Interested and competent bidders are invited to collect the TOR and submit their firm’s profile, including technical and financial document between February 10 2013 to February 15 2013 to the following address.

National Network of Positive Women EthiopiansEthio- China road from Wollo Sefer to Gotera,

200 meters from Medico Bio Medical College BuildingIn front of Ethio Tai Message

P.O.Box 1270 code 1250 orEmail [email protected]

Website: - nnpwe.org Tel 011-467 4231/32.

REQUEST FOR EXPRESSION OF INTEREST

Save the Children is the world’s leading independent non-profit organization for children.

Save the Children Ethiopia Country office would like to update/ create required vendor lists for the year of 2013 for packing, moving, storage transport, customs clearing, freight forwarding, crane & fork lift and related service providers. Hence, all companies engaged in related business are invited to participate and submit full company profile including documents mentioned below:

• Renewed business license for the year 2004/ 2005 E.C.

• VAT registration certificate and TIN.

• Company profile showing detailed technical back ground (Machineries, vehicles storage places…), skilled manpower, previous experience and other relevant credentials.

• Availability and acceptance of orders through fax and E-mail.

• Credit facilities.

Vendors may submit their documents to Save the Children Addis Ababa Country office Reception Desk, from February 12 th – 22th, 2012 during working hour 08:00am – 04:30 pm our office located at the following address:-

Save the Children

Ethiopia Country Office

Near Bisrate Gebriel Church, P.O Box 387 Tel 011 3 72 84 55-61 or 011 6 53 51 74

Addis Ababa

REQUEST FOR PROPOSAL- Ref- (RFP-2013-9105395)

1. Topic: Consultancy Services - to provide vehicles maintenance services for UNICEF Ethiopia at Addis Ababa- for period of 24months.

2. Background:

UNICEF Ethiopia owns over 130 vehicles and seeking the services of qualified companies that could provide Vehicle maintenance services for all vehicles those operate in Ethiopia.

3. Objectives: The service provider is expected to provide Maintenance services to all UNICEF owned vehicles.

4. Minimum requirements from the Services Provider:The Contractor should be licensed for such works and registered with concerned authorities.b) The Contractor should have at least five years of experience in the provision of the

Vehicle maintenance services detailed above and should provide accreditations from its current and / or past clients.

c) The Contractor should deploy appropriate and qualified staff all the time.d) The Contractor should have a well-equipped workshop premises and with clear address

and contacts.e) The service provider must have a minimum of grade 5 OR 4, license for the same work

from Ethiopian Road Transport Authority. Levels below these are not acceptable

Interested and eligible bidders are invited to collect the complete tender document by sending an email to the address below starting 11 -Feb- 2013. Formal offers are to be submitted to UNICEF on or before 10.00 am. 28th Feb- 2013. Due to the nature of the bid, there will be no bid public opening for this offer.

UNICEF reserves the right to accept or reject part or all of any or all bids.

ADDRESS: UNICEF ETHIOPIA, Supply Section, Room 112, Attn. Mr. Sebastian Muzuma ([email protected]) P.O.BOX 1169, TEL: +251-11 5184233, ADDIS ABABA, Ethiopia.

Page 59: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 11 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2ማስታወቂያ

INVITATION TO TENDERMercy Corps is an international humanitarian organization operating in the emergency response health and nutrition, Water and Sanitation, Economic development, Livelihoods and Capacity building and similar sectors in the regions of Somali, Oromia, Addis Ababa and SNNPR.Through the principles of Accountability, Participation and peaceful change Mercy Corps works with communities, Public and private sectors to implement relief and development interventions. Mercy Corps is looking for potential suppliers that can supply;

Item No. Item Description Quantity1. Wheel Loader

At least 220Hp, Bucket capacity not less than 3 m3, Fuel Tank capacity not less than 200lts, having turbo charged diesel engine, forward speed not less than 35km/hr , reverse speed not less than 15km/hr and having maximum grade ability of not less than 250.

2

2. Damp Truck4 wheel drive, Single Axle, damp body capacity of 8 to 10m3 and all steel welded construction and having drop rear gate, automatic tail gate releasing system and mechanical safety lock .

2

3. Motor cycles 100-150CC, all road/off road type2 stroke, Petrol,Makes include Indian, Chinese, Japanese

10

4. Motor Cycles 100-150cc, Off road type4 stroke, PetrolMakes include Indian, Chinese, Japanese

10

♦The supplier must be registered by the government of Ethiopia and have to submit renewed business license with a copy of TIN certificate.

♦Has to mention the delivery time.♦Must enclose the bid documents sealed in the envelope and submit to Mercy Corps Ethiopia head office until

Thursday, Feb.14, 2013 5:00 pm.♦The bidders must state and attach;

- The detail specifications and brands of the machines.- Performance history and/or testimonials of the machines in Ethiopia (especially in low land areas)- At least 3 references that are practically using the machines and that can be contacted for checking

actual performances of the machines.- Confirmation on availability of workshop and spare parts locally including locations of workshops

& service places in Somali, Afar and Southern Oromia.♦ Confirmation on reparability in places out of Addis Ababa with the help of qualified mechanics. ♦Mercy corps requests your company to send a representative on Friday Feb.15,2013 at 9:00 a.m to Mercy

corps Ethiopia Head Office located at Arada Kefle Ketema, Kebele 01/02,House No. 054 i.e. Piazza, behind Enrico Pastry, Tel.No.011-1110777 for witnessing the bid opening process.

♦Bids received after this date will not be considered.♦Mercy Corps reserves the right to reject the bid fully or partially.

ናይል ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ. ሲገለገልባቸው የነበሩት ተሽከርካሪዎች፣ ሞተር ሳይክሎች፣ የቢሮ ዕቃዎች (Office Furniture & Office Equipments” እና ኮምፒውተርና ተጓዳኝ ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ የጨረታው አፈፃፀም 1. ማንኛውም ተጫራች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ንብረቶቹ

በሚገኙበት አድራሻ ዘወትር በሥራ ሰዓት በመመልከት የተ.ዕ.ታክስን ጨምሮ የመግዣ ዋጋቸውን እስከ የካቲት 15 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ሠዓት ድረስ በታሸገ ፖስታ ለዚሁ ዓላማ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

2. ተጫራቾች የንብረቱን ጨረታ መነሻ ዋጋ 20% በባንክ በተረጋገጥ ቼክ (ሲፒኦ) ብቻ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

3. አሸናፊው ጨረታውን ከአሸነፈበት ቀን ጀምሮ ባሉት 1ዐ ቀናት ጊዜ ውስጥ ገንዘቡን ገቢ በማድረግ ንብረቱን መረከብ ይኖርበታል፡፡ ይህ ካልሆነ ያስያዘው ገንዘብ ለኩባንያው ገቢ ይሆናል፡፡

4. የጨረታው አሸናፊ ማንኛውንም የመንግስት ግብር ወይንም ታክስ እንዲሁም የሥም ማዘዋወሪያ ወጪ ይሸፍናል፡፡

5. ኩባንያው የተሻለ መንገድ ከአገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

6. ጨረታው የካቲት 16 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡3ዐ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኩባንያው የመሠብሠቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡

7. የጨረታው መክፈቻና መዝጊያ ቀን በዓል ላይ የሚውል ከሆነ ጨረታው የሚከፈተው ወይንም የሚዘጋው በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል፡፡

አድራሻ ፣ ናይል ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ. ዋናው መ/ቤት /ጎተራ/ የሰው ኃይልና ንብረት አስተዳደር መምሪያ /3ኛ ፎቅ/ የመ.ሣ.ቁ. 12836 የስልክ ቁጥር 0114-42 60 00 ፋክስ 0114-42-60-08 አዲስ አበባ

ጨረታ

ለህይወት ኢንሹራንስ ሽያጭ ወኪልነት የወጣ ማስታወቂያ

ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ ከዚህ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶቸ የሚያሟሉ የህይወት ኢንሹራንስ የሽያጭ ወኪሎችን አወዳድሮ በኮሚሽን ማሰራት ይፈልጋል፡፡

የትምህርት ደረጃ - 12ኛ ክፍል ያጠናቀቀ (ች) ና ከዚያ በላይ

የስራ ልምድ - የፋይናንስ ተቋማትና የሌሎች አክሲዮን ማህበራትን አክሲዮን የሸጠ(ች) እንዲሁም በተለያዩ ድርጅቶች በምርት ሽያጭ ወኪልነት የሰራች

ክህሎት - ከፍተኛ የመግባባት ችሎታ ያለው (ያላት) የተወዳዳሪ ድርጅቶችን የገበያ ስልት የመረዳት ችሎታ እንዲሁም የኢንሹራንስ ኢንደስትሪውን አሰራር በሚገባ የሚያውቅ (የምታውቅ)

አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አስር የስራ ቀናት ውስጥ የማይመለስ የትምህርትና የስራ ልምድ ማስረጃ በመያዝ በድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት በአካል በመቅረብ አሊያም ማስረጃቸውን በፖስታ በመላክ መመዝገብ ይችላሉ፡፡ ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ) የመልዕክት ሳጥን ቁጥር 285 ዋና መስሪያ ቤት ደምበል ሲቲ ሴንተር የማርኬቲንግ እና ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት መምሪያ 11ኛ ፎቅ ቦሌ መንገድ ስልክ 011553 51 29 32, 0115543705, 0115527581

Page 60: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 12 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

ማስታወቂያማስታ

ወቂያ

ለሐበሻ ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበር

ባለአክሲዮኖች በሙሉ!

ሐበሻ ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበር ጥር 19 ቀን 2005 ዓ.ም. ባካሄደው

የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባዔ ላይ በተገለጸው መሰረት ባለአክሲዮኖች

ያለባችሁን ቀሪ የአክሲዮን ድርሻ ክፍያ እስከ የካቲት 21 ቀን 2005

ዓ.ም. ከፍላችሁ እንድታጠናቀቁ እያሳሰብን ክፍያውን እስከተጠቀሰው

ቀን ድረስ የማይከፍሉ ባለአክሲዮኖች ያልተከፈለባቸው የአክሲዮን

ድርሻዎች በንግድ ሕጉ አንቀጽ 342 መሰረት ለሽያጭ የሚወጡ

መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ሐበሻ ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበር!

የጨረታ ማስታወቂያኤሊኮ-አዋሽ ቆዳ ፋብሪካ

ኤሊኮ-አዋሽ ቆዳ ፋሪካ ልዩ ያገለገሉ ተሸከርካሪዎች፣ ማሽኖችን፣ የመለዋወጫ

ዕቃዎችን የቢሮ መገልገያ ዕቃዎችን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡

ተጫራቾች፣

1. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው መሆን አለባቸው፤

2. እያንዳዱን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100 ከፍለው መግዛት ይችላሉ፤

3. የጨረታ ማስከበሪያ፣

• ለመኪና የጨረታ መነሻውን 5%

• ለመለዋወጫ ዕቃዎች ብር 5000.00 (አምስት ሺ ብር)

• ለጽ/መሣሪያና የቢሮ ዕቃዎች ብር 3000.00 (ሶስት ሺህ ብር)

• በጥሬ ገንዘብ ወይም በCPO (በባንክ በተረጋገጠ ቼክ) ማስያዝ

ይኖርባቸዋል፡፡

4. የጨረታ ዋጋ ማቅረቢያ ጊዜ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት

9 ተከታታይ የሥራ ቀናት ይሆናል፡፡ የጨረታው መክፈቻ በ10ኛው የሥራ

ቀን ጠዋት በ4፡00 ሰዓት ይሆናል፡፡

5. ድርጅቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ

ነው፡

አድራሻ፣ኤሊኮ-አዋሽ ቆዳ ፋብሪካ ስልክ

ቁጥር 011 442 25 25/011 440 02 14ደብረዘይት መንገድ አቃቂ ቃሊቲ ጉምሩክ አካባቢ

አዲስ አበባ፣

Page 61: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 13 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2ማስታወቂያ

UNIVERSITY OF SOUTH AFRICA

ETHIOPIA REGIONAL LEARNING CENTRE

We are pleased to announce that Unisa* has restarted admitting students to

MASTER OF PUBLIC HEALTH (MPH) program.

Admission applications will be accepted until February 10, 2013.

To apply, please come with originals and two photocopies of the following documents to our Centre located in Akaki.

Academic Documents (degree and transcript)

Curriculum Vitae (CV)

Birth Certificate or Passport

For further information, please call us at 011 4 352244, 011 4 350078, 011 4 345769, or 011 4 352090; write to us at [email protected] , [email protected] ; or visit our Akaki office.

UNISA Regional Learning Centre, P.O.Box 13836, Akaki, Addis Ababa, Ethiopia; Fax: 011-435-1243; Website: www.unisa.ac.za

*UNISA is an open distance learning university owned by the Republic of South Africa.

Learn Without Limits!

Page 62: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 14 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

ማስታ

ወቂያ

Invitation for Local Consultancy Service The USAID/Improving Quality of Primary Education Program (IQPEP) is a five-year country-wide program in Ethiopia working with the Ministry of Education (MoE), the Regional State and City Administration Education Bureaus (RSEBs/CAEBs), Teacher Education Institutions (TEIs), Woreda Education Office (WEOs), Schools, kebeles, and communities to build quality, equity and access to education within Ethiopia’s rapidly expanding primary education sector. IQPEP is funded by the United State Agency for International Development (USAID) and implemented by FHI360 and Pact/Ethiopia.IQPEP also introduces new directions within programs, most notably and emphasis on improving reading proficiency of students in the early primary grades. The IQPEP In-service Teacher Education team, with Support from an international consultant, developed four teacher training modules based upon the findings of Early Grade Reading Assessment (EGRA) that was conducted jointly by the MoE, RTI, and IQPEP during 2010.Now that two years have passed since the first baseline EGRA was conducted, it is time to conduct the second EGRA to measure the impact of the previously mentioned interventions. Like the first EGRA, approximately 9,500 students from 240 schools across Ethiopia will represent both intervention and control schools. The impact assessment will involve a total of about 84 data collectors and supervisors, and will require six days of training and practice by data collectors and supervisors on the content and intent of EGRA instrument (18 – 23 March, 2013). Data will be collected from Eight Regions – Addis Ababa, Amhara, Benshangul Gumze, Harari, Oromia, Somali, SNNP, and Tigray in five Languages- Amharic, Afan Oromo, Sidaminga, Somaligna and Tigrigna. Data will be collected immediately after the training workshop during March 24 - April 10, 2013. Accordingly, the IQPEP would like to hire a local experienced consultant on EGRA who will conduct the training in collaboration with an international consultant during the mentioned period. Therefore, interested applicants holding a Masters degree and above could apply to the project head office. Applicants should submit (in person), non-returnable hard copies of their relevant documents and CV with an application letter within 10 (ten) days from this announcement to the following address.

USAID/IQPEP Ministry of Education, Arat Killo

New Building, 3rd floor, MERA Component Office No. 312

Addis AbabaEthiopia

Application through proxy is not allowed and only short listed candidates will be contacted

የአልሙኒየም ሥራዎች የጨረታ ማስታወቂያ

ባቱ ኮንስትራክሽን አክስዮን ማሕበር በፊንጫ ስኳር ፋብሪካ እያከናወነ ላለው ባለ አንድ ፎቅ ሕንፃ ግንባታ የተለያዩ ቢሮች መስኮቶችና መወጣጫዎች በአልሙኒየም ፍሬምና መስታወት ጨምሮ አቅርቦ ሚገጥም ባለሙያ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ማንኛውም ተጫራች፡-

1. በዘርፋ የታደሰ የንግድ ፈቃድ

2. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢነት ማረጋገጫ

3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሊኖረው ይገባል

4. ዝርዝር የጨረታ ሰነዱን ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ከአክስዮን ማሕበሩ ገንዘብ ቤት መውሰድ ይችላሉ

5. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 10,000 /አሥር ሺህ ብር/ በጥሬ ገንዘብ በመድን ዋስትና ወይም በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ (CPO) ማስያዝ ይጠበቅበታል

6. አሸናፊው ተጫራች ማሸነፋ እንደተገለጸለት የሚገጥማቸውን አሉሙኑየምና መስታወት ናሙና አቅርቦ በተቀጣጣሪ ድርጅት በራሱ ወጪ ያስፈትሻል ደረጃውን የጠበቀ መሆኑ ሲረጋገጥለትም አክሲዮን ማሕበሩ ቀርቦ ውለታ ይፈጽማል

7. ማንኛውም ተጫራች ቴክኒካል እና ፋይናንሻል መወዳደሪያዎቹን ለየብቻ በታሸገ ኤንቨሎኘ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት እስከ የካቲት 18/2005 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ አክሲዮን ማሕበሩ ግዥና አቅርቦት መምሪያ ቢሮ ቁጥር 10 ማስገባት ይጠበቅበታል

8. ጨረታው የካቲት 18/2005 ዓ.ም በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአ/ማሕበሩ አዳራሽ ይከፈታል

9. አክሲዮን ማሕበሩ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ፡- ባቱ ኮንስትራክሽን አ/ማ

ስልክ ቁጥር፡-0113-210251/0113-210248/0113-214262

በምሕረት አስቻለው

አንዲት ሴት መቼና ስንት ልጆች መውለድ እንዳለባት የመወሰን መብት አላት:: የፈለገችውን ዓይነት የወሊድ መቆጣጠሪያ በመረጠችው ጊዜ መጠቀምም የእሷው ውሳኔ ነው:: የተለያዩ አገሮች የሕዝብ ቁጥርን ዕድገት ለመገደብ አልያም ለመቆጣጠር ያስችላቸው ዘንድ የሚያወጡት ፖሊሲ የሴቶችንም ሆነ የወንዶችን የሥነ ተዋልዶ መብት በተለያየ መልኩ ጥያቄ ውስጥ የሚጥልበት አጋጣሚ ቢኖርም የመውለድ፣ ወሊድን የመቆጣጠርና ሌሎችም ተመሳሳይ የሥነ ተዋልዶ ጉዳዮች የግለሰቦች መብቶች መሆናቸውን ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ይደነግጋሉ::

ዶ/ር ሰለሞን ቁምቢ በጋንዲ ሆስፒታል የማሕፀንና የጽንስ ስፔሻሊስት ናቸው:: ከአሥራ አምስት ዓመታት በፊት በሥነ ተዋልዶና ሥነ ጾታ ጤናና መብት ዙሪያ ስዊድን አገር ትምህርት ተከታትለዋል:: እሳቸው እንደሚሉት ቀደም ሲል የነበረው ነገር አንዲት ሴት የወሊድ መቆጣጠሪያ ተጠቃሚ ለመሆን የተጓዳኟ ይሁንታ ያስፈልጋል የሚል አንድምታ ነበረው:: የሴቶች ብቻቸውን የሚወስኑበት አሠራር አልነበረም:: ይልቁንም ውሳኔው የጥንዶች በተለይም የወንዶችን ይሁንታ የሚጠይቅ ነበር::

እ.ኤ.አ በ1974 ቴህራን ላይ በሚመለከተው ሰነድ ላይ ይህ ውሳኔ የጥንዶች ብቻ ሳይሆን የግለሰቦችም ይሆን ዘንድ ማሻሻያ ተደርጓል:: ከዚያም ከሥነ ተዋልዶ ጤና ጋር በተያያዘ ግለሰቦች እንዲሁም ጥንዶች መረጃና አቅም ማግኘት ይችሉ ዘንድ ሌላ ነጥብ ተጨመረ:: ቢሆንም ዛሬም ጥንዶች የወሊድ መቆጣጠሪያን በሚመለከት ተመካክረው ቢወስኑ ይመረጣል::

‹‹ስለዚህ የሥነ ተዋልዶ ጤና መብት ተጠቃሚ ለመሆን ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው:: የአእምሮ ሕመም ያለባቸውና ከሥነ ተዋልዶ ጤናቸው ጋር በተያያዘ የተለያዩ ነገሮች ላይ መወሰን ለማይችሉም ቢሆንም እንዲሁ ሌላ ሰው ሊወስንላቸው የሚችልበት ሁኔታ የለም:: በተወሰነ መልኩ ነገሩ ላይ ፍላጐታቸውን ማሳየት የሚችሉበት ዕድል መኖሩ በሥነ ልቦና ወይም በአእምሮ ሐኪም ይታያል:: ቢያንስ ፈቃዳቸውን መጠየቅ ይቻል ይሆናል፤›› ይላሉ::

ዓለም አቀፍ ስምምነቶች የአገሮች መመሪያዎች የወሊድ መቆጣጠሪያን መጠቀም የግለሰቦች መብት እንደሆነ በግልጽ ቢያስቀምጡም ይህ መብት በአንድም ይሁን በሌላ መንገድ በግለሰቦች በተቋም ደረጃም የሚጣስበት አጋጣሚ ጥቂት የሚባል አይደለም:: የጥሰቱ መጠን ከባህል፣ ከወግ፣ ከአገሮች የጤናና ሕዝብ ፖሊሲ ጋር ሊያያዝ ይችላል::

ከሁለት ሳምንታት በፊት በተለያዩ መገናኛ ብዙሀን የተላለፈው ወደ እሥራኤል አገር ያመሩ ቤተ እሥራኤላውያን ያለ ዕውቅናና ፈቃዳቸው የወሊድ መቆጣጠሪያ ተጠቃሚ የመሆን ዜና የሥነ ተዋልዶ መብት ጥሰት ማሳያ ነው::

ሴ ት

የመብት ጥሰት ብቻ ሳይሆን ዘረኝነትን መሠረት ያደረገ ዕርምጃ እንደሆነም የሚከራከሩ አሉ:: የእስራኤል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የቤተ እስራኤላውያኑን ቁጥር ለመቀነስ ዕርምጃው እንደተወሰደ አምነዋል:: የእስራኤል የመብት ተሟጋች ማኅበራትም ከዕርምጃው ጀርባ ባለው ዘረኝነት መንግሥትን ወንጅለዋል::

ከአሥራ ስምንት ዓመት በታች የሆኑ ሴቶችን የወሊድ መቆጣጠሪያ የመጠቀም መብትን የሚገድብ ሁኔታስ አለ ወይ?

ቀደም ባሉት ዓመታት ያለ ዕድሜ ጋብቻ ያበረክት የነበረው አስተዋጽኦ የነበረ ቢሆንም ‹‹ዘመናዊነትን››

ተከትለው በመጡ ተፅዕኖዎች አልያም በአቻ ግፊትና በሌሎችም ከአሥራ ስምንት ዓመት በታች ያሉ ልጆች የግብረ ሥጋ ግንኙነት ቀደም ብለው ሲጀምሩ ይታያል::

የ2011 የኢትዮጵያ የሥነ ሕዝብና ጤና ጥናት እንደሚያሳየው ዕድሜያቸው ከ25 እስከ 49 ከሆኑ ሴቶች 29 በመቶ የሚሆኑት ለመጀመሪያ ጊዜ የግብረ ሥጋ ግንኙነት የፈጸሙት 15፣ 62 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ 18 ዓመት ሳይሞላቸው ነው::

‹‹ከአሥራ ስምንት ዓመት በታች የሆኑ ሴቶችን በሚመለከት ከግንዛቤ የሚገቡ ሙያዊ ሥነ ምግባርን መሠረት ያደረጉ ነገሮች አሉ:: ለምሳሌ ከቤተሰብ ተለይተው

የወሊድ መቆጣጠሪያ የግለሰብ ወይስ የጥንዶች ውሳኔ?

የሚኖሩ፣ ያገቡ፣ ሥራ የያዙ ሴቶች ምንም እንኳ ከ18 ዓመት በታች ቢሆኑ በዚህ ረገድ ለመወሰን የበቁ እንደሆኑ ይታሰባል፤›› የሚሉት ዶ/ር ሰሎሞን ከባህልና ከወጋችን አንፃር ከ18 ዓመት በታች የሆነች ሴት የወሊድ መቆጣጠሪያ ለመጠቀም የምታደርገው እንቅስቃሴ በተለያየ መልኩ ጥያቄ ውስጥ ይገባል::

‹‹ክሊኒክ ወይም ፋርማሲ ሔዳ መቆጣጠሪያ ስትጠይቅ የሚጠብቃት አስተያየትና አቀባበል የሚታወቅ ነው:: በመጀመሪያ ደረጃ ማኅበረሰቡ ከ18 ዓመት በታች ያሉ ልጆችን ግብረ ሥጋ ግንኙነት መፈጸም አይቀበልም:: እውነታው ግን አለ::››

አንዳንዱ የልጆቹን ዕድሜ ከግንዛቤ በማስገባት እንደ ባለሙያ አማክሮ ውሳኔውን ለልጆቹ ይተዋል:: በሌላ በኩል ለማማከር ለመተባበርም ፈቃደኛ ላይሆን የሚችል ይኖራል:: የወሊድ መቆጣጠሪያ የጠየቀች ከ18 ዓመት በታች የሆነች ሴትን ቢያስተናግድም መስተንግዶ እንዴት በዚህ ዕድሜዋ ግንኙነት ጀመረች? የሚል ጥያቄን ያዘለ ከዚያም አልፎ ክብርን የሚነካ ሊሆን ይችላል::

ከአሥራ ስምንት ዓመት በታች የሆኑ ሴቶች የወሊድ መቆጣጠሪያ ተጠቃሚ ከመሆን ጋር አገሮች እንደየሁኔታው የተለያዩ አሠራሮችን ይከተላሉ:: ምንም እንኳ ኋላ ውሳኔው ለልጆቹ የሚተው ቢሆንም ለልጆቹ አማካሪ የሚመድቡ አገሮችም አሉ:: በእኛም አገር ጤና ጥበቃ ያወጣው መመሪያ እንደሚያሳየው ማንም ሴት መረጃ ሳይሰጣት፣ የምክር አገልግሎት ሳታገኝ የወሊድ መቆጣጠሪያ መርጦ መጠቀም የለባትም:: በተለይም የወሊድ መቆጣጠሪያ የጐንዮሽ ጉዳቶች በሚገባ ለተጠቃሚው ሊገለፅ ይገባል:: ከፍተኛ የአገልግሎት ጫና፣ የሕክምና ባለሙያዎች እጥረት ባለበት ሁኔታ መመሪያው ምን ያህል ተግባራዊ ይሆናል? ምን ያህል ሴቶች በምን ያህል ደረጃ ገለጻ ተደርጐላቸው ይወስናሉ? የሚሉና ሌሎችም ጥያቄዎች ይነሳሳሉ:: መመሪያው ተግባራዊ በማይሆንበት አጋጣሚ በቂ ግንዛቤ ባለመጨበጥ የወሊድ መቆጣጠሪያ የሚያቋርጡ፤ ለመቆጣጠሪያዎቹ የጐንዮሽ ጉዳት እንግዳ የሚሆኑም እንደሚኖሩ ዶ/ር ሰሎሞን ይናገራሉ::

የኢትዮጵያ የሥነ ሕዝብና የጤና ጥናት እንደሚያሳየው ዕድሜአቸው ከ15 እስከ 49 ዓመት በሆኑ ሴቶች የወሊድ መቆጣጠሪያ ሥርጭት 20 በመቶ ነው:: ባለትዳር በሆኑ ሴቶች 29 በመቶ ሲሆን ባላገቡ ሴቶች 57 በመቶ ነው::

Page 63: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 15 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2ማስታወቂያ

AWASH INTERNATIONAL BANK s.c. INVITATION TO BID

Procurement Reference Number AIB 012/2012/13

1. Awash International Bank s.c. invites sealed bids from

eligible bidders for the supply and installation of the bank

logo on Awash Adama Building

2. Bidding will be conducted in accordance with the open

tendering procedures contained in the Directives of the Bank

and other Relevant Laws of the country, and is open to all

bidders from eligible source countries.

3. A complete set of bidding documents in English shall be

obtained from Procurement Division of Awash International

Bank S.c located at Awash Towers 10th floor upon payment

of non refundable fee Birr 100.00 /One Hundred Birr/ only

during office hours (Monday to Friday 8:00-12:00 AM;

1:00-4:30PM and Saturday 8:00-12:00AM) starting from

February 12, 2013. Presentation of copy of renewed Trade

license, VAT Registration Certificate, and TIN certificate

are a must.

4. Bid must be accompanied by a bid bond amount birr 50,000.00

(Fifty Thousand Birr) in the form of Bank guarantee or cash

payment order (CPO).

5. Bid document must be deposited in the bid box prepared for

this purpose on or before March 01 2013, 10:00 AM in the

above mentioned address.

6. Bid opening shall be held at the meeting hall of AIB s.c.

Awash Towers 12th floor in the presence of bidders and/

or their representatives who wish to attend on February 26,

2013, 10:30 AM.

7. Interested eligible bidders may obtain further information

from the office of Procurement and Warehouse Division tel.

0115-57-01-87 or 0115570084

8. Failure to comply with any of the conditions form No. 2 to 6

above shall result in automatic rejection.

9. The Bank reserves the right to accept or reject the bid either

partially or fully.

የስብሰባ ጥሪ 

የኢትዮጵያ ሜካኒካል ኢንጅነሮች ማኅበር አባላት በሙሉ

የኢትዮጵያ ሜካኒካል ኢንጅነሮች ማኅበር አሥራ ሰባተኛ ዓመታዊ ጉባዔውን የካቲት 10 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም. ከጠዋቱ 2፡3ዐ ጀምሮ በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ ሆቴል  የስብሰባ አዳራሽ ስለሚያካሂድ የማኀበሩ አባላት በሙሉ እንድትገኙ ጥሪውን በአክብሮት ያስተላልፋል፡፡ እንዲሁም እስካሁን የማኀበሩ አባል ያልሆናችሁ እና አባል ለመሆን የምትሹ እንድትመዘገቡ ማኀበሩ በዚሁ አጋጣሚ ጥሪውን ያቀርባል፡፡ 

የኢትዮጵያ ሜካኒካል ኢንጅነሮች ማኅበርEthiopian Society of Mechanical Engineers

ለበለጠ መረጃ፡- Ø ስ.ቁ. ዐ11 629 34 8ዐØ   ፖስታ ሣ.ቁ. 17626

Ø    ፋክስ፡- ዐ116 29 34 80

Ø    ኢ.ሜል  [email protected]

የኢትዮጵያ ሜካኒካል ኢንጅነሮች ማኅበር

አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማየተሽከርካሪ ጥገና ጨረታ ቁጥር AIB 013/2012/13

አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ. የባንኩን ተሽከርካሪዎች ሰርቪስ ለማስደረግና ለማስጠገን ብቁ የሆኑ ጋራዦችን በጨረታ አወዳድሮ ለ12 ወራት በኮንትራት ማሰራት ይፈልጋል፡፡ በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ሁሉ

1. በመስኩ የታደሰ የንግድ ፍቃድ እና ተጨማሪ እሴት ታክስ መመዝገባቸውን የሚገልፅ ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡

2. ተጫራÓች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000.00 (አስር ሺ) በሲፒኦ ወይም ቅድመ ሁኔታን ባላስቀመጠ ባንክ ጋራንቲ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

3. ተጫራÓች የጨረታ ሰነዱን ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት የስራ ቀናት ከሰኞ - አርብ ከ 2፡00-6፡00 ሰዓት እና 7፡00-10፡30 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ 2፡00-6፡00 ሰዓት አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ ዋና መስሪያ ቤት ግዥና ስቶር ዋና ክፍል አዋሽ ታወርስ 10ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 10-02 የካቲት 6 ቀን 2005 ጀምሮ የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡

4. ተጫራÓች የሚያስገቧቸውን ሠነዶች በሰም በታሸገ ኤንቨሎኘ እስከ የካቲት 26 ቀን 2005 ዓ.ም ከቀኑ 4፡00 ሰዓት ድረስ ከላይ በተራ ቁጥር 3 በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡

5. ጨረታው የካቲት 26 ቀን 2005 ዓ.ም ከቀኑ 4፡30 ሰዓት ተጫራÓች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዋሽ ታወርስ 12ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የባንኩ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡

6. ከላይ ከተራ ቁጥር 1-4 ያሉትን መስፈርት ያላሟሉ ተጫራÓች ከጨረታው ውጪ ይሆናሉ፡፡

7. ባንኩ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0115-570187 ወይም 0115-570084 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

Page 64: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 16 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

ማስታወቂያ

አድራሻ፡-ቦሌ ክ/ከ፣ ቀበሌ 14/15፣ ስዩም የዐይን ክሊኒክ ፊት ለፊት ሕብረት ባንክ የረር በር ቅርንጫፍ በሚገኝበት ሀዌተን ሕንጻ ሁለተኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0116-515215 ይደውሉልን፤

የሾላ አክስዮን ማህበር (ሪል እስቴት) ዘመናዊ የአፓርትመንት መኖሪያ ቤቶችShola Share Company /Real Estate /Modern Apartment Buildings

ሪል እስቴታችን ከዚህ በፊት እንደሚታወቀው 123 G+1 የሆኑ ዘመናዊ ቤቶችን በአጭር ጊዜ ገንብቶ በማስረከብ ተአማኒ፣ ተወዳዳሪና ተፈላጊ ሪል እስቴት ለመሆን የበቃ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ደግሞ እጅግ ዘመናዊ የሆኑ ስፋታቸው 175፣ 202፣ 204 እና 206 ካሬ ሜትር የሆኑ የአፓርትመንት መኖሪያ ቤቶችን፣ ውበቱና መሰረተ ልማቱ በበቂ ሁኔታ በተሟላለት አካባቢ ተመጣጣኝ በሆነ ዋጋ በመገንባትና በመሸጥ ላይ ይገኛል፡፡

የዘመናዊ አፓርትመንቶቹ መንደር ልዩ ገጽታዎች• ለብቻው የተዘጋጀ የመኪና ማጠቢያ ቦታ• የእንሰሳት ዕርድ መፈጸሚያ ቦታ• መጠለያ የተዘጋጀለት መኪና ማቆሚያ• የእሳት ማጥፊያና መከላከያ• የራሱ የውሃ አቅርቦት አማራጭ ከጉድጓድ የተዘጋጀለት • በቂ አረንጓዴ ማረፊያ ቦታ

Unique feature of the site• Car wash room• Common slaughter house• Shaded parking• Fire hydrant• Alternative water supply from bore hall• Spacious green and seating places

የዘመናዊ አፓርትመንቶቻችን መለያዎች• በየህንፃው ላይ ያሉት መኖሪያ ቤቶች አንደኛው ከሌላው መኖሪያ ቤት ጋር ግርግዳ

አይጋሩም• ፈጣንና ዘመናዊ ሊፍት የተገጠመላቸው• የእሳትና የደህንነት መከላከያ• ለእያንዳንዱ መኖሪያ ቤት ከምድር ቤት ሥር የዕቃ ማስቀመጫ የተዘጋጀላቸው • እያንዳንዱ መኖሪያ ቤት ለማጠቢያና ለተለያዩ ሥራዎች የሚሆኑ ተጨማሪ ሰፋፊ

ክፍሎች በምድር ቤት የተዘጋጀለት• በያንዳንዱ ህንጻ ላይ ለልብስ ማስጫና ለሳተላይት ማስቀመጫ የሚሆኑ የጣሪያ

በረንዳ ያለው • እያንዳንዱ መኖሪያ ቤት የሠራተኛ እና የልብስ ማጠቢያ ክፍል ያለው

Unique features of the Apartments • No wall sharing between units• Latest and Fast Elevator• Fire and security protection• Private Stores at basement• Shared laundry and local activity space at basement• Shared laundry and local activity space at basement• Roof terrace for satellite dishes & cloth drying • Maid’s room and laundry in each unit

206/204

5 መኝታ ቤት (Bed Room)

4 መኝታ ቤት (Bed Room)

202/1754 መታጠቢያ ቤት (Bath Room) 3 መታጠቢያ ቤት የቀሩት ቤቶች በጣም ውስጥ በመሆናቸው ዕድሉ እንዳያመልጥዎት ዛሬውኑ ቢሮአችን ብቅ ብለው ይስተናገዱ፡፡

Page 65: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 17 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2ማስታወቂያ

Page 66: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 18 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

ማስታወቂያ

›”ud ›=”g<^”e Ÿ<v”Á (›.T.)LION INSURANCE COMPANY (S.C.)

የጨረታ ማስታወቂያ

አንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ.) በግጭትና በመገልበጥ አደጋ ጉዳት የደረሰባቸውን

የተለያዩ አይነት ከባድና ቀላል ተሽከርካሪዎችን እንዲሁም የተለያዩ ንብረቶችን

/የተለወጡ አሮጌ የተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕnዎችን/ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ

ይፈMጋል፡፡

1. የመኪኖቹን/የንብረቶቹን ሁኔታ ማየት የሚðልጉ ተጫራቾች በአንበሳ ኢንሹራንስ

ኩባንያ ጉዳት የደረሰባቸው ተሽከርካሪዎች ማቆያ ቦታ (አቃቂ ድልድይ 100ሜ.

ወደ ደብረዘይት አቅጣጫ አለፍ ብሎ uስተቀኝ በኩል) በስራ ሰዓት በSገኘት እስከ

የካቲት 12 ቀን 2005 ዓ.ም. ድረስ ማየት ይችLሉ፡፡

2. ስለአሻሻጡ የተዘጋጀውንና የተሽከርካሪዎቹን ዝርዝር የያዘውን ፎርም አክሱም

ሆቴል ጎን ኮሜት ሕንፃ በሚገኘው የአንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ ዋና መ/ቤት ካሣ

መምሪያ ሁለተኛ ፎቅ የካቲት 4 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ መውሰድ ይችLሉ፡፡

3. ተጫራቾች መግዛት የሚፈልጉትን የእያንዳንዱን ተሽከርካሪ/ንብረት ዋጋ በሰም

በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ የካቲት 15 ቀን 2005 ¯.ም. ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ

ኮሜት ሕንፃ በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መ/ቤት ካሣ መምሪያ ለዚሁ በተዘጋጀ

ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባ†ዋል፡፡

4. ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ተሽከርካሪ/ንብረት የመነሻ ዋጋ ብር 20% (ሃያ

በመቶ) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (CPO) ማስያዝ ይኖርባቸªል፡

፡ በጨረታው yተሸነፉ tጫራቾች በማeያዣነት ያስያዙት ገንዘብ ወዲÁውኑ

ተመላሽ ይደረግ§cዋል፡፡

5. Úረታው yካቲT 16 ቀን 2005 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ኮሜት ህንፃ

በሚገኘው በኩባንያው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ

ወኪሎቻቸው እና ታዛቢዎች በተገኙበት ይከðታል፡፡

6. ተጫራቾች በጨረታ ያሸነፉትን ተሽከርካሪ ወይም ንብረት ሙሉ ክፍያ በ5 ቀናት

ውስጥ መክፈል ይኖርባቸዋል፡፡ ክፍያውን ከፈጸሙ በኊላ በ10 ቀናት ንብረቶቹን

ካላነሱ ለሀያ ቀናት በየቀኑ ብር 30.00 /ሰላú ብር/ የማቆሚያ ቦታ ኪ^ይ

የምናስከፍል ሲሆን በእነዚህ ቀናት ውስጥ ከፍለው ካላነሱ ግን ያስያዙት ገንዘብ

በቅጣት መልክ ለኩባንያው ገቢ ሆኖ አሸናፊነታቸው ይሰ[ዛል፡፡

7. ለጨረታ በቀረቡት ተሽከርካሪዎችና ንብረቶች ላይ የሚፈለግ ¥ንኛውም ዓይነት

የስም ማዛወሪያ፣ እና ልዩ ልዩ ወጪዎች ቢኖሩ yጨረታው አሸናፊ ይከFላል፡፡

8. Kተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0116-616741 ወይም 0116−187000/6632947

በመደወል ወይም በተራ ቁጥር 3 በተጠቀሰው አድራሻ በግንባር ቀርቦ መጠየቅ

ይ‰ላል፡፡

9. መስሪያ ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ’ው፡፡

10. Lሌሎች tጫራቾች ባቀረቡት ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ ክልክል ነው፡፡

11. ኩባንያው የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገdድም፡፡

አንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ (›.T)

የሸቀጥ አቅራቢዎች ምዝገባ ማስታወቂያ

ጅንአድ መሠረታዊ ሸቀጦችን በመግዛት በአገሪቱ ውስጥ በሚገኙ 83 የድርጅቱ የሽያጭ ቅርንጫፎች ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ የሚያቀርብ መንግስታዊ ድርጅት ነው፡፡ ድርጅቱ የተለያዩ ሸቀጦችን ከአምራቾችና አከፋፋዮች መግዛት እንዲችል በቅድሚያ የአምራቾችና አከፋፋዮች ዝርዝር በቋሚነት መያዝ ይፈልጋል፡፡

ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ሸቀጦች /አንድ ወይም ሁለትና ከዚያም በላይ/ ለማቅረብ ፈቃደኛ የሆኑ አምራቾች ወይም አከፋፋዮች ስለድርጅታቸው አቅምና ሌሎች ተያያዥነት ያላቸውን መረጃዎች እስከ የካቲት 20 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ እንዲያቀርቡ ተጋብዘዋል፡፡

ድርጅታችን የሚፈልጋቸው የሸቀጦች ዝርዝር፡-

ሀ/ የህንፃ መሣሪያዎች ሐ/ ጠቅላላ ሸቀጣ ሸቀጥ

1. የውሃ ቧንቧ 16. የልብስ ሳሙናና ዲተርጀንት 2. የአርማታ ብረት 17. የዱቄትና ፈሳሽ ሣሙና3. የኤሌክትሪክ ገመድ 18. የገላ ሳሙና4. ኮንዲዩት 19. ክብሪት5. አልሙኒየም /ላሜራ/ 20. በረኪና6. ኘላስቲክ ቱቦና መገጣጠሚያ 21. የፎም ትራስና ፍራሽ7. ኤሌክትሮድ መ/ ወረቀትና የጽ/መሣሪያዎች8. ምስማር 22. የፎቶ ኮፒ ወረቀት9. ከብረት የተሰሩ ቱቦዎች 23. የህትመት ወረቀቶች10. ሽቦና የሽቦ ውጤቶች 24. የአርት ወረቀት11. የቤት ክዳን ቆርቆሮ 25. የልባስ ወረቀት12. ሌሎች የህንፃ መሳሪያዎች 26. ቦክስ ፋይል

ለ/ የምግብ ሸቀጦች 27. ካርቦን13. ሻይ ቅጠል 28. የመፀዳጃ ቤት ወረቀት እና14. የምግብ ዘይት 29. ደብተር ናቸው፡፡15. ፖስታና ማካሮኒ

ከአቅራቢዎች የሚፈለጉ መረጃዎች፡-

1. የድርጅቱ አድራሻ፣2. የድርጅቱ ድረ ገጽ (ዌብ ሣይትና) ኢ-ሜይል፣3. የድርጅቱ ሥም፣ Contact person እና ስልክ ቁጥር፣4. ድርጅቱ የተሰማራበት የምርትና አገልግሎት ዓይነት፣5. የድርጅቱ አጠቃላይ መግለጫ፡- የማምረት አቅም፣ የቅርንጫፎች ብዛት፣ የሠራተኞች ብዛት፣ ካፒታል6. የተጨማሪ ታክስና የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሠርተፍኬት ኮፒ 7. የታደሰ የንግድ ፈቃድ ኮፒ ናቸው፡፡

አምራቾችና አከፋፋዮች ከላይ የተመለከቱትን መረጃዎች በድርጅታችን ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1897 መላክ ወይም በድርጅታችን ግዥ መምሪያ የሀገር ውስጥ ግዥ ዋና ክፍል ድረስ በግንባር ማቅረብ ይቻላል፡፡

ተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 011 155 07 00/ 011 111 4683/ 011 111 1930 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡

የሸቀጦች ጅምላ ንግድና አስመጪ ድርጅት ዌብ ሳይት www.mewit.com.et.

Page 67: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 19 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2ማስታወቂያ

A Call for Consultants to Undertake

Terminal Evaluation of 2011-12 Drought Emergency Response Carried out by Christian Children’s Fund of Canada- Ethiopia in Oromia region-Arsi Negelle woreda and SNNP region-Soddo Zuria woreda specific Kebeles

Christian Children’s Fund of Canada (CCFC) is non-profit, child-centered international development organization working in different regions of Ethiopia to improve the quality of life for children and youth through enhanced family and community capacity for sustainable development.

CCFC started its operation in Ethiopia in 1987 and has been implementing development projects mainly focusing on Education, Health and Nutrition, Water, Sanitation and Hygiene, Sustainable Livelihood Development, Strengthening Institutional and Community Organizations and Emergency responses in Oromia Regional State, Southern Nations, Nationalities and Peoples’ Regional State (SNNPRS), and Addis Ababa City Administration in partnership with 7 local NGO partners which are directly implementing the programs.

Goals of Evaluation: The evaluation is carried out to critically identify the successes and failures of the drought emergency operations; and provide recommendations including the lessons learned. This should contribute to improve future handling of emergencies through policy/strategy changes.

Major Tasks of the Evaluation: The consultant will prepare a work plan, apply evaluation methodology to obtain raw quantitative and qualitative data, conduct data entry and analysis on the raw quantitative and qualitative data p reports on the analysis.

Minimum Requirements of Applicants: The Consultant should have sufficient experience and proven track record in implementing quantitative surveys for evaluation purposes, implementing qualitative tools for evaluation purposes and analyzing both quantitative and qualitative data for evaluation purposes. The Consultant should also have proficiency at providing high-quality analysis and reports in a timely fashion. The Consultant is expected to have a trained and experienced team of professionals skilled in survey techniques, data entry and analysis and focus group leadership. This team should speak any local languages required to communicate with evaluation participants, and be able to complete the evaluation in the designated timeframe.

Interested consultants who meet the requirements are invited to submit detail technical and financial proposals to Christian Children’s Fund of Canada- Ethiopia Country Office.

The detailed TOR is available at the country office indicated in the address below, and the proposals should be submitted in hard and soft copies to the office 10 days from the appearance of this announcement.

Address:Christian Children’s Fund of CanadaEthiopia Country OfficeP.O. Box 9123Bole Sub City Kebele 05 House No. 638Tel: + 251 116 627534/35 Fax: + 251 116 61 05 [email protected]

www.ccfcanada.ca

›”ud ›=”g<^”e Ÿ<v”Á (›.T.)LION INSURANCE COMPANY (S.C.)

INVITATION FOR BID(CONSULTANCY SERVICE)REF. NO. LIC/IT/001/13

Lion Insurance Company (S.co), Invite interested and eligible local bidders (Consultancy service provider) for the provision of consultancy service during the process of acquiring and implementation of full-fledged Integrated Insurance and Financial Management Application Software and hardware.1. Interested and eligible consultants may obtain the completed bid documents during the working hours up on payment of non returnable 100 birr from the Information Technology Service of the Company located at:

Haile G/Selassie Avenu

Comet Bldg, 2nd floor Room No. 209

Addis Ababa, Ethiopia,

P.O.Box 26281/1000,Telephone: +251-11-618-7000, +251-11-

6188800.

Fax +251-11-6632940

Email: [email protected], [email protected].

2. The bid must be accompanied by a bid security equivalent to 2% of the total fixed value offered in the form of cash, CPO, Bank or Insurance guarantee.

3. The bid shall be closed on March 01, 2013 at 3:00 PM and opened in the presence of bidders or their representative on the same date at 3:30 PM at the Company’s board room. Bid presented by any bidder after the closing date and time shall not accepted.

4. Sealed bids marked as “Tender for the consultancy service” Original and Copy in separate three sealed envelopes marked General Proposal, Technical Proposal and Financial Proposal sealed in one big envelop must be submitted to the address specified above in the box prepared for this purpose on or before March 01,2013 3:00 PM

5. LIC Reserve the right to accept or reject all or parts of this bid.

Page 68: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 20 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

በምሕረት ሞገስ

ውልደቱና ዕድገቱ አራት ኪሎ አካባቢ ነው:: እ.ኤ.አ በ1999 ከቤተሰቡ ጋር ወደ አሜሪካ የሄደው የ26 ዓመቱ ሔኖክ ዐቢይ፤ ሔኖክ አራዳ በመባልም ይታወቃል:: ሔኖክ አራዳ የሚለውን ቅፅል ስም ያሰጠው ደግሞ በሚኖርበት አሜሪካ የኢትዮጵያን ባህል ያልለቀቁ የባህል ልብስ ዲዛይኖችን ከምዕራባውያኑ ዲዛይን ጋር በማዋሐድ፤ የአገሩን ባህል ስላስተዋወቀና ሥራውንም ለገበያ ስላዋለ ነው::

ታዲያስ መጽሔት እንደዘገበው፣ ዲዛይነር ሔኖክ የ‹‹አራዳ ፋሽን›› ሥራውን የጀመረው በ2001 ሲሆን ዓላማውም በአሜሪካ በሚገኙ ኢትዮጵያውያንና በሌሎች ዜጎች ዘንድ ፍላጎቱ እየጨመረ የመጣውን የኢትዮጵያን ባህላዊ ልብስ ፍላጎት መድረስ ነው:: ዲዛይኑን ከምዕራባውያኑ ዲዛይን ጋር በማጣመር የገበያውን ፍላጎት መሙላትና የአገሩን ባህል ማስተዋወቅም እንዲሁ::

በቲሸርቶች ላይ ‹‹አይ አም አራዳ›› (እኔ አራዳ ነኝ) የሚል ጽሑፍና የኢትዮጵያ ስሪት የሆነውን መስቀል በመቅረጽ ሥራውን በስፋት ያስተዋወቀው ሔኖክ አራዳ በተለይ የአፍሪካን ዳያስፖራ ዓላማ ባደረጉ ዲዛይኖቹ ታዋቂነትን አትርፏል:: ለወጣት ሴቶች የሚስማሙና ኢትዮጵያዊ ዲዛይኖችን ሳይለቁ በምዕራባውያኑ ስታይል በሚሠራቸው አጫጭር ቀሚሶችም ይታወቃል::

በዌስትቸስተር ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መማሩ በዲዛይን፣ በፋሽንና በቪዲዮ ኮሚዩኒኬሽን ዘርፍ እንዲቀጥል ፍላጎት እንዳሳደረበት የሚናገረው ሔኖክ፣ ፍላጎቱን እውን አድርጎ የዲዛይን ሥራዎቹን ከአልባሳት አልፎ ቦርሳዎች ላይም አስፋፍቷል::

ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በያሉበት ሆነው የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ እንዲገነቡና አገራቸውን እንዲያስተዋውቁ በአገራቸው ልማትም ተሳታፊ እንዲሆኑ መንግሥት የተቀናጀ ጥረት የጀመረው ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ነው:: ሔኖክ አራዳ ደግሞ የታዳጊ ወጣትነት ዕድሜው ሳይገድበው በሥራው አማካይነት የኢትዮጵያን የባህል ልብስ፣ ዲዛይንና አገሩን ማስተዋወቅ የጀመረው አሜሪካ በገባ በሁለት ዓመቱ ነው::

በ2002 የኢትዮጵያን የባህል ልብስ ከምዕራባውያኑ ጋር በማቀናጀት በሎስአንጀለስ ባደረገው የመጀመሪያው ፋሽን ሾው ከተመልካቹ ጥሩ አቀባበልን ያገኘ ሲሆን ከዚህ በኋላም ‹‹ሜድ ኢን አራዳ›› ሥራዎቹን በዋሽንግተን፣ በችካጎ፣ በፎኒክስ፣ በአትላንታ እንዲሁም በዳላስ አሳይቷል:: በመጪው ሐምሌ በሚካሄደው የኢትዮጵያውያን የእግር ኳስ ውድድር ላይም አዳዲስ ዲዛይኖችን አካቶ ፋሽን ሾው ለማሳየት እየተዘጋጀ ነው::

ዳ ያ ስ ፖ ራ

የ‹‹አራዳ ፋሽን›› ጥበበኛ

በአሜሪካና በአዲስ አበባ የራሱን ድርጅት ለመክፈት ዕቅድ ያለው ሔኖክ ‹‹ባህላችንን በዘመናዊ አሠራር ቃኝቼ ተጠቃሚው ከዚህ በፊት አይቶት የማያውቀውን ዓይነት ጥበብ ማሳየት እፈልጋለሁ፤›› ብሏል:: የዕርዳታ ድርጅቶችንና አብያተ ክርስቲያናትን መርዳት ደግሞ ዓላማው ነው::

ሔኖክ ከንግዱም ባለፈ የአገሩን ባህል በማስተዋወቅና መልካም ገጽታን በመገንባት እያደረገ ያለውን አስተዋጽኦ የኢትዮጵያ የዳያስፖራ ፖሊስም የሚደግፈው ነው::

በርካታ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት ሙዓለ ንዋያቸውን አገር ውስጥ በማፍሰስ፣ ዕውቀትና ቴክኖሎጂን

በማሸጋገር፣ የውጭ ምንዛሪ አገር ውስጥ በመላክ፣ ንግድና ቱሪዝምን በማስፋፋት የአገራቸውን ገጽታ በመገንባት ረገድ ተጨባጭ ውጤቶችን እያስመዘገቡ ነው:: በጎ ጅምሮችን በማጎልበት ዳያስፖራውን በአገሩ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እንቅስቃሴዎች በማሳተፍ ራሱንና አገሩን ተጠቃሚ ማድረግ የሚችልበት የዳያስፖራ ፖሊሲም ተቀርጿል:: ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በአገራቸው አጠቃላይ ልማት ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማስቻል በተረቀቀው የዳያስፖራ ፖሊሲም ባህላዊ እሴቶችን ማዳበርና ገጽታ ግንባታን ማትጋት አንዱ ነው::

የዳያስፖራው አባላት በሚኖሩባቸው አካባቢዎች

ለሚያዘጋጃቸው የባህል ነክና የኪነት ትርዒቶች እንዲሁም

የስፖርት በዓላት አስፈላጊውን ማበረታቻ እንዲያገኙም

ፖሊሲው ይደግፋል::

ፖሊሲው ለወጣት ዳያስፖራዎች የተደራጀ ተሳትፎም

ልዩ ትኩረት ይሰጣል:: በውጭ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን

ስብስቦች ጋር በመተባበር በአገር ውስጥና በውጭ አገር ያሉ

ወጣቶች ሐሳባቸውን የሚለዋውጡበት ወጣቶችን ማዕከል

ያደረገ የኢትዮጵያን የባህል፣ የሥነ ጽሑፍ የኪነ ጥበብና

የስፖርት ዝግጅቶችንም ያበረታታል::

ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም

ባ ህ ል

በአያሌው ወረታ

በሽሮሜዳና አካባቢዋ በአብዛኛ)ዋቹ ቀደምት ነዋሪዎችና የዕድሜ ባለፀጐች አንደበት ሸማ (የአገር ባህል ልብስ) ለሰፈሩ መታወቅ ቀዳሚ ምክንያት ነው:: ሽሮሜዳ ቀስ እያለችም ቢሆን በጥበብ ኩታ መደብሮች የመሟሟቅ ምልክት ይታይባታል:: ጥቂት ስለአንዷ የጥበብ ኩታ መንደር

ከስድስት ኪሎ ወደ እንጦጦ ተራራ በሚወስደው መንገድ ሽሮሜዳን አለፍ ብሎ እንጦጦ አምባ ትምህርት ቤት ይደረሳል:: የትምህርት ቤቱ የፊት ለፊት አጥር መዳረሻ ላይ በግራ በኩል የሚገኘው ቁልቁለት ማብቂያ አንዷ የጥበብ ኩታ መንደር ደቡባዊ ድንበር መነሻ ነው:: ይህች ሽሮሜዳን በአገር ባህል ልብሶች (ጥበብ ኩታ፣ ነጠላ፣ ቀሚስ፣ ጋቢ፣ ብሉኮ ወዘተ) በመሳሰሉ ድንቅ የቤት ውስጥ የሽመና ውጤቶች እንድትጠራ ዋና ምንጭ ከሆኑት

መንደሮች አንዷና አሮጌዋ በያኔ ስሟ ደጃች መታፈሪያ፣ እስከቅርብ ጊዜ 23 ቀበሌ ዛሬ ደግሞ 18 ቀበሌ በመባል ትጠራለች::

አለቃ ማዳ ከዛሬ 40 ዓመታት በፊት በዚች ቀበሌ ከሰፈሩ ነዋሪዎች መካከል ይገኙበታል:: (አለቃ በጋሞ ብሔረሰብ ሹመት ነው):: አለቃ እንደሚያስታውሱት ‹‹በወቅቱ የእኔን ጨምሮ ራቅ ራቅ ብለው የተሠሩና ጥቂቶቹ በእርጥብ ባሕር ዛፍ ቅጠል የታጠሩ ቤቶች ነበሩ:: ከነዚህ መካከል አምስት የሚሆኑት በወቅቱ ክብር ዘበኞች፣ ጦር ሠራዊትና የአካባቢውን የመሬት ባለቤት ጨምሮ ሦስት አራት የሚሆኑ ሲቪል የመንግሥት ሠራተኞች ቤቶች ሲሆኑ፣ የተቀሩትና አብዛኛዎቹ ቤቶች እንደኔው በሽመና ሙያ የተሰማሩ ጋሞዎች የሠሯቸው ቤቶች ናቸው::››

ቀበሌዋ በምሥራቅ ከቀጨኔ፣ በምዕራብ ከሽሮሜዳ ገበያና በሰሜን ከፊሉን የእንጦጦ ጋር ሥር ትዋሰናለች:: አንዳንድ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት የነዋሪው ቁጥር ከ40

እስከ 45 ሺሕ ይደርሳል::በቀበሌው 1,734 ሕጋዊና 223 የጨረቃ ቤቶች ይገኛሉ:: ከነዚህ መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት እርስ በእርሳቸው ተያይዘው ከጭቃና ከባሕር ዛፍ እንጨት እንደነገሩ የተሠሩ የቆርቆሮ ክዳን ቤቶች ናቸው:: መረጃውን መነሻ በማድረግ በቀበሌው በአንድ ቤት በአማካይ 24 ሰው እንደሚኖር ማስላት ይቻላል:: ከነዚህ ቤቶች ስንቶቹ የመፀዳጃ ቤትና መታጠቢያ እንዳላቸው መጠየቅ ቅንጦት ይሆናል:: በቀበሌው ምንም የመንግሥት ጤና ጣቢያ ወይም ክሊኒክ የለም:: አንድ ከ1ኛ-4ኛ ክፍልና አንድ የመዋለ ሕፃናት በመንግሥት ተከፍተው አገልግሎት ይሰጣሉ::

አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የቀበሌው ጽሕፈት ቤት ሠራተኛ እንደሚናገሩት በቀበሌው የሕዝብ ቁጥር ዕድገት እጅግ ፈጣን ብቻ አይደለም:: በእርሳቸው አገላለጽ ‹‹እጅግ የሚፈላ ነው፤›› ለዚህ እንደምክንያት የሚያነሱት የአብዛኛው የቀበሌው ነዋሪ ባህል የሚፈቅደውን ከአንድ

‹‹ኢስታ ናማ›› - አንድ ሁለት

Page 69: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 21 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2

ማ ህ በ ራ ዊ

በታደሰ ገብረማርያም

የወንዙ ውኃ የተፈጥሮ ቀለሙን ቀይሮ የቀለጠ ሬንጅ ወይም የተቃጠለ የሞተር ዘይት ይመስላል:: አለፍ አለፍ ብሎም የወየበ አረፋ ደፍቆ ይታያል:: ከስፍራው የሚፈሰው መጥፎ ጠረን አፍንጫን ይሰነፍጣል:: የቤት ጥራጊ፣ የተለያዩ ደረቅ ቆሻሻዎች፤ ፌስታሎችና የፕላስቲክ ጠርሙሶች፣ የሞተ ዶሮና ድመት የጨርቅና የወረቀት ቅዳጆች በወንዙ ላይ ተጥለው ይታያሉ:: የወንዙ ግራና ቀኝ ዳርቻዎች በሸንበቆ ተክል ተከበዋል:: በስተቀኝ በኩል ያለውን የወንዙን ዳርቻ ተከትሎ ቆስጣ፣ የሐበሻና የፈረንጅ ጎመን፣ ሠላጣና የመሳሰሉት አትክልት ለምተዋል:: ልማቱ አካባቢውን አረንጓዴ በማድረጉ የተነሳ ዓይንን ይማርካል:: ወደ አትክልቱ የሚያቀኑት ቦዮች ግን በሚያስተላልፉት ውኃ መጥቆር ሳቢያ ጥላሸት መስለዋል:: ወንዙ ከ40 ዓመት በፊት ለልማት ብቻ ሳይሆን ለመጠጥም ይውል ነበር::

ከወንዙ በተገኘው ውኃ በሚካሄደው በዚሁ የአትክልት ልማት ላይ በርካታ አምራቾች ልዩ ልዩ ዓይነት የእርሻ መሳሪያዎቻቸውን ይዘው ይኮተኩታሉ፣ የውኃ መተላለፊያ ቦዮችን ይንከባከባሉ፣ አራሙቻ ይነቅላሉ::

አዲስ አበባን አቋርጠው ከሚፈሱት ልዩ ልዩ ወንዞች መካከል አንዱና ትልቁ የአቃቂ ወንዝ ነው:: ከወጨጫ ተነስቶ በገፈርሳ አቅንቶ አዲስ አበባ ከገባና በሳሪስ በኩል አድርጎ ወደ ሃና ማርያም ከተሻገረ በኋላ ጉዞውን ቀጥሎ ከአባ ሳሙኤል ጋር ይቀላቀላል:: ከሁለት ሺሕ በላይ የሚጠጉ አባላትን ያቀፉ ዘጠኝ ማኅበራት ይህንኑ ወንዝ ተከትለው በመስኖ የአትክልት ልማት ሥራ ላይ ከተሰማሩ ውለው አድረዋል:: ከእነዚህም መካከል አንደኛው መካኒሳ ጎፋ ሣሪስ የአትክልት አምራቾች

የአዲስ አበባን አትክልት መጋቢው የተበከለ ወንዝ

ሚስት በላይ ጋብቻና ከገጠር ፍልሰትን ዋና ዋናዎቹ በማለት ነው:: እኚህ ሠራተኛ እንደሚሉት ዛሬ ዛሬ ወደዚህ ቀበሌ መልቀቂያ ይዘው በመምጣት የነዋሪነት ፈቃድ የሚጠይቁ ሰዎች ብዛት በቀን በአማካይ 11 ደርሷል:: ከነዚህ 85 በመቶ የሚሆኑት የሚመጡት ወጣቶችና ከጋሞጐፋ ዞኖች ሲሆን፣ የተቀሩት ደግሞ በአብዛኛው ከአማራና ከሌሎች ልዩ ልዩ የአገራችን ክልሎች ነው::

በቀበሌው ውስጥ የሚገኙ የችርቻሮ ሱቆች ሸቀጦችን እስከመጨረሻው ይቸረችሯቸዋል:: ምንነታቸው አይጥፋ እንጂ ተቆርጠው፣ ተሰንጥቀው ወይም ተቆንጥረው ይሸጣሉ:: የክብሪት እንጨት በቁጥር በአምስት ሳንቲም ሁለት ወይም ሦስት ይሸጣል:: ሳሙና ተቆራርጦ ይቸረቸራል:: የኩንታል ስኳር ዋጋ የቱንም ያህል ቢጨምር ግማሽ ማንኪያም ቢሆን በጥቂት ሳንቲም ደረጃ ይገኛል:: ሌላም ሌላም::

ቀበሌውን ለሁለት ከፍሎ የሚያልፈው ዋናው መንገድ በስተሰሜን ጫፍ ቁስቋም ቤተ ክርስቲያን ሲደርስ ወደ እንጦጦ ተራራ ከሚወስደው መንገድ ጋር ይገናኛል:: ይህ መንገድ መጀመርያ ከተዘጋበት ከንጉሡ ጊዜ ጀምሮ ከመጠነኛ ጥገና በስተቀር አንዳችም ማሻሻያ አልተደረገለትም:: ከመጐዳቱ የተነሳ በመኪና መጓዝ የሚቻለው ግማሽ ድረስ ብቻ ነው:: አብዛኛዎቹ የውስጥ ለውስጥ መንገዶችም ቢሆኑ በተለምዶ የኬር ድንጋይ ተብሎ የሚጠራውን እንኳን አላገኙም:: በመንገዶቹ የተንጠለጠሉት አምፖሎች መጠን በምሽት ለመጓዝ አያደፋፍሩም:: ሽመና በሽሮሜዳና አካባቢው

ባህላዊው የቤት ውስጥ ሽመና በአገራችን በአንድና ሁለት ብሔረሰቦች ብቻ የሚከናወን ሙያ አይደለም:: ይህንን ለማረጋገጥ በሽሮሜዳና አጐራባች ሰፈር ቀጨኔ አካባቢ ከጋሞ ብሔረሰብ በተጨማሪ የአማራና ኦሮሞ ብሔረሰብ አባላት በሽመና ሙያ ተሰማርተው መመልከቱ በቂ ይሆናል:: ይሁን እንጂ የየብሔረሰቡ ባህልና ልማድ የፈጠረው ይመስላል:: አንድ ብሔረሰብ በተወሰነ የሸማ መስክ ላይ ብቻ የማተኮር ዝንባሌ ይታያል:: ለምሳሌ በጋሞ ብሔረሰብ ሸማኔዎች በጥበብ ያጌጡ ነጠላና ቀሚሶችን ማምረት ይዘወተራል:: ከብሔረሰቡ አንድ አዛውንት በጋሞ ጐፋ ሽመና የተጀመረው ከ150 ዓመታት ገደማ በፊት በየሰፈሩ በሚገኙ ሜዳዎች በመሰባሰብ ለግል ፍጆታቸው የሚውሉ የሸማ አልባሳትን በማምረት እንደሆነ ይናገራሉ:: በወቅቱ በዚህ መልኩ ይዘጋጁ ከነበሩ የባህል ልብሶች መካከል ጋቢ፣ ብልኮ፣ ቀሚስ፣ ከወገብ በላይ የሚለበስ ጥብቆና እስከ ጉልበት የሚሸፍን ቁምጣ ይገኙበታል::

ዛሬ የኢትዮጵያ የባህል ልብስ በመሆን በመላው ዓለም እያስተዋወቀን የሚገኘው በተለይ በልዩ ልዩ ጥበብ አጊጦ የሚዘጋጀው ነጠላና ቀሚስ በሽሮሜዳና አካባቢዋ በስፋት ይመረታል::

‹‹ኢስታ ናማ እልሻለሁእልሻለሁየጥበብ ኩታ አለብስሻለሁአንቺ ብትመጪ እኔ አልጐዳምግን ስትለዪኝ አዝናለሁ በጣም››እነዚህ በጋሞና አማርኛ የተቀላቀሉ የዜማ ስንኞች

ከሃያና ሠላሳ ዓመታት በፊት በአካባቢው ገችሌዎች (ልጆች) ከሚዜሙ የሕዝብ ዘፈኖች ከአንዱ የተቀነጨቡ ናቸው:: ስንኞቹ ካዘሉት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በተያያዘ የሽመና ሙያ በወቅቱ ምን ያህል የኩራት ምንጭ እንደነበር ይጠቁማሉ:: አለቃ ማዳ በወቅቱ ከሸማ ሥራ ከሚያገኙት ገቢ በሳምንት ሦስት የተለያዩ መጠን ያላቸው እቁቦችን ይጥሉ ነበር:: በየዓመቱም የመስቀል በዓል ሲደርስ ከእቁቦቻቸው መካከል ቢያንስ አንዱ እንዲወጣላቸው የነበራቸውን ጉጉት ያስታውሳሉ:: (ከነቤተሰቦቻቸው ወደ አርባ ምንጭ በመጓዝ በዓሉን ከዘመድ አዝማድ ጋር ለማሳለፍ) ይሁን እንጂ ዛሬ ሽመና ከእጅ ወደ አፍነቱም አጠራጣሪ እየሆነ እንደሚገኝ የአለቃ ሥጋት ነው:: የአገር ልብሶችን ገዥና ተጠቃሚ ቁጥሩ እየጨመረና በመላው ዓለም ተፈላጊ በሆነበት በአሁኑ ወቅት ይህ መከሰቱም አለቃን ያስገርማቸዋል::

ዱሻ ዱራሞ የአለቃ ጎረቤት ነው:: የሸማ ሥራውን ካቆመ

አራት ዓመቱ ነው:: በአንድ የሕንፃ ሥራ ድርጅት ውስጥ በቀን ሠራተኛነት ተቀጥሯል:: የልጆቹ እናት ከእንጦጦ ጫካ የማገዶ ቅጠል በመሸከም ኑሮአቸውን ትደግፋለች:: ዱሻ የሸማ ሥራን ‹‹አበረታች ጥቅም አጣሁበት›› ይላል:: በአሁኑ ገበያ ለአንድ ነጠላ የጥሬ ዕቃ መግዣ ቢያንስ 50 ብር ወጪ ይደረጋል:: አንድ ሸማኔ ሌት ከቀን ከሠራ በሳምንት አራት ነጠላ ይቆርጣል:: ጊዜውን ለሌሎች ጉዳዮች ያዋለ ወይም ሳይጨናነቅ የሠራ ሸማኔ ደግሞ ሁለት ነጠላ ያደርሳል:: ሸማኔ ለነጋዴ አንዱን ነጠላ በአማካይ 80 ብር ሲሸጥ ነጋዴ ለለባሽ 120 ብር ይሸጥለታል:: ሸማኔው ከአንድ ነጠላ 30 ብር ሲያገኝ ነጋዴው ደግሞ 40 ብር ያገኛል:: ‹‹ሸማኔውና ለባሹ ቢገናኙ ዓለም ነበር፤›› ይላል ዱሻ ከአንድ ነጠላ 70.00 ብር ትርፍ ሊገኝ እንደሚችል አስቦ:: የሽመና ጥቅም አበረታች እንዲሆን ብቸኛ መፍትሔ ባይሆንም ለባሹና ሸማኔው እንዲገበያዩ ገበያዎችን ማመቻቸትና ለባሹ ወይም ተጠቃሚው ከአምራቹ ጋር የመገበያየት ልምድ እንዲያዳብር ማስቻል መልካም ጐን እንዳለው ይስማማል:: ይሁን እንጂ ተጠቃሚው አንዲት ነጠላና ቀሚስ ከያዘ ሸማኔ ከመግዛት ይልቅ ከብዙ ነጠላና ቀሚሶች መካከል መርጦ መግዛትን ይመርጣል:: በተገዛው ልብስ ቅሬታ ቢፈጠር እንኳን ወደ መደብሩ በመመለስ መቀየር ወይም መመለስ ስለሚቻል ተጠቃሚው ከሸማኔ ከመግዛት ይልቅ መደብሮችን በደንበኛነት መያዝ የበለጠ

መተማመኛ አድርጐ ይወስደዋል በማለት ዱሻ አስተያየቱን ይገልጻል:: ባህላዊው ሽመና ምን ተሻለው?

በአዲስ አበባና አካባቢዋ ባህላዊውን ሽመና ከገቢ ምንጭነቱ አኳያ በሦስት ሁኔታዎች መክፈል ይችላል:: የመጀመርያዎቹና አብዛኛዎቹ ለግል የገቢ ምንጭነት በማኅበር ወይም በግል የሚሸምኑት ናቸው:: ሁለተኛዎቹና ጥቂት የማይባሉት ለወላጆቻቸው ወይም አሳዳጊዎቻቸው የሚሸምኑት ሲሆኑ፣ ሌሎች ሦስተኛዎቹ ደግሞ ለሌሎች ተቀጥረው የሚሸምኑ ናቸው:: በቀጣሪዎቻቸው ቤት እያደሩ ለቀጣሪዎቻቸው የሚያመርቱ ሸማኔዎች ቆጣሪዎች በመባል ይታወቃሉ:: ቆጣሪዎች ከአሠሪዎቻቸው የሚዋዋሉት በቃል ነው:: እንደ ሁለቱ ወገኖች የቃል ስምምነት ለጥሬ ዕቃ መግዣ የዋለው ተቀንሶ ትርፉን ቀጣሪና ቆጣሪ እኩል ይካፈላሉ:: ቆጣሪው በቀጣሪው ቤት የሚመገብ ከሆነ ከድርሻው ይቀነሳል:: ውኃና መብራት ግን በነፃ ይጠቀማል::

ከባህላዊው ሽመና ተገቢውን ጥቅም ማግኘት እንዲቻል በማኅበራት መደራጀት እንደመፍትሔ መታየት የተጀመረው ከንጉሡ ጊዜ ጀምሮ እንደነበር በወቅቱ አባል በነበሩ ሸማኔዎች ይነገራል:: በንጉሡም ሆነ በደርግ ሥርዓት ተቋቁመው የነበረ ማኅበራት አባሎቻቸውን በአግባቡ ጠቅመዋል ወይም አልጠቀሙም ለማለት ማሰረጃዎቹ አሻሚ ቢሆኑም በወቅቱ የማኅበራቱ ተመራጮች የአንበሳውን ድርሻ ያገኙ እንደነበር በእርግጠኝነት መጻፍ ይቻላል:: ዛሬም በሽሮሜዳና አካባቢዋ ተደራጅተው የሚያመርቱ የሸማኔዎች ማኅበራት ቁጥራቸው ትንሽ አይባልም:: አባላቱ እንደሚገልጹት የመንግሥት ልዩ ልዩ ድጋፍና ክትትል አልተለያቸውም:: የመሸጫ ማዕከላትም አሏቸው:: የገቢና ወጪ ቁጥጥር በሥርዓቱ ይካሄዳል:: ሆኖም አንዳንድ አስተያየት ሰጪ አባላት ኑሯችን ተለውጧል በማለት አፍ ሞልተን አንናገርም ይላሉ::

ግርማ ቡልቻ እውቅ ሸማኔና ጥበበኛ ነው:: ነጋዴዎችም ሆኑ ተጠቃሚዎች ሰው በሰው አፈላልገው ከሚያገኟቸው ምርጥ ሸማኔዎች መካከል እንደነበር ጎረቤቶቹም ይመሰክራሉ:: ግርማ ዛሬ በአንበሳ አውቶቡስ ጋራዥ የላባጆ (እጥበት) ሠራተኛ ሆኗል::

የሸማ ሥራ ምናልባት በትርፍ ጊዜ እንደተጨማሪ ገቢ ማስገኛ ካልሆነ በስተቀር ብቻውን የሚሰጠው ጥቅም ሸማኔውን ማኖር እንደማይችል ይናገራል:: ባህላዊው ሽመና ጊዜውን ተከትሎ በቴክኖሎጂ አልታገዘም እንጂ እንደምርቱ ተፈላጊነት ለአምራቹም ሆነ ለአገር ከፍተኛ ጥቅም ማስገኘት የሚችል ሙያ ይሆን ነበር የሚለው ግርማ፣ በዚህ ረገድ የተሠሩ ሥራዎች ደካማ እንደሆኑ አስተያየቱን

ወደ ክፍል 2 ገጽ 23 ዞሯል

ለአፍሪካ አገሮች ዛሬም ችግር

የሆነው የሴቶች ግርዛት

በጋዜጣው ሪፖርተር

የማዕከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ የ2011 ጥናት እንደሚያሳየው ዕድሜአቸው ከዜሮ እስከ 14 በሆኑ ሴቶች ብሔራዊ የግርዛት መጠን (ሬት) 23 በመቶ ነው:: ትልቅ የግርዛት ሬት የተመዘገበው በአፋር ሲሆን፣ 59.75 ሲሆን ትንሹ በቤንሻንጉል 7.36 በመቶ ነው::

የተባበሩት መንግሥታት የሕፃናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) እና የሥነ ሕዝብ ፈንድ (ዩኤንኤፍፒኤ) የሴቶች ግርዛትን ለማስቀረት ከሚንቀሳቀሱባቸው አሥራ ሰባት አገሮች መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ናት::

እነዚህ ድርጅቶች ሌሎችም የሴቶች ግርዛትን ለማስቀረት የሚንቀሳቀሱ አገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት ተግባሩን እንደ አንድ ጐጂ ልማዳዊ ድርጊት ብቻ ሳይሆን፣ ከሥነ ተዋልዶ ጤናና ከሰብዓዊ መብት አንፃርም ይመለከቱታል::

ረቡዕ ጥር 29 ቀን 2005 ዓ.ም. አስረኛው ዓለም አቀፍ የሴቶች ግርዛትን ያለመታገስ ቀን በአፍሪካ ታስቦ ውሏል:: የሴቶች ግርዛትን ለማስቀረት የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ተግባሩን የሚከለክሉ ሕጐች የወጡ ቢሆንም፣ የሴቶች ግርዛት አሁንም ትልቅ ችግር የሆነባቸው የአፍሪካ አገሮች አሉ:: የዓለም የጤና ድርጅት መረጃ እንደሚያመለክተው ዓለም ላይ ከ100 እስከ 140 ሚሊዮን የሚሆኑ ሴቶች ተገርዘዋል:: በየዓመቱ ደግሞ ከሦስት ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሴቶች በየዓመቱ ለግርዛት ይጋለጣሉ::

ወደ ክፍል 2 ገጽ 23 ዞሯል

ፎቶ በ

ሪፖርተ

ር/ታምራት ጌ

ታቸው

Page 70: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 22 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

ከ ታ ሪ ክ ጥ ግ

ኪ ን

በሔኖክ ያሬድ

በዓለም እጅግ ዝነኛ የሆነችው ሉሲ ቅሬተ አካል በአሜሪካ የነበራትን የአምስት ዓመታት ቆይታ አጠናቃ ወደ ኢትዮጵያ ከመመለሷ በፊት ለመጨረሻ ጊዜ በአሜሪካዋ ሳንታ አና ካሊፎርኒያ ከተማ እየተጎበኘች ነው:: ‹‹Lucy Legacy the hidden treasure of Ethiopia›› (የሉሲ ውርስ ድብቁ የኢትዮጵያ ቅርስ) በሚል መሪ ቃል በሳንታ አና የሚታየው ዐውደ ርዕይ እስከ ግንቦት 4 ቀን 2005 ዓ.ም. እንደሚቆይ አርት ሚዲያ ኤጀንሲ በድረ ገጹ ዘግቧል::

የሰው ዘር መነሻ፣ የታቦተ ጽዮን መገኛ እንደሆነች በሚነገርላት ኢትዮጵያ የተገኘችውና በአሜሪካ በእይታ ላይ የከራረመችው ሉሲ 3.2 ሚሊዮን ዓመታትን ማስቆጠሯ ዝነኛነቷን ያጎላው ሲሆን፣ ከተገኘች ሦስት አሠርታት በኋላም በሰው ዘር አመጣጥ ላይ ባለው ግንዛቤ ላይ ተጽዕኖዋ አሁንም እንደቀጠለ መሆኑ እየተነገረላት ነው::

‹‹ታሪካዊ ቅርሶች የአገርን ገጽታ በማስተዋወቅ በኩል ሰፊ ሚና ይጫወታሉ›› በሚል ኃይለ ቃል ስለሉሲ ጥር 29 ቀን መግለጫ ያወጣው ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሉሲን ለመጨረሻ ጊዜ ለማሳየት በተዘጋጀው ዐውደ ርዕይ ላይ ለመገኘት በሚኒስትር አሚን አብዱልቃድር የሚመራ የልዑካን ቡድን ወደ አሜሪካ ማቅናቱን አስታውቋል::

በዐውደ ርዕዩ ወቅት በኢትዮጵያ የሰው ዘር አመጣጥ ላይና ሉሲ የሁለቱን አገሮች የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት

በጋዜጣው ሪፖርተር

ታዋቂው ሩሲያዊ የአጭር ልቦለድ ደራሲና የሕክምና ባለሙያ አንቷን ቼኾቭ 153ኛ ልደት የካቲት 4 ቀን 2005 ዓ.ም. በ11 ሰዓት በፑሽኪን አዳራሽ ይከበራል::

የሩሲያ የሳይንስና የባህል ማዕከል ለሪፖርተር እንዳስታወቀው፣ በበዓሉ ከሩሲያ የመጡት የፒያኖና የኦፔራ ሙዚቀኞች ናታሊያና አሌክሴይ የሙዚቃ ኮንሰርት ያቀርባሉ:: በዓሉን በሩሲያ የባህል ሻይ ‹‹ሳሞቫር ሻይ›› እንደሚያጅበው ታውቋል::

‹‹ሥነ ጽሑፍ ውሽማዬ ስትሆን ሕክምና የሕግ ሚስቴ ናት›› በሚል አገላለጹ የሚታወቀው አንቷን ቼኾቭ ሥራዎቹ በኢትዮጵያውያን ደራስያን ተተርጉሞለታል::

በጋዜጣው ሪፖርተር

በናታን መልቲሚዲያ ፕሮዳክሽን የተቋቋመው ‹‹የተራኪ ዳንሰኛና ድራማ ክለብ›› ያዘጋጀው ‹‹ውቢት እንቅልፏማ›› የተሰኘው ድራማ በኤድና ሞል ሲኒማ የካቲት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. ለእይታ በቅቷል::

አዘጋጁ እንዳስታወቀው፣ ድራማው በብላቴን ጌታ ማኅተመ ሥላሴ ወልደ መስቀል ‹‹እንቅልፍ ለምኔ›› ከተሰኘው የተረት ስብስብ ውስጥ ‹‹ስለ አንድ ንጉሥ የዘመን ሁኔታ መጠየቅ›› ከተሰኘውና ወንድማማቾቹ ጀርመናውያን ፎክሎሪስቶች ጃኮብና ዊልሄልም ግሪም አጠናቅረው ካሳተሟቸው የተረቶች (ፌሪቴሎች) ስብስብ

‹‹ስሊፒንግ ቢዉቲ››ን መሠረት አድርጎ የተዘጋጀ ነው::‹‹ውቢት እንቅልፏማ›› በአቀራረቡ የአገራችንን

ባህልና ወግ፣ እንዲሁም ጥንታዊውን የሀገረሰብ የጥበብ ቅርጽ የሆነው ተረት ክወናን መንገድ የተከተለና የዳንስን፣ ሙዚቃንና ድራማን ጥበባዊ ቅርጾችን አካቶ የተዘጋጀ መሆኑንም አዘጋጁ አክሎ ገልጿል::

ሉሲ ለመጨረሻ ጊዜ በሳንታ አና እየተጎበኘች ነው

በማጠናከርና ለአገሪቱ ገጽታ ግንባታ ያበረከተችውን አስተዋጽኦ በተመለከተ በፕሮፌሰር ዶናልድ ጀሃንሰን (ሉሲን ያገኙ) እና በዶክተር ዘረሰናይ ዓለም ሰገድ (ሰላምን ያገኙ) ሳይንቲስቶች ለተጋባዥ እንግዶች ገለጻ ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግበት ታውቋል:: ከዚህ ዐውደ ርዕይ ጉብኝት በኋላ ሉሲ ወደ አገሯ የምትመለስ ሲሆን፣ ከሚያዝያ ወር መጨረሻ በኋላ ኢትዮጵያ ትገባለች ተብሎ እንደሚጠበቅም ሚኒስቴሩ አመልክቷል::

ባለፉት ዓመታት በተለያዩ የአሜሪካ ከተሞች በሚገኙ ሙዚየሞች ለዕይታ የቀረቡት ሉሲና ሌሎች 149 ቅርሶች የአገሪቱን በጎ ገጽታ ለመገንባትና የኢትዮ አሜሪካን የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር በ2000 ዓ.ም. የተጓዙት ከአሜሪካ የሂዩስተን የተፈጥሮ ሳይንስ ሙዚየም ጋር በተፈረመው የአምስት ዓመታት የዐውደ ርዕይ ስምምነት መሠረት መሆኑ ይታወቃል::

በሳይንሳዊ ስሟ ‹‹አውስትራሎፒቲከስ አፋራንሲስ›› በመባል የምትታወቀው ሉሲ (ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ስሟ ድንቅነሽ)፣ በአፋር ሐዳር ውስጥ በ1966 ዓ.ም. የተገኘችው በአሜሪካዊው ፓሊዎአንትሮፖሎጂስት ዶናልድ ጆንሰን መሆኑ ይታወቃል:: ቅሬተ አካሏ የተሟላ አካል ያለው መሆኑ የተነገረላት ሉሲ ስሟን ከአንድ ዘፈን ማግኘቷ ይታወሳል::

‹‹ውቢት እንቅልፏሟ››-አዲሱ የልጆች ድራማ

የአንቷን ቼኾቭ 153ኛ ልደት ነገ በፑሽኪን አዳራሽ ይከበራል

የኢትዮጵያ ልዑካን ለመጨረሻው ዝግጅት አምርቷል

ኦሪጂናሉ የሉሲ ቅሬተ አካል በክሬኤሽን ሙዚየም‹‹ሉሲ›› ዳግም ተሠርታ (ሪኮንስትራክሽን)

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን እኤአ በ1957 ካርቱም ላይ በሱዳን፣ ግብፅ፣ ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ አባልነት ተመሠረተ:: ኮንፌዴሬሽኑ ከአፍሪካ አንድነት ድርጅትም በፊት የተመሠረተ የመጀመሪያው አህጉራዊ ማኅበር ነው::

ደቡብ አፍሪካ ትከተለው በነበረው የአፓርታይድ ሥርዓት ወዲያውኑ ከኮንፌዴሬሽኑም አባልነት ከውድድሮቹም ስትሠረዝ፣ የተቀሩት ሦስት አገሮች ግን ተጨማሪ አባላትን እየመዘገቡና ድርጅቱን እያጠናከሩ፣ ዛሬ 51 አባል አገሮች ያሉት ጠንካራ አህጉራዊ ማኅበር እንዲሆን መሠረቱን ጥለዋል::

የመጀመሪያው የድርጅቱ ፕሬዚዳንት ግብፃዊው አብድል አዚዝ አብደላ ሳሌም ለአንድ ዓመት ማለትም ከ1950-51 አገልግለዋል:: ሁለተኛው አሁንም ግብፃዊው ጄኔራል አብድል አዚዝ ሙስጠፋ ለ10 ዓመታት ከ1951 እስከ 61 አገልግለዋል:: ሦስተኛው ሱዳናዊው ዶክተር አብዱል ሐሊም መሐመድ ለ4 ዓመታት ከ1961 እስከ 1965 አገልግለዋል:: ይድነቃቸው ተሰማ ድርጅቱን በመሥራች አባልነትና በምክትል ፕሬዚዳንትነት ከ1950 እስከ 65 ማለትም ለ15 ዓመታት ሲያገለግል ከቆየ በኋላ በ1965 ፕሬዚዳንትነቱን ተረክቦ በተከታታይ ለ4 ጊዜ የአራት ዓመት አገልግሎት በመመረጡ ሕይወቱ እስካለፈችበት እስከ ነሐሴ 13 ቀን 1979 ዓ.ም. በፕሬዚዳንትነት ሠርቷል:: ከእሱ ሞት በኋላ የተመረጡት የካሜሩን ተወላጅ ኢሣ ሃያቱ እስካሁን ድረስ ድርጅቱን በፕሬዚዳንትነት በመምራት ላይ ይገኛሉ::

የድርጅቱ ዋና ጽሕፈት ቤት ካይሮ ሲሆን ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ጽሕፈት ቤቱን በዋና ፀሐፊነት የመሩትም ግብፃውያን ናቸው:: ድርጅቱ ሥራውን የሚመሩ ጠቅላላ ጉባኤ፣ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴና ልዩ ልዩ ቋሚ ኮሚቴዎች አሉት:: ባለፉት አርባ ዓመታት ያስመዘገባቸው ውጤቶች እና ዛሬም የሚገኝበት ደረጃ ለሌሎች አህጉራዊ ድርጅቶች ምሳሌ የሚሆን ነው::

በየዓመቱ በርካታ አህጉራዊ ውድድሮች በማዘጋጀት የአፍሪካ ወጣቶች ከአገር አገር እየተዘዋወሩ እርስ በእርስ እንዲተዋወቁና አህጉራቸውንም እንዲያውቁ አድርጓል::

ከኮንፌዴሬሽኑ እንቅስቃሴ አየር መንገዶች፣ ሆቴሎች፣ የጉዞ ወኪሎች እና ከቱሪዝም ጋር የተያያዙ የንግድ ተቋሞች ሁሉ ሰፊ ጥቅም አግኝተዋል::

በስፖርት አማካይነት የሚገኝ የማስተወቂያ ገቢ እያደገ በመጣ ቁጥር የኮንፌዴሬሽኑም የገንዘብ አቅም አድጓል:: ይኸም በአህጉሩ የእግር ኳስ ዳኞችን፣ ሐኪሞችን፣ አሠልጣኞችን በሰፊው ለማስተማርና ለአፍሪካ ፉትቦል ሁለገብ ዕድገት ለማስገኘት አስችሏል::

በዓለም ዋንጫና በኦሊምፒክ ውድድሮች ዛሬ

አፍሪካውያን እያስመዘገቡ ያሉት ውጤት ኮንፌዴሬሽኑ ለአፍሪካ ፉትቦል ዕድገት ለሚያደርገው ያላሰለሰ ጥረት ምስክር ነው::

ይድነቃቸው ተሰማ ያደረገው አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ ነው:: ይኸንንም አፍሪካውያን የሥራ ጓደኞቹ አልረሱም:: ሕይወቱ ባለፈ በ40ኛው ቀን በካይሮ የመታሰቢያ በዓል በማዘጋጀት፣ የድርጅቱን ልዩ የወርቅ ሜዳልያ በመሸለም አሁን ደግሞ የኮንፌዴሬሽኑን 40ኛ ዓመት ከእርሱ አሥረኛ ሙት ዓመት ጋር ነሐሴ 13 ቀን አረጋግጠዋል::

በሰለጠነው ዓለም ለአንድ ድርጅት መጠናከር ሠፊ አስተዋጽኣ ያደረጉ ሰዎች ሕይወታቸውም ካለፈ በኋላ ይታወሳሉ:: የኦሊምፒክ እንቅስቃሴ መሥራች እና መነሻው ላይ ሰፊ አስተዋጽኦ ያደረጉት ‹‹ባሮን ፒየር ደ ኩበርተን›› የዛሬ 100 ዓመት የሠሩት ሥራ አስከዛሬ በኢንተርናሽናል ኦሊምፒክ ቤተሰብ የተከበረ ነው:: በአፍሪካችንና በሌሎች በማደግ ላይ ያሉ አገሮች ግን ይኸ ባህል አልተለመደም:: ይልቁንም አዲሱ ተረካቢ ትውልድ ለሚያጋጥሙት ችግሮች ሁሉ ያለፈውን ተጠያቂ ለማድረግ ሲሞክር ነው የሚታየው::

በዚህ አንጻር የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን እንኳንስ የይድነቃቸውን ታሪክ ሊያወግዝና በየአጋጣሚው የመታሰቢያ ሥርዓቶች በማዘጋጀት አድናቆቱን መግለጽ መቻሉ ለአህጉራችን አዲስና ጥሩ ምሳሌ ነው::

ይድነቃቸው በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ የነበረውን አቋምና የፊፋና የአፍሪካ ፉትቦል ኮንፌዴሬሽንንም የግንኙነት ሒደት በአጭሩ ለአንባቢ ይገልጻሉ የሚል እምነት አለኝ::

ይድነቃቸው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ከተቋቋመበት ከ1949 ዓ.ም. ሕይወቱ እስካለፈችበት እስከ 1979 ዓመታት በነበሩት ጊዜያት ያደረገው አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ ነው:: በእነዚያ 30 ዓመታት ውስጥ ከሥራ ባልደረቦቹ ጋር በመተባበር በሦስት አገሮች አባልነት የተቋቋመውን ድርጅት ወደ ጠንካራ አፍሪካ አቀፍ ድርጅት ለመለወጥ ችሏል:: ከእሱ ሥልጣን የተረከቡት ኢሳ ሃያቱ የወረሱት ኮንፌዴሬሽን ሲቋቋም የነበረው አይደለም:: እሱ የፕሬዚዳትነቱን ሙሉ ሥልጣን በያዘበት በ1965 ዓ.ም. የነበረውም አይደለም::

ፍፁም የተለየ ድርጅት ነው:: በፊፋ ለአፍሪካ እኩልነት ያደረገው ያልተቋረጠ ትግል:: በሚከተሉት ነጥቦች ላይ

የነበረው የማይለወጥ እና ጽኑ አቋም ሀ. ጉቦኝነት በድርጅቱ ውስጥ እንዳይኖርለ. አንዳንድ የአፍሪካ የፖለቲካ መሪዎች በተጽእኖ

ውሳኔዎች ለማስለወጥ በድርጅቱ ታሪክ በተለያዩ ወቅቶች ያደረጓቸውን ሙከራዎች በመቋቋም

ሐ. የትምባሆና አልኮል ማስታወቂያዎች በአፍሪካ ስቴድየሞች እንዳይሰቀሉ በመከላከል

መ. አፓርታይድን በመቃወምየተለያዩ ውድድሮችን በመፍጠር እና በማስተዋወቅ

የአፍሪካ ተጨዋቾች፣ ዳኞችና ኮሚሽነሮች የኢንተርናሽናል ውድድሮች ልምድ እንዲቀስሙ ሁኔታዎችን በማመቻቸት እንዲሁም በተከታታይ የሥልጠና ፕሮግራሞች አፍሪካ በስፖርት ሐኪሞች፣ አሠልጣኞች፣ ተጨዋቾች እና ዳኞች እራሷን እንድትችል ማድረግ፤ ይድነቃቸው ለአፍሪካ እግር ኳስ ዕድገት ካደረጋቸው ከፍተኛ አስተዋጽኦዎች ውስጥ የሚጠቀሱ ናቸው::

የእነዚህን ጥረቶች ውጤት በከፊል በሕይወት ዘመኑ ለመመልከት በቅቷል:: ይሁንና እዚህ ላይ ይድነቃቸው የሥራ ባልደረቦቹን ሙሉ ትብብርና ድጋፍ ባያገኝ ትግሎቹና ውጤቶቹ ሁሉ ሊሳኩ እንደማይችሉ መገንዘብ ያስፈልጋል:: ከእርሱ በፊት የነበሩት ፕሬዚዳንቶች፣ አብረውት የሠሩ የሥራ አስፈጻሚ አባላት እና ጠቅላላው አባል ፌዴሬሽኖች ድርሻቸውን አበርክተዋል::

ካይሮ የሚገኘውን ጽሕፈት ቤትም በጣም ያደንቅ ነበረ:: ሙራድ ፋህሚና ልጃቸው ሙስጠፋ ፋህሚ፣ እንዲሁም እጅግ ጠንካራ የነበሩት የኮንፌዴሬሽኑ ምክትል ዋና ፀሐፊ ወ/ሮ አሚራ ከሌሎቹ የጽሕፈት ቤቱ አባላት ጋር ይኸንን ምንአልባት በአፍሪካ ካሉት አህጉራዊ ድርጅቶች ሁሉ የተሻለ ውጤት ያስመዘገበውን ድርጅት ለማጠናከር ላደረገው ጥረት ያበረከቱት ዕርዳታ በቃላት ሊገለጽ አይችልም::

የቀድሞው የቶጎ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት እንዲህ ብለው ነበር:: ‹‹በ1971 ዓ.ም. በአፍሪካ ወጣቶች የወደፊት ዕድል ታላቅ እምነት ያለው አንድ ሰው አገኘሁ:: ያ ሰው የአፍሪካን የእግር ኳስ ለማሳደግ ሥራና ጊዜ እንደሚጠይቅ ቀደም ብሎ የሚያምን ነበር:: በታላቅ ትጋትና በትህትና መርህ ያምኑ የነበሩት ይድነቃቸው ተሰማ በአፍሪካ የእግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ሥራቸውን በምን ዓይነት ብልሃትና ጥበብ ያካሄዱ እንደነበር ዛሬ ሁላችንም እየተገነዘብን ነው::››

ታደለ ይድነቃቸው ተሰማ፣ ‹‹ይድነቃቸው ተሰማ መስከረም 1-1914- ነሐሴ 13-1979 በዓለምና በስፖርት ዓለም›› (1989)

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን

የአፍሪካን እግር ኳስ በተለያየ ጊዜ የመሩት የግብፁ ጄኔራል አብዱል አዚዝ ሙስጠፋ(በግራ) እና አቶ ይድነቃቸው ተሰማ

Page 71: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 23 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2

በዳዊት ወርቁ

የገበጣ መጫወቻ ከመሰለው አስፋልት ዳር ቆማ ታክሲ እየጠበቀች ነው:: ምንም ክረምት ቢሆን፣ ምንም ካስፋልቱ ቆሬዎች ላይ ጎርፍ ቢያቁር፣ አንድም ለካፊ ሾፌር ፣ ተሸቀዳድሞ እድፍ ውሃ አላከናነባትም:: ይህም ስላልሆነ ክፉኛ አዘነች:: ተብከነከነችም:: እንደዚያ ‹‹ደግ ዘመን›› መለከፍ እንደቀረባት ዘግይታም ቢሆን ደረሰችበት::

‹‹ሴትን ልጅ ለካፊ ወንዶች እማይለክፏት በሦስት ምክንያት ነው›› ይላት ነበር መላኩ:: ሰባተኛ ፍቅረኛዋ:: ሾፌር ነበር:: የላዳ ታክሲ ሾፌር::

መላኩ ሴትን ልጅ ለካፊ ወንዶች የማይለክፉበትን ሦስት አንቀጾች ሲዘረዝርም፣

አንቀጽ አንድ፣ ጠመንጃ አንጋች ከሆነች

አንቀጽ ሁለት፣ መነኩሴ ከሆነችና

አንቀጽ ሦስት፣ ካራቲስት ከሆነች ነው ይላል::

(የባለታሪካችን ስም በዚች ያጭር አጭር ታሪክ ላይ ቢነሳም ባይነሳም ምንም ስለማያመጣ በስምምነት እንተወዋለን)

እሷም ‹‹መላኩዬ አንተኮ ታክሲ ሳይሆን መንኮራኩር ነጂ መሆን ነበረብህ››፤ ትለው ነበር ስለሴት ልጅ አለመለከፍ ሦስቱን ምክንያቶች ተመራምሮ ስለደረሰበት::

ከሆነ ጊዜ በኋላ ግን ለካፊዎች እሷን መልከፍ እንዳቆሙ ዕለቱንና ሰዓቱን በውል በማታስታውስበት ጊዜ አወቀች::

ለመሆኑ ለካፊዎቹ መልከፋቸውን ለምን አቆሙ? . . . በሰባተኛው ፍቅረኛዋ መላኩ መርህ መሠረት፣

ጠመንጃ ማንገት ጀምራ ነው? . . . አይደለም::

መንኩሳ ነው? . . . አይደለም::

ጁዶ ጀምራ ነው? . . . አይደለም::

ታዲያ ምን ሆና ነው? . . .

ሰባተኛው ፍቅረኛዋ መላኩ ያልደረሰበት፣ ወይም ሆን ብሎ ያልነገራት አራተኛ አንቀፅ ቢኖር ነው::

አንድ ወደፊት የሚመጣ ሳይሆን ወደኋላ የሚሄድ የሚመስል ላዳ ታክሲ፣ ሲንገታገት መጣና አጠገቧ ቆመ::

አንገቱን በተከፈተው መስኮት አስግጎም ሾፌሩ፣ ‹‹ትሄጂያለሽ?›› አላት

አንዳችም ሳትመልስለት ወደ ኋለኛው በር አመራች::

በሩ አልከፈት አላት::

‹‹ቆይ እንደሱ አይደለም›› ብሎ ሾፌሩ በሲባጎ ገመድ የታሰረውን እጀታ ከውስጥ ሲስበው ተከፈተ::

ገባች::

ተቀምጣም ዙሪያ ገባዋን ትቃኝ ገባች:: ታክሲዋ የቀበሌ ቤት ትመስላለች:: ሾፌሩ የታክሲዋን ቤልት ቆርጦ ሱሪውን አስሮበት ሳይሆን አይቀርም ቤልቷ የለም:: ወንበሩን እየነቀለም ቤቱ ይቀመጥበታል መሰለኝ አለቅጥ ወደኋላ ተለጥጦ ጥጋበኛ አስመስሎታል:: የተቀመጠችበት ወንበር ተላልጦ፣ ስፖንጁ አፈትልኮ ስፕሪንግ ሽቦው ይታያል:: ታክሲዋን ባዲስነቷም ባይሆን በጥሩ ይዞታ ላይ ሆና ታውቃታት ነበር:: ሰባተኛው ፍቅረኛዋ መላኩ ነበር የሚሾፍራት::

መድረሻዋ እስክትደርስም ያቺ ታክሲ ከሰባተኛው ፍቅረኛዋ መላኩ ጋ ሳለች ያሳለፈቻቸውን አያሌ ትዝታዎች እንደማግ ጎልጉላ አወጋቻት:: ትለክፍበት ስለነበረው ‹‹ደግ ጊዜ››::

ቤቷ ስትደርስ አንገቷን ጉልበቶቿ ውስጥ ቀብራ ስቅስቅ ብላ አነባች::

አራተኛውን አንቀጽ ሰባተኛ ፍቅረኛዋ መላኩ ሳይሆን ይነዳት የነበረችው ታክሲ ነግራት ነበርና::

ቁሶች በርጅና መስታወታቸው ማርጀታችንን ሲያሳዩን እንደሰው ይሉኝታ አያውቁም::

ጥር 2005 አዲስ አበባ

አራተኛው አንቀጽ . . . የአጭር አጭር ልቦለድ ጭኮ

አስፈላጊ ጥሬ ዕቃዎች• 20 ጆግ (10 ኪሎ ግራም) ነጭ

ገብስ• 2 የቡና ስኒ (200 ግራም) ነጭ

አብሽ• 2 የቡና ስኒ (200 ግራም) ነጭ

አዝሙድ• 2 የቡና ስኒ (200 ግራም)

ድንብላል

አዘገጃጀት• ነጭ ገብሱን በደንብ ለቅሞ

መሸክሸክ፤• በፈላ ውሃ ገንፈል እያደረጉ

ማውጣት ወይም የፈላ ውሃ ውስጥ በሳፋ ዘፍዝፎ ለሁለት ሰዓት ያህል ካቆዩ በኋላ አጠንፍፎ በአንድ እቃ ውስጥ አፍኖ ማሳደር፤

• ጠዋት በሰፊ እቃ ብትን አድርጎ ማስጣት፤

• ጠፈፍ ሲል በትንሽ፣ በትንሹ መቁላት (በሚቆላበት ጊዜ እንደበሶ እንዳይጠቁር ተጠንቅቆ መቁላት)፤

• ሸክሽኮ ከገለባው መለየት፤• ንፁሕ እቃ ላይ አስጥቶ

ማድረቅ፤• ነጭ አብሹን ለቅሞ ሳያሳርሩ

መቁላት፤• ነጭ አዝሙዱንና ድንብላሉን

በነጩ መቁላት፤• ገብሱ ከደረቀ በኋላ ሁሉንም

ደባልቆ አልሞ ማስፈጨትና ማስቀመጥ::

• [ጭኮውን መብላት ሲፈለግ በንፁሕ እቃ በለጋ ቅቤና ጨው ለውሶ ትሪ ላይ መጠፍጠፍና ቅርፅ እያወጡ መመገብ ይቻላል::]

(ደብረወርቅ አባተ፤ ‹‹የባህላዊ ምግቦች አዘገጃጀት››፣ 2003)

ላ ን ዳ ፍ ታ

ይሰነዝራል:: አንዳንድ ሸማኔዎች የተዋወቋቸውና እየተገለገሉባቸው የሚገኙ ዘመናዊ የተባሉ የመሸመኛ መሣርያዎች ቢኖሩም ተመራጭ መሆን አልቻሉም:: ግርማ ለዚህ ምክንያት የሚያደርገው ከባህላዊዎቹ መሸመኛ መሣርያዎች በበለጠ የሰው ጉልበት ይጠይቃሉ በማለት ነው:: ይህ አስተያየት ለውጥን ከመጥላት ወይም ከመፍራት በመነጨ እንዳልሆነም ያሰምርበታል::

ሸማኔውንና ለባሹን ወይም ተጠቃሚውን ለማገናኘት ብዙ ሙከራዎች የተደረጉ ቢሆንም በቅርቡ የአዲስ አበባ ከንቲባ በነበሩት አቶ አርከበ እቁባይ የተሞከረው ጥረት የተሻለ እንደነበር ግርማ ያስታውሳል::

ግርማ እንደሚናገረው ‹‹ሁሉንም ሸማኔ ባለመደብር ማድረግ አይቻልም፤ ነገር ግን በየቀኑ መገበያየት የሚቻልባቸው የቁም ገበያዎች የሸማኔውንና ለባሹን ግብይት የተለመደ ለማድረግ ይጠቅማሉ::›› በእርግጥም በከንቲባ አርከበ አስተዳደር በሽሮሜዳ አካባቢ መንገድ ዳር ተገንብተው ውጤታማ ከሆኑትና በተለምዶ የአርከበ

ሱቆች ከሚባሉት በተጨማሪ ሁለት ሰፋፊ የቁም ገበያዎች ተገንብተዋል:: ይሁን እንጂ ሸማኔውም ሆነ ተጠቃሚው እንዲለምዳቸው የተሠራ ሥራ ባለመኖሩ ወይም በታሰበው መጠን ባለመጥቀማቸው ይሆን አይታወቅም ተገልጋይ አላቸው ለማለት አያስደፍርም::

‹‹የሸማ ውጤቶች ኢትዮጵያዊ ተጠቃሚውንና ነጋዴውን ብቻ ሳይሆን የውጭ ጎብኚዎችንም ፍላጐት በመማረክ ላይ ይገኛል:: አዲስ አበባ መጥቶ በሸማኔ የተዘጋጁ የአገር ልብስና ሌሎች የሸማ ውጤቶችን ሳይገዛ የሚመለስ ጐብኚ በጣት የሚቆጠር ነው፤›› በማለት የሚናገረው ታሪኩ ዮሐንስ በአንድ የአስጐብኚ ድርጅት ተቀጣሪ ነው:: ታሪኩ እንደሚለው፣ አንዳንዶቹ ጐብኚዎች የሸማ ውጤቶችን ለመግዛት በቀጥታ ስለሚጠይቁ ወደ ሽሮሜዳ እንደሚወስዷቸውና ሌሎች ደግሞ የአዲስ አበባን አጠቃላይ ገጽታ ለመመልከት ወደ እንጦጦ ጋራ ስለሚጓዙ እግረ መንገዳቸውን ሽሮሜዳ ገበያን ያስጐበኟቸዋል:: እናም በሽሮሜዳ አካባቢ ነዋሪና የምጣኔ ሀብት ባለሙያ የሆነው

ወጣት ሔኖክ ‹‹ሸማኔው ከምርቱ ተገቢ ጥቅም እንዲያገኝ

ለባሹንና ሸማኔውን በቀጥታ እንዲገበያዩ ማመቻቸት

ፋይዳው እስከዚህም ነው፤›› ይላል:: ይልቁንስ ሸማኔው

በጥቂት ሰዓታት ውስጥ ተፈጥሯዊነታቸውን ያልቀየሩ ብዙ

ሸማ ማምረት የሚችልበትን ዘመናዊ ማሽኖችና ሌሎች

ቴክኖሎጂዎችን ማስተዋወቁ ይበጃል:: ሔኖክ ሐሳቦቹ

የግሉና አዲስ እንዳይደሉ ገልጾ፣ በተጨማሪም በጣም

በርካታ የልብስ ዲዛይነሮች፣ ሞዴሊስቶችና ነጋዴዎች

ወደዚህ ገበያ የሚመጡበት መንገድ ተስፋፍቶ ከቀጠለ

ምርቱ አሁን እንደሚታየው ለሸማኔው ጥቅም ሥጋት

እንደማይሆን ይተነብያል:: እውን የሔኖክ ትንቢት ይደርስ

ይሆን?

ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው

[email protected] ማግኘት ይቻላል::

‹‹ኢስታ ናማ››... ከክፍል 2 ገጽ 21 የዞረ

የአዲስ አበባን... ከክፍል 2 ገጽ 21 የዞረ

የህብረት ሥራና የገበያ አገልግሎት ማኅበር ነው:: ከሁለት መቶ አርባ በላይ አባላትን ያቀፈውና

ሕጋዊ ሰውነት ያለው ይኸው ማኅበር የመስኖ ልማቱን የሚያካሂደው በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በወረዳ አምስት አቋርጦ በሚያልፈው በዚሁ ወንዝ ዳርቻ ነው:: ከአትክልቱ ልማት ጋር የተያያዘው ይኸው ወንዝ በስተጀርባው በአዲስ አበባ አስተዳደር ቄራዎች ድርጅት፤ በታላላቅ ጋራዦችና በልዩ ልዩ አገልግሎት መስጪያ ተቋማት የተከበበ ሲሆን፣ ከፊት ለፊቱ ደግሞ ቁጥሩ እጅግ የበዛ የወረዳው ነዋሪዎች ይገኙበታል::

በስፍራው ሲንቀሳቀሱ ካገኘናቸው አምራቾች መካከል መስፍን ቢረዳ አንዱ ነው:: ዕድሜው 32 ሲሆን ዛሬ በሕይወት የሌሉትን አባቱን ተከትሎ በዚሁ የልማት ሥራ ላይ የተሰማራው ገና በልጅነቱ ነው:: እናቱን፣ ወንድሞቹንና እህቶቹን በአጠቃላይ ቤተሰቡን የሚያስተዳድረው ከዚሁ ልማት በሚገኘው ገቢ ነው::

መስፍን እንደሚለው ወንዙን ተከትሎ ሰባት ግድቦች አልፎ አልፎ ተገንብተዋል:: የወንዙ ውኃ በግድቦቹ እየገባ እንዲጠራቀም ከተደረገ በኋላ በመስኖ ለአትክልት ልማት ይውላል::

የውኃው መጥቆር በምርቱ ላይና በሰው ጤንነት ያስከተለው ተጽእኖ አለ? የሚል ጥያቄ የቀረበለት መስፍን፣ “አፈሩ በእርግጥ ለምነትን አጥቷል፣ ምርቱም ከዓመት ዓመት እየቀነሰ መጥቷል:: ቀደም ባሉት ዓመታት ጥቅል ጎመን እናመርት ነበር:: አሁን

ግን አፈሩ አልቀበልም ብሎናል:: በሰው ሕይወት ላይ ግን እስካሁን የደረሰውን ጉዳት አላየሁም፣ አልሰማሁም:: እኔና ቤተሰቤ አትክልት ተመጋቢዎች ነን:: በተለይ ሠላጣ የዘወትር ምግባችን ነው:: አንድም

ቀን ቁርጠት እንኳን ተሰምቶን አያውቅም፤” ሲል መልሷል::

ይህም ሆኖ ግን የቄራዎች ድርጅት የሚያርዳቸውን እንስሳት ፈርስ የሚለቀውና በአቅራቢያው የሚገኙ ልዩ ልዩ የአገልግሎትና የምርት ተቋማት የተገለገሉባቸውን ፍሳሾች የሚያስወግዱት በዚሁ ወንዝ ውስጥ ነው:: በዚህም የተነሳ የውኃውንና አትክልቱን ናሙና ለምርመራ ለኢትዮጵያ ጤናና ሥነ ምግብ ምርምር ኢንስቲትዩት ከአምስት ዓመት በፊት ቀርቦ ነበር:: ኢንስቲትዩቱም የወንዙ ውኃ በመርዛማ ፍሳሾች ተበክሏል፣ በሰውና በተክሎች ላይ የሚያስከትለውን ጉዳት የምንገልጸው ግን ፍርድ ቤት ወይም ፖሊስ ሲጠይቀኝ ብቻ ነው የሚል መልስ እንደሰጣቸው ተናግሯል::

እ.ኤ.አ በ2011 የተካሄደው ጥናት እንደሚያሳየው ማኅበራቱ የአትክልት ልማት የሚያካሂዱበት የአቃቂ ወንዝ ከቄራዎች ድርጅት በሚለቀቀው ፈርስ፣ ከመጸዳጃ ቤቶች በሚወጡ ፍሳሾች፣ ከጋራዦችና ከነዳጅ ማደያ ጣቢያዎች በሚለቀቁ እጣቢዎችና በተቃጠለ የሞተር ዘይቶች ተበክሏል:: በዚህ መልኩ የተበከለውን ውኃ ሳይታከም ለአትክልት ልማት እንዲውል ማድረጉ በሰው ጤንነት ወይም ሕይወት ላይ አደጋ እንደመጋበዝ ነው::

ቀደም ባሉት ዓመታት ወንዙ ትናንሽ አሳና እንቁራሪቶች ይኖሩበት ነበር:: አሁኑ ግን ከኢንዱስትሪዎች ከሆስፒታሎችና ከሽንት ቤቶች የሚለቀቁ መርዛማ ፍሳሾች ውኃውን ከማጥቆራቸው በተጨማሪ የነበሩትን ነፍሳት አጥፍተዋል:: በዚህ ዓይነቱ ውኃ የሚለማውን አትክልት የሚመገብ ሰው ደግሞ ወዲያው ሕመም ባይሰማውም እየቆየ ሲሄድ ለተለያዩ በሽታዎች ሊዳረግ እንደሚችልና ከወዲሁ

አማራጭ መፍትሔ ሊፈለግ እንደሚገባ ጥናቱ ጠቁሟል::

በአዲስ አበባ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የከተማ ግብርና የሥራ ሑደት ባለቤት የሆኑት አቶ ዓለማየሁ ታዬ ስለጉዳዩ ተጠይቀው “የወንዙን ውኃ አክሞ ንጹህ እንዲሆን የማድረግ ሁኔታ እስካሁን አልተሠራም:: የከተማ ግብርና ግን የአቃቂንም ሆነ የሌሎቹን ወንዞች ውኃ ከብክለት ነፃ የሚያደርግ ፖሊሲና ስትራቴጂ ቀርጾ አጽድቋል:: በዚህ ፖሊሲና ስትራቴጂ በመጠቀም የተበከለን ውኃ የማጥራቱ ሥራ ወደፊት ይቀጥላል:: ከዚህ ጎን ለጎን ባለድርሻ አካላት ወደ ወንዙ የሚለቁትን ፍሳሽ እንዲያቆሙ የማድረጉ ሥራ ጉዳዩ በሚመለከተው አካል መከናወን ይኖርበታል፤” ሲሉ መልሰዋል::

አቶ ማንቻለው ዓለሙ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቄራዎች ድርጅት የሕዝብ ግንኙነት ኤክስፐርት ድርጅቱ ፈርሱን በማጥራት (ትሪት በማድረግ) የሚወጣውን ንጹህ ውኃ ብቻ ወደ ወንዙ እንዲገባ የማድረግ ሥራ ለመጀመር በእንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል::

ወይዘሮ አረጋሽ ሳሙኤል በኢትዮጵያ ጤናና ሥነ ምግብ ምርምር ኢንስቲትዩት የጤናና የሥነ ምግብ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የአቃቂን ወንዝ መበከልን አስመልክቶ በድርጅቱ ባለሙያዎች የተከናወነ ሰፊ የጥናት ውጤት መኖሩን ገልጸው በጥናቱ ውጤት ዙሪያ ለመነጋገር ግን ጊዜ እንደሚፈጅ አስረድተዋል::

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በዚህ ዙራያ ያለውን አስተያየት ለመጠየቅ ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው ሳይሳካልን ቀርቷል::

Page 72: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 24 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

ማስታወቂያ

Page 73: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 25 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2ማስታወቂያ

Page 74: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 26 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

ማስታ

ወቂያ

የኦዲት ሥራ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ከተሞች የትብብር መድረክ በበጎ አድራጎትና ማህበራት ኤጀንሲ ህጋዊ ሆኖ 28 የኢትዮጵያ ከተሞች ያቋቋሙት መንግስታዊ ያልሆነ አገር በቀል ማህበር ነው፡፡ አላማውም የአባል ከተሞች አመራር አባላትን የርስ በርስ የልምድ ልውውጥ መድረክ በማዘጋጀት ልምዳቸውንና መልካም ተሞክሮዎቻቸውን እንዲለዋወጡ ማድረግ እንዲሁም በከተሞች የሚታየውን ያልተመጣጠነ ዕድገት፣ ድህነትና ስራ አጥነት ለመቅረፍ ከተሞች የርስ በርስ ግንኙነታቸውን በማጠናከር እንዲሁም ከሌሎች መልካም ተሞክሮ ካላቸው የውጭ ሃገር ከተሞች የልምድ ልውውጥ በማድረግ ጠቃሚ አማራጮችንና ልምዶችን በመቀመር በአባል ከተሞች የማስፋፋት ስራ በማከናወን ላይ የሚገኝ መንግስታዊ ያልሆነ ተቋም ሲሆን የ2012 ዓመት ሂሳብ ሪፖርት (2) ሁለት ቦክስ ፋይል ብቻ የሆነ በውጪ ኦዲተሮች ማስመርመር ይፈልጋል፡፡

በዚሁ መሰረት የሚከተሉትን መስፈርት የሚያሟሉ የኦዲት ድርጅቶች አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡

• የ2005 በጀት ዓመት የታደሰ ፈቃድ ያላቸው፣• የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው፣• በፌዴራል ኦዲት መ/ቤት የተመዘገቡበት የሙያ ፈቃድ ያላቸው፣• ስራውን በምን ያህል ጊዜ ሰርተው እንደሚያጠናቅቁና ምን ያህል ክፍያ እንደሚጠይቁ በመግለፅ ከፕሮፋይላቸው ጋር በማያያዝ፣ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ5 ተከታታይ ቀናት፣ በሚከተለው አድራሻ በማቅረብ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን ይገልጻል፡፡ ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

አድራሻአ/አ ልደታ ክ/ከተማ፣ ቀበሌ 7/14፣ የቤት.ቁ 403፣ በሔራዊ ባንክ ፊት ለፊት፣ መምህራን

ማህበር ሕንጻ ላይ፣ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 127 ስልክ ቁጥር 011 895 11 85 ፖ.ሣ.ቁ 40960 አ/አበባ ኢትዮጵያ

የኦዲት ሥራ ማስታወቂያድርጅታችን Voluntary Service (Vs) የ2012 በጀት

ዓመት ሒሳቡን በተፈቀደላቸው ኦዲተሮች ማስመርመር

ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሒሳብ ምርመራ ሥራ ለማከናወን

የስራ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ ድርጅቶችን

እንዲወዳደሩ ይጋብዛል፡፡

ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ

ባሉት አስር ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ በፖ.ሳ.ቁ.

34760 አዲስ አበባ በመላክ መወዳደር የሚቻል መሆኑን

እንገልፃለን፡፡

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0911 68 69 21

ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን

ማስታ

ወቂያ

ሸለምጥማጦች አጫጭር ቅልጥም ያላቸውና ሽንጠ ረጅም የሆኑ፣ በከፊል ዛፍ ላይ የሚኖሩ ሥጋ-በሎች ናቸው:: በሙሉ ጀርባቸው በረጃጅም ተርታዎች ነጠብጣብ አላቸው:: ረጅም ጅራታቸው ቀለበቶች የመሳሰሉ ጥቋቁር ክቦች አለው:: ሁሉም እግሮቻቸው አምስት አምስት ጣቶች አሏቸው:: ክብደታቸው ሁለት ኪ.ግ ገደማ ነው:: ዓይኖቻቸው ከፊት ለፊት ይገኛሉ:: አፋቸው ጋ ረጃጅም ፀጉር አላቸው:: ኮኮኔዎቻቸው የጎበጡና ስል፣ የሚወጡና የሚገቡ ናቸው::

በኢትዮጵያ የተለያዩ የሽለምጥማጥ ብቸኛ ዝርያዎች ይገኛሉ:: ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ሽለምጥማጦች፣ በዝርዝር የተጠኑት ሁለቱ ብቻ ናቸው:: ‹‹G. tigrina›› እና ‹‹G. genetta››:: የሸለምጥማጦች ምንጭ የኮንጎ የዝናብ ደን ነው ቢባልም፣ ከሰሃራ በስተቀር በአፍሪካ የሌሉበት ሥፍራ የለም:: ከዚህም አልፈው በደቡባዊ ምዕራብ አውሮፓና በዓረቢያ ባሕር ሰርጥም ይገኛሉ:: መደበቂያና ምግብ በሚያገኙባቸው ሥፍራዎች ሁሉ ይገኛሉ:: ገና በቂ ጥናት የተደረገባቸው ባይሆኑም፣ የተለያዩት ብቸኛ ዝርያዎች በመልክና በምግባር የተመሳሉ መሆናቸው ግልጽ ነው:: ‹‹G.felina›› እና ‹‹G.tigrina›› ከሌሎቹ ሁሉ ሰፊ ስርጭት ያላቸው ከመሆናቸው በላይ ያሉበት ቦታ ተደራራቢ ነው:: በአንድ ሥፍራ እየኖሩም ግን አንዱ ዓይነት ከሌላው የማይዋለዱ ናቸውና የተለያዩ ብቸኛ ዝርያዎች ለመሆናቸው የሚያጠራጥር ነገር የለም::

ሸለምጥማጦች እጅጉን የተለያዩ ዓይነት ምግቦች ይበላሉ:: አይጥ፣ የሌሊት ወፍ፣ ሜንጦዎች፣ አእዋፍ (ዶሮ የሚያህሉት ድረስ)፣ እንሽላሊት፣ እባብ፣ እንቁራሪት፣ የእግዜር-ፈረስ፣ ጢንዚዛ፣ ሸረሪት፣ አርባ እግር፣ ጊንጥ፣ የሳት ራት የመሳሰሉትን ሁሉ ይበላሉ:: ፍራፍሬና የአበባ ወለላም ይበላሉ:: የተለያዩ ብቸኛ ዝርያዎች፣ የተለያዩ ሥነ ምህዳራዊ ሁኔታዎች ስለሚፈቅዱ፣ ተለያይተው ይኖራሉ:: በደን ውስጥ የሚገኙ የሸለምጥማጥ ብቸኛ ዝርያዎች ቢኖሩም፣ ‹‹G. tigrina, G. abyssinica, G. feline,›› የተባሉት የሚገኙት ዛፍ በሌለባቸው ገላጣ ሥፍራዎች ነው:: ‹‹G. tigrina›› ሰው በሚኖርባቸው አካባቢዎች ይኖራል:: የታወቀ የዶሮ ሌባ ነው::

ማኅበራዊ አደረጃጀታቸው፣ ግለኛ፣ ዋነኞቹ ወንዶች

ሸለምጥማጥ ‹‹Genet››(Genetta feline, G.tigrina, G.abyssinica)

የሸለምጥማጥ ጠረን ይኖረዋል::ሸለምጥማጦች ሲጣሉ፣ ንክሻቸው የሚያነጣጥረው

ራስ፣ አንገትና ደረት ላይ ነው:: ባይቋሰሉም ፀጉር ይነጫጫሉ:: ከዚያም ተሸናፊው ይጮሃል፣ ይሸናል፣ ቂጡ ጋ ካለው ከረጢት ውስጥ ያለውን ግም ፈሳሽ ይለቃል::

ሴቶቹ በዓመት ሁለት ጊዜ በአማካይ በአንድ ጊዜ ከሁለት እስከ ሦስት ግልገሎች ይወልዳሉ:: የሚያረግዙት ከ70 እስከ 77 ቀኖች ነው:: በስሪያ ወቅት የሴቷን ብልት ወይም ሽንት ወይም እዥ ያሸተተ ወንድ፣ ሽቅብ ያንጋጥጣል:: የደራች መሆኑን ይገነዘባል:: ከዚያ እያጉረመረመና የጉንፋን የመሰለ ድምፅ እያሰማ ይከተላታል:: በመጀመርያ ታፋና ጭራዋን ዝቅ አድርጋ ትሸሸዋለች:: በኋላ ግን እንዲጠጋት ትፈቅዳለች:: ፊታቸውንና ብልቶቻቸውን ተሸታትተው፣ ጉንጮቻቸውን ይተሻሻሉ:: ሴቷ ጭራዋን ከፍ አድርጋና ወደ ጎን ብላ፣ ከታፋዋ ከፍ ብላ ትጋብዘዋለች:: ደረትና ሆዱ ከታፋዋ ላይ አርፎ፣ በእጆቹ ከላይ በኩል ጭኖቿን ይዞ፣ ግንኙነቱን ይፈጽማል:: አንዳንዴ አምስት ደቂቃ በሚፈጀው ስሪያ በመጨረሻዎቹ ሰኮንዶች፣ የአንገቷን ፀጉር ይነክሳል:: ከዚያ ሴቷ በቂጧ ትንፏቀቅና በጀርባዋ ትንከባለላለች:: በመጨረሻ ሁለቱም የየራሳቸውን ብልቶች ይልሳሉ::

ሸለምጥማጦች የሚወልዱት በጉድጓድ ውስጥ ወይም ከቅጠሎች በተሠራ ጎጆ ነው:: እናቲቱ እየላሰቻቸውና ዓይነምድራቸውን እየበላች፣ ከግልገሎቿ ጋር ብዙ ቀናት ትቆያለች:: ከቦታ ቦታ ስታዘዋውራቸው የጀርባቸውን ቆዳ ነክሳ አንጠልጥላ ነው:: የግልገሎቹ ፀጉር ግራጫና ምልክቶቹ የማይለይ ነው:: ዓይንና ጆሯቸው የሚከፈተው ወደ 10ኛው ቀን ገደማ ነው:: ከወተት ሌላ መመገብ የሚጀምሩት ከ6 ሳምንቶች በኋላ የመንጋጋ ጥርሳቸው ሲወጣ ነው:: አዳኝነቱን የሚመሩት ቀስ በቀስና ደረጃ በደረጃ ነው:: ከ18 እስከ 254 ሳምንት እስኪሞላቸው፣ እናታቸው የገደለችውን ይበላሉ:: ለማደን ጥረት የሚያደርጉት 11 ሳምንት ገደማ ከሞላቸው በኋላ ነው:: አደን ማደን ከጀመሩ በኋላ በእዥ ምልክት ማድረግም ይጀምራሉ::

ሰሎሞን ይርጋ (ዶር.) ‹‹አጥቢዎች›› (2000)

ሥ ነ ፍ ጥ ረ ት

አንዳንዴ አድፍጠው፣ አንዳንዴ አሯሩጠው ያድናሉ:: የሌቴ እንስሳት ናቸው:: ደማቅ የጨረቃ ብርሃን ሲኖርም ተግባሮቻቸውን በቅልጥፍና ያካሄዳሉ:: በኢትዮጵያ፣ በኦሞ ፓርክ በተደረገ ጥናት፣ ‹‹G. tigrina›› ብዙ ተግባሮቻቸውን የሚያካሂዱት፣ ፀሐይ ከጠለቀች ጀምሮ እስከ እኩለ ሌሊት መሆኑ ተረጋግጧል::

የሸለምጥማጦች የማሽተት ኃይል ከፍተኛ ነው:: ሽንት፣ ዓይነ ምድር እና ከተለያዩ የአካል ክፍሎች ከሚወጡ እዦች፣ የአካባቢው ኗሪ ሸለምጥማጥ ወይንስ የእንግዳ መሆኑን መለየት ይችላሉ::

በዓይነ ምድር መውጫና በቆለጥ (ወይም ሴት ከሆነች በብልቷ) መካከል ዘይትነት ያለው ብጥብጥ እዥ የሚያወጣ ዕጢ አላቸው:: በዚህ እዥ ነው ወይ ከኋላቸው ዝቅ ብለው፣ አሊያም ከቆመ ነገር ጋር ተሻሽተው ምልክት የሚያደርጉበት:: መለስተኛ መዓዛ ያለው ይህ እዥ፣ ሲደርቅ ቡናማ ጥቁር ይሆናል:: ተደጋግሞ የተጠረገበት ግንድ ከአራት ዓመት በኋላም

የአያሌ ሴቶችን መኖርያ የሚጠብቁበት፣ ማለትም አንድ ወንድ ብዙ ሴቶችን የሚቆጣጠርበት ነው:: ምንም እንኳ አንዳንዴ ወንድና ሴት ከልጆቻቸው ጋር እንደ አንድ ቡድን ሊታዩ ቢችሉም፣ ሸለምጥማጦች ግለኛ ቢባሉ ትክክል ነው:: ትልቁ ቡድን እናትና ቡችሎቿ ናቸው:: ይኸም የሚዘልቀው፣ ቢበዛ መንፈቅ ሞልቷቸው ጡት እስኪጥሉ ነው:: ሆኖም የዳበረ አካል የሚኖራቸው በሁለት ዓመታቸው ግድም ነው:: ወንዶቹ እስከ አምስት ካሬ ኪ.ሜ በሆነ ሥፍራ የሚዘዋወሩ ሲሆኑ፣ ሴቶቹ እጅግ በጠበበ ሥፍራ የተወሰኑ ናቸው:: ሆኖም ግን ተይዘው፣ ከተጠመዱበት ሥፍራ 35 ኪ.ሜ ርቆ የተለቀቁ ሴት ሸለምጥማጦች፣ በጥቂት ቀናት ከመኖርያ ሥፍራቸው ተመልሰዋል:: ወንዶቹ በክልላቸው በሚዘዋወሩበት ጊዜ፣ የርምጃቸው ፍጥነት በሰዓት ሦስት ኪ.ሜ ይሆናል::

ሸለምጥማጦች ቀልጣፋና በዛፍ ላይ ሆነ በምድር ብቁ አካላዊ እንቅስቃሴ ያላቸው አዳኞች ናቸው::

Page 75: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 27 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2

አሰናጅ፡- ምሕረት ሞገስ፣ ሔኖክ ያሬድ

የቫላንታይን ቀን በአሜሪካ፣ በካናዳ፣ በሜክሲኮ፣ በእንግሊዝ፣ በፈረንሳይና በአውስትራሊያ ከጥንት ጀምሮ የሚከበር ነው:: ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ደግሞ እንደቀደሙት አገሮች በስፋት ባይሆንም በአፍሪካ ያሉትን ጨምሮ በተለያዩ አገሮች የቫላንታይን ቀንን ማክበር እየተለመደ መጥቷል:: በተለይ በከተማ ውስጥ በሚኖሩና ለመረጃ ቅርብ በሆኑ ወጣቶችና ተማሪዎች ዘንድ ቫላንታይን ቀንን ማክበር ተለምዷል:: በኢትዮጵያም ቫላንታይን ቀንን ቀይ በመልበስ ቀይ አበባና ስጦታ በመለዋወጥ መከበር

ከጀመረ ሰንብቷል:: በ18ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ

በጓደኛሞችና በወዳጆች መካከል በእጅ የተጻፈ የፍቅር መግለጫ መለዋወጥ የተለመደ ነበር:: በ19ኛው ክፍለ ዘመን ከሕትመት ቴክኖሎጂ መምጣት ጋር ተያይዞ፤ በማሽን በተተየቡ ጽሑፎች የፍቅር መልዕክቶችን ወደመለዋወጥ ተሸጋገረ:: ስሜትን በቃላት ከመግለጽ ባሻገርም በካርዶች ላይ በታተሙ ጽሑፎች መግለጹ ተመራጭ እየሆነ መጣ:: 85 በመቶ የሚሆኑ የቫላንታይን ስጦታዎችን የሚገዙትም ሴቶች ናቸው:: በ2008 ላይ

በአሜሪካ የተደረገ ጥናትን ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው፣ በአሜሪካ ስምንት ሚሊዮን የሚጠጉ ሴቶች የቫላንታይን ስጦታ ገዝተው ለራሳቸው ያበረክታሉ:: ይህንንም የሚያደርጉት ብቸኝነት እንዳይሰማቸው ነው:: በቫላንታይን ቀን አብዛኛው የሚበረከቱ ስጦታዎች ቀይ አበባ፣ ሪቫን፣ ሻማ ቸኮሌት፣ የአንገት ጌጥና ፖስት ካርዶች ናቸው:: ‹‹እወድሻለሁ›› ወይም ‹‹እወድሃለሁ›› የሚሉ ቃላት የተጻፉባቸው ፖስት ካርዶች ትልቁን ሥፍራ ይይዛሉ::

የቫላንታይን ቀን ስጦታዎች

ስለቫላንታይን ከሚነገሩ

በ1980ዎቹ ዶክተሮች ልባቸው ለተሰበረ ታካሚዎቻቸው ቸኮሌት እንዲመገቡ ይመክሩ ነበር:: ይህንን የሚያደርጉትም ቸኮሌት እንዲፅናኑ ያደርጋል በማለት ነበር:: በአሁኑ ጊዜም ብዙ ልባቸው የተሰበረ ሴቶች ቸኮሌት በተሰጣቸው ጊዜ ይፅናናሉ:: ምቾትም ይሰማቸዋል::

ከፍተኛው የቫላይንታይን ካርድ ስጦታ የሚደርሳቸው ለመምህራን ነው:: ሕፃናት፣ እናቶች፣ ሚስቶች፣ ውሾችና ድመቶች እንደቅደም ተከተላቸው በብዛት ይደርሳቸዋል::

ዘጠኝ ሚሊዮን የሚጠጉ የቤት እንስሳት ባለቤቶች በቫላንታይን ቀን ስጦታ ይገዛሉ::

በቫላንታይን ቀን ወንዶች ከሴቶች በእጥፍ ለስጦታ ወጪ ያወጣሉ:: በዚህ ዓመት አንድ ወንድ ለቫላንታይን ስጦታ መግዣ ከ150 ዶላር በላይ ያወጣል ተብሎ ተገምቷል::

የታይላንድ ኮረዶች የሚያረግዙበት የቫላንታይን ቀን

የቫላንታይን ወይም የፍቅረኛሞች ቀን በየዓመቱ የሚከበርበት የካቲት 7 (ፌብሬዋሪ 14) የታይላንድ ወጣቶች ልቅ ወሲብ የሚፈጽሙበት ነው:: ከየካቲት 4 እስከ 9 ባለው የቫላንታይን ሳምንት የታይላንድ ታዳጊ ወጣቶች ወሲብን ይፈጽማሉ:: ብዙ ታዳጊ ሴቶችም ያረግዛሉ:: ይህ ደግሞ የታይላንድን መንግሥት አስጨንቆታል::

እ.ኤ.አ በ2008ቱ ቫላንታይን በዓል የታይላንድ ታዳጊ ወጣቶች ወሲብ እንዳይፈጽሙ ሲለምን የነበረው የአገሪቱ ፖሊስ፣ በ2013 ለሚከበረው በዓል ከወሲብ ጋር የተያያዙ ወንጀሎች እንዳይፈጸሙ ፖሊስ በንቃት እንዲጠብቅ አስጠንቅቋል::

በታይላንድ በቫላንታይን ቀን በተለይ ሴቶች ላላስፈላጊ ወሲብ እንደሚጋለጡ ከዚህ ባለፈም የሕገወጥ ዝውውርና የወንጀል ሰለባ እንደሚሆኑ ኤንኤንቲ ዘግቧል::

ዝ ን ቅ

በታማኝነት ለመኖር የሚረዳዎት መመሪያዎችየውሳኔ ሰው ይሁኑ፡- በሕይወትዎ ውስጥ ለአንድ

ነገር አለመወሰን የሚያሳጣዎት ብዙ ነገር አለ:: በዚህች ምድር ላይ ሕይወት ይበልጥ መራራ የምትሆንብዎት የውሳኔ ሰው ካልሆኑ ብቻ ነው:: ያለመወሰን ትልቁ ምክንያት በፍርሃት መያዝ ነው:: አእምሮ በጥርጣሬና በጭንቀት ሲማስን በቀላሉ ለብዙ የስህተት ውሳኔዎች በሮቹን መክፈት ይጀምራል::

ሁልጊዜም ቢሆን በመንገዱ መሃል ላይ መቆም አደጋዎች እንዲከሰቱ ያደርጋል:: የማይወስን ሰው በሕይወቱ ሁሉም አቅጣጫዎች ውስጥ አለመረጋጋት ዘው ብለው ይገባሉ:: በምኞት ባህር ውስጥ የሚሰጥሙ ያለውሳኔ መሃል ላይ የቆሙ ሰዎች ናቸው:: ለራስዎ አስፈላጊ የሆነውን ነገር ካልወሰኑ ሁልጊዜ ለሌሎች አስፈላጊ የሆነውን ነገር ይሠራሉ:: ይህም የራስዎን ሳይሆን የሰውን ኑሮ መኖር ነው::

በሕይወት ውስጥ አንድ ዕርምጃ ካልተንቀሳቀሱ ንዴት የግል ሀብትዎ፣ ደስታ ደግሞ ዘበት ትሆንብዎታለች:: ተኝቶ ከሚውል ብርቱ ጥቂት ብቻ የሚንቀሳቀስ ገልቱ ይሻላል:: ሁልጊዜ ሞትን እያሰቡ ከመጨነቅ የማይሞት ተግባርን ስለመፈጸም ማሰብ ትልቅ ዋጋ እንዳለው ይረዱ::

ዛሬን በደንብ ይኑሩ፡- ትናንት የረፈደ ጊዜ ነው፤ ዛሬን በደንብ ይኑሩ፤ ከዛሬ የተሻለ ጊዜ የለምና፤ በልብዎ የዛሬዋ ዕለት የዓመቱ ምርጥ ዕለት እንደሆነች ያስቡ::

ከትናንት ጸጸት ከተፋቱ ከዛሬ ጋር ተጋብተው የሚያምሩ ነገዎችን መውለድ ይችላሉ:: ዛሬ በጥረትዎ ብቻ ልትዋብ እንደምትችል ይወቁ:: ዛሬ ያልሰጡት ነገር በፍጹም ለነገ ሊሰጥዎት አይቻልምና::

ያለፉት ነገሮች በዛሬ ሕይወትዎ ላይ ተፅዕኖ መፍጠር የለባቸውም:: እነዚህ ነገሮች ሕይወትዎ ላይ ጐጂ ተፅዕኖ አላቸው:: ሁልጊዜ ወዳለፈው ነገር የሚመለከቱ ከሆነ ወደፊት ለማየት አይቻልዎትም::

ዛሬን በደንብ መኖር ለነገ ዕድሎችም ሆነ መሰናክሎች ዝግጁ ያደርግዎታል:: ያለፈውን ቀን በማድነቅ የዛሬውን ቀን አያባክኑ:: ያማረ ነገን ለመፍጠር የተዋበ ዛሬን መኖር የግድ ነውና::

ለፍትሕና ለነጻነት መስዋዕትነት ይክፈሉ፡- ፍትሕና ነፃነት፣ ሰላምና ፍቅር እንደ ድርና ማግ የተሳሰሩ መንታ እውነቶች ናቸው:: ፍትሕ የነፃነት ጥላ ሲሆን ነፃነት ደግሞ የሰላም አካል ነው:: በፍትሕ የሚዘጋጀው ዕቅድ በነፃነትና በፍቅር ሥራ ላይ ይውላል::

ያለ ፍትሕ ነፃነትን አናስተውልም:: ያለ ሰላምና ፍቅርም ፍትሕና ነጻነት ተፈላጊነትን ያጣሉ:: ፍትሕ በጠፋበት ቦታ ነፃነት ሁልጊዜ ታነባለች፤ ያለ ፍትሕ ነፃነት በራሱ ነፃ አይደለምና::

እውነትን መፈለግ፣ መናገርና ማድረግ የነፍሳችን ጥልቅ መሻት ነው:: ሁልጊዜ በእውነትና በሐሰት፣ በፍትሕና በኢፍትሐዊነት፣ በመልካምና በክፉ፣ በታማኝነትና በክህደት፣ በጥንካሬና በስንፍና መካከል እልህ አስጨራሽና መስዋዕትነትን የሚጠይቅ ትግል አለ:: ሰለሆነም ለታመኑበት እውነት ሲሉ ለፍትሕና ለነፃነት መስዋዕትነትን መክፈል ታላቅነት ነው::

ለፍትሕ መሞት ለእውነት መኖር ነው::ዳንኤል ዓለሙ (የምሕረት ልጅ) ‹‹ራስን የመለወጥ

ምሥጢር›› (2005)

ውበትውበት የጊዜ ድምበር የሌለው ቋንቋ ነው፤

ለሰው ልጅ ሁሉ የወል የሆነ:: ውበት ነፍሶቻችን ብቻ ጠንቅቀው የሚረዱቱ፣ አብረው የሚደሰቱበቱ’ና በ’ሱም እየተኮተኮቱ የሚያድጉበቱ ምስጢር ነው:: ኅሊናችንም የሆነ እንደሁ በ’ሱ ፊት ግራ ይጋባል፤ በቃላት ልንገልጸው’ና ሥጋ ወደሙ ልናላብሰው ብንሞክርም ይሳነናል፤ በተመልካቹ ልዩ ስሜቶችና በታይው ገሃድነት መሀል የሚናብል ካ’ይን የተከለለ ጎርፍ ነው:: የ’ውኑ ገሃዳዊው ውበት የሚመነጨው ከነፍስ ቅድስተ ቅዱሳን እምብርት ከሚፈነጥቀው ከሰውነት አልፎ ተርፎም ከሚያበራው ጮራ ነው:: ከከርሰ ምድር ማሕፀን ውስጥ ሒወት ወጥታ፣ ለአበባ መልክ’ና ማ’ዛ እንደምትሰጠው ዓይነት:

:የአረጋዊ ዕንባበተሸበሸቡት የአረጋዊ ጉንጮች ላይ አንዲት

የምታብለጨልጭ የእንባ ዛላ ካ’ንድ ጎልማሳ ዓይኖች ከሚፈስሱ የእንባ ዘለላዎች ሁሉ ይልቅ ነፍስን በይበልጥ ትጎዳለች::

በጎልማሳነት ዘመን በገፍ የሚነባው እንባ የሚጎርፈው ከሞላች ልብ ጥጋጥግ ሲሆን፣ ካ’ዛውንት ሰው የሚመነጨው እንባ ግን ካ’ይንብሌን የሚፈስ የሒወት እንጥፍጣፊ ነው - የተዳከመ ሰውነት ፍድፋጅ:: በጎልማሳ ዓይኖች ያሉ እንባዎች በጽጌረዳ ቅጠሎች ላይ እንዳሉ የጤዛ ጠብታዎች ዓይነት ነው፤ ነገር ግን ዘመን በገፋ ሰው ፊት ላይ ያሉ እንባዎች የሒወት ክረምት ሲብት የሚነፍሰው ነፋስ እንደሚጥላቸው የወየቡ የመፀው ቅጠሎች ዓይነት ናቸው::

ካህሊል ጂብራን ‹‹የተሰበሩ ክንፎች›› (1999)

እኔ የሞትኩ ዕለትክሪስቲና ሮዜቲ (1830-1894)ስድ ትርጉም በከበደ ዳግማዊ

ፍቅሬ ሆይ ወዳጄ፣ እኔ እንደሞትኩኝ፤

ልብን የሚነካ ሙሾ አታውርድልኝ፤

ጽጌረዳም ይቅር ወደአናቴ መትከል፤

አርዘ ሊባኖስም ጥላው የሚያረካ፤ አስፈላጊም አይደል::

እንደ ለምለሙ ሳር ከበላዩ ብቀል፤

ካፍያ ያጤዘበት፤ ያለበሰው ጤዛ፤

ከፈለግህ አስታውሰኝ ወይ እርሳኝ አለዛ::

እኔ እንደሁ አበቃሁ ጥላውን አላየው፤

ዝናሙ እያረጥበኝ እኔም አልሰማው፤

ወፏም ብትዘፍን የሚያስለቅስ ዜማ፤

ስቃይ እንዳለባት ልብን የሚያሟማ፤

እኔ ግድም የለኝ ሁሉንም አልሰማ፤

ሳልም እኖራለሁ በዝያ በጭለማ በማይጠልቀው ጀምበር

(የጉም አጋፋሪ) በማይነጋው ሌሊት፤ ሁሉም እንዳልነበር::

ከሆነልኝማ እኔ አስታውሳለሁ፤

ታልሆነም ይቀራል እኔም እረሳለሁ::

ለሁሉም የሚል ስያሜ የተሰጠው የውኃ፣ የስልክና የኤሌክትሪክ ኃይል የአገልግሎት ክፍያ (የአዲሱ የቢል አከፋፈል) ሰልፍ ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. ፎቶ በሪፖርተር/በናሆም ተስፋዬ

Page 76: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 28 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

የእርስ በርሱን ጦርነት አቁሞ ለልማት እንዲተጋ ማሰባቸው ለሁላችንም ምክር ሊሆን ይችላል:: አገራችን ዘላለማዊት ስትሆን ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ግን ተለዋዋጭ ነው:: ዘርም፣ ቋንቋም ተለዋዋጭ ነው:: ትውልድ አልፎም ትውልድ ይተካል:: ስለሆነም የጥላቻን መርዝ አስወግደን የተጀመረውን የልማት ለውጥ ማካሄድ ተቃውሞ ቢኖረንም በአግባቡ እያቀረብን ለማስተካከል የበኩላችንን አዎንታዊ ሚና መጫወት ይጠበቅብናል::

ፈትሑላህ ጉለን የተባሉ ቱርካዊ የመቻቻልና በሰላም አብሮ የመኖር መሐንዲስ «የነፍሳችን ሐውልት» በሚለው መጽሐፋቸው ውስጥ እንዳስቀመጡትም «ፈጣሪ የምድር ወራሽነትን ለአንድ የተወሰነ ነገድ፣ ጎሳ፣ አገር፣ ወይም ዘር ለመስጠት ቃል አልገባም:: ወራሾቹ ባሪያዎቹ፤ በአስተሳሰባቸውም ሆነ በእምነታቸው ትክክል የሆኑ፣ የአንድነት፣ የስምምነት፣ የአብሮነትና የወንድማማችነት አመለካከትን የሚያስተምሩ፣ በተግባር የሚገልጹና አጥብቀው የሚይዙ፣ ያሉበትን ዘመን የሚረዱ፣ በሳይንስና በዕውቀት የበለፀጉ፣ የዚህን ዓለምና የሚቀጥለውን ዓለም ሚዛን ጠብቀው የሚኖሩ... ናቸው፤» ካሉ በኋላ «በዚህ ያልታደለ ጊዜ የአስተዳደርና የአስተዳዳሪዎች ድክመት በግልፅ ለመናገር ልቦናን የመስበር (የሚያሳዝን) ነው፤፡» ሲሉ የሚከተለውን አስተያየት «የነፍሳችን ሐውልት» በተሰኘው መጽሐፋቸው ይተነትናሉ::

ፈትሑላህ እንዳሉት፡- እውነቱም በምንም መንገድ ይቅርታ ሊደረግለት የማይገባ የታሪክ ስህተት መፈጸማችን ነው:: በዚህም ምክንያት «በጭራሽ መፍታት በማይቻል ነገር ግን ዋጋ ቢስ በሆነ ድር» ተተብትበን እየታገልን እንገኛለን:: ሰው ሠራሽ፣ አዲስ ፈጠራ የሆነ ሥርዓት በሕዝብ ላይ ተጭኗል:: በእርሾ የተነፋ ጡብ የመሰለና ቀጣይነት የሌለው እሴት ያለው፣ መርሕ የተገነባ ታላቅ መንግሥት እንደገና ተነድፏል:: በዚህም ሳቢያ ታሪክ፣ የማኅበረሰቡ ማኅበርና የጥንታውያን አባቶችና ብሔራዊ ባህልና ቅርስ ተጣሉ፣ ተዋረዱ፣ ተሰደቡ፣ ተጥላሉ፣ መሳቂያ መሳለቂያ ሆኑ:: ለሺሕ ዓመታት የአስተሳሰባችንን ሥርዓት ከሚቃወሙና አርቲቡርቲና እንግዳ ከሆነ አሳባቸው፣ ሃይማኖታዊ ካልሆነ፣ የተቀደሱ ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን ከሚንቅ አስተሳሰባቸውና ነውረኛ ከሆነ አገላለጣቸው ጋር ተደባልቆ ወደ አገራችን ገባ:: በዝርውና በግጥም ሥነ ጽሑፍ እንደዚህ ያለውን (አርቲቡርቲ ነገር) የሚያሞጋግሱና ከፍከፍ የሚያደርጉ የሽልማትና የክብር ዓይነት ተርከፈከፈላቸው:: በፍጹም የዓለም ስህተት፣ ትክክል ባልሆነ ቁልምጫ ስህተት ሌሎችን አወገዙ፣ እንዲሁም ጨቆኑ:: በስሜት፣ በአመለካከትና በሞራል ለመበልፀግ እስከ ኮሚኒዝም ተጓዙ::

እንደ ሶሻሊዝምና ኮሚኒዝም ያሉ ርዕዮተ ዓለሞች ባለወቅት በነበሩበት ጊዜ በደርዘን የሚቆጠሩ በክህደት (ሃይማኖት) የተነሰነከሉና ብቃት የሌላቸው፣ እራሳቸውን ጭምር የሚጠራጠሩ፣ በታወቁ ሰዎች፣ በሌሎች ቀኖናዊ አመለካከትና ርዕዮተ ዓለም በስተጀርባ ተደብቀው ዘወትር ለመኖር የሚሹ ሰዎች ጋጠወጥ በሆነ መንገድ ሃይማኖትን ለማጥቃት፣ ቅዱሳን ተግባራትን ለማስቆም ጥረት ያደርጉ እንደነበረ እስካሁን ድረስም አስታውሰዋለሁ::

በአሁኑ ጊዜም እነዚያን በእጅጉ በሚመስሉ ሰዎች፣ የወንጀል ቡድኖች (ወሮ በሎች) እጅግ አስቀያሚ፣ አስደንጋጭ፣ በእጅጉ አስፈሪና አዋራጅ እንዲሁም ቅሌታም የሆነ ዘመቻ ሲያካሂዱ እንመለከታለን:: አሁንም ሕገወጥ በሆነ የርዕዮተ ዓለም አመለካከት ላይ ተመሥርተውና በዚያው አመለካከት እየታገዙ የሃይማኖት ሰዎችንና ሃይማኖታዊ ሕይወትን ዝም ለማሰኘት የጠላትነት ስሜታቸውን፣ ተንኮላቸውን፣ ጭካኔያቸውን፣ ባልኩት አይመልሰኝ ባይነታቸውን፣ መራር የጠላትነት ስሜታቸውን፣ እንዲሁም በሌሎች ክፉ አመለካከቶች በመላው ኃይላቸው የጥረት ጦርነት እያደረጉ ነው::

በዚህ ረገድ፣ ጥረትና የማያቋርጥ የዕድገት ሒደት መሪ ቃላችን፣ የጠለቀ የእምነት ዕውቀትና ሐቅ የጥንካሬ ምንጫችን ነው:: ከበር ወደ በር እንድንንከራተት የሚያደርጉን፣ ከእምነተ ቢስነትና ከሞራል ቢስነት መድኃኒትና መፍትሔ የሚፈልጉልን ምንጊዜም ስህተት ናቸው:: ምንጊዜም በአቋማችን ፀንተን እስከኖርንና ለፈጣሪ ራሳችንን በሙሉ ልባችን አስገዝተን እስከኖርን፣ ብዙ የደከምንላትን አገራችንን፣ ሕዝባችንን፣ ምድራችንን እስከ መረጥን ድረስ ምንጊዜም ክብርንና በክብር መቆየትን እናገኛለን:: አማራጩን በሚመለከት ማብራራት የሚያስፈልግ አይመስለኝም::

ለሁሉም የዕውቀት መስኮች ማለትም አርቆ አስተዋይነት፣ በጥበበኛነት፣ በባህል፣ በመንፈሳዊ ዕውቀት፣ በወኔያቸው፣ በመንፈሳዊ ቅዱስነት ሙላታቸውና ብልጽግናቸው፣ የሚያክሙን መንፈሳዊ ሐኪሞች ያስፈልጉናል:: እንደዚህ ወይም እንደዚያ ያለ የተለየ ዓይነት ወይም ችሎታ ያለው ብለን የምንመርጠው ሳይሆን አጠቃላይ ግንዛቤ ያለውን

ነው:: አንጎል በቅርቡም ሆነ ከእርሱ ርቀው፣ ከጥቃቅኖቹም

ሆነ ከትላልቁ ከሚገኙ የሰውነታችን መላ ሴሎች ጋር በነርቭ ፀጉሮች አማካይነት እንደሚገናኘው ሁሉ፣ እንደዚህ ያሉት የአንጎል ካድሬዎች ከመላው የአካላችን ግዛት ውስጥ ከሚገኙ አቶሞች፣ ሞለኪውሎች፣ ቅንጣቶች ጋር እንደሚገናኙት፣ እንደሚያገናኙትና አንዱን ከሌላው ጋር እንደሚያስተሳስሩት ሁሉ የመንፈስና የአስፈላጊው እውነት ሐኪሞችም ሁሉንም ኅብረተሰብ አካል ይደርሳሉ:: እጆቻቸው በዋናዎቹ ተቋማት ላይና ውስጥ ያርፋሉ:: በጨዋነት ስሜትም፣ ካለፈው ጊዜ የመጣና በአሁኑ ጊዜ ጥልቀት ያገኘ እንዲሁም ወደፊት ሊዘረጋ የሚችል ከመንፈስና ከእውነት አንዳች ነገር በሕይወት ላለው ፍጡር ሁሉ መልዕክት ያስተላልፋሉ::

አስተሳሰባችንን፣ ስሜታችንን፣ መንገዳችንን፣ ፍልስፍናችንን እንደገና ሕያው እስካደረግን ድረስ የራሳችንን ሰማያዊና የማይሞት ስልታችንን አሰባስበን ማምጣት የሚያስችሉን ናቸው:: ለዚህም ነው እንደምንመለከተው፣ የምንጓዝባቸውን ጎዳናዎች በሙሉ ከሁሉ አስቀድመን መፈተሽ፣ መመርመር፣ እንደገናም አጠናክረን መሥራት ያለብን:: ለዳግማዊ ሕዳሴያችን አርአያ፣ ምሳሌ፣ መነሻና፣ መለኪያ የሚሆኑን ወኔያችን፣ ቆራጥነታችን፣ የሚያነሳሳ መንፈሳችን፣ በሃይማኖት ረገድ ፍሬያማ መሆናችንን፣ (ያለፈውን ታሪካችንን) ለማረጋገጥ የሚያስችል ከባቢ ሁኔታ፣ ጽናታችን፣ በመካከላችን ውስጥ የሚገኘው ስበታችን፣ ኮስታራንታችን ምክንያት በማቅረብና በነገረ ጥበብ ችሎታችን፣ የማንናወጽ መሆናችን ለራሳችን ነጻነት የሚያጎናጽፈን ሰብዓዊ ሩህሩህነታችን ናቸው:: የፍልስፍና ጥልቀት፣ የማጣራት፣ የማሻሻል፣ ወደፊት የማራመድ፣ በኪነ ጥበብና በፍልስፍናችን ውስጥ የሚገኝ በጥልቅ እሳቤ የተሞላ አመለካከታችን፣ ይህም ሁሉ ከዋናው ማዕከል ጥራት ያለውና በአሠራር ሊያስኬድ በሚችል አስተሳሰብ ላይ የተመሠረተና በራዕይ የተነሳሳ ሊሆን ይገባል:: የትምህርት አርበኝነት

በጥቂት አንደኛ ደረጃ፣ ሁለተኛ ደረጃና በአንድ ዩኒቨርሲቲ ከ30 ዓመታት ላላነሰ ጊዜ ቆይተናል:: ዛሬ ግን የተፈለገውን ያህል ባይስፋፋም በርካታ ትምህርት ቤቶች ተከፍተዋል:: ከ30 በላይ ዩኒቨርሲቲዎች ከተቋቋሙ ገና አሥር ዓመታት አልሞሉም:: በነዚህ ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩና የሚሠሩም ለብለብ ባለ ሥልጠናና ዕውቀትም ቢሆን ተሞልተዋል:: እውነቱን ለመካድ ካልፈለግን በስተቀር በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የትምህርት አርበኝነት ዘመቻ አስተማሪዎችና ተማሪዎች እኩል የስድስተኛና የስምንተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ይወስዱ ነበር:: አብረውም የሚያጠኑ ነበሩ:: ነገሩ ጠንከር ሲልም ተማሪዎቻቸው የሚያስጠኗቸው አስተማሪዎች ነበሩ:: ይህም ሆኖ «የዛሬ ተማሪ ... ?» በማለት ከማጥላላት ጀምሮ ሌሎች አስፀያፊ ነገሮች ሲናገሩ የሚሰሙ አሉ:: በመሠረቱ ይህን የሚናገሩ ሰዎች ራሳቸውን ከአዲሱ ትውልድ ከፍ አድርጎ ለማስቀመጥ ነው:: ነገር ግን ደደቡ ሁሉ እንደዚያ ሲል ያሳዝናል:: ልጆቹ ሳይሆኑ የልጅ ልጆቹ አንዳች መሠረታዊ ዕውቀት ሲጠይቁት የማይመልስ ከሆነ ደግሞ ያሳፍራል:: እውነቱን ለመናገር ለመሆኑ ከኛ የሚበልጡ ወጣት ምሁራን የሉም? የዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ በዕድሜ ልጆቹ ከሚሆኑ ልጆች ጋር ተምሯል፣ አስተምረውታልም:: በሁለቱም ወቅቶች ወርቅ ብቻ ሳይሆን አልማዝ የሆኑ ልጆች እንዳሉ ተመልክቷል:: ስለዚህ በጅምላ መናገርን አስወግደን ወርቅና አልማዞቻችንን ማበረታት ይኖርብናል::

እርግጥ ነው የአሁኑ ትምህርቱ ጥራት እንደተፈለገው ላይሆን ይችላል:: የምዕራባውያንና የምሥራቃውያን ተፅዕኖ ሊኖርበት ይችላል:: የሞራል ድቀትና የሥነ ምግባር እንዲሁም የግብረ ገብነት እሴት በአስፈላጊው መጠን ላይኖረው ይችላል:: ነገር ግን ዳር ሆነን የምንነቅፈውን ጨምሮ ሁላችንም በትምህርቱ ጥራት የምንረባረብ የትምህርት አርበኞች ብንሆን በቀላሉ የማይገመት ለውጥ ልናመጣ እንችላለን:: ለመሆኑ ዛሬ ምንም ዓይነት ልዩነት ይኑረን ምን ይህ ጊዜያዊ ልዩነት ሳይገድበን ተቻችለን፣ ተከባብረን፣ ተፋቅረን የትምህርት አርበኞች ሆነን ካልሠራን የኛንም ጨምሮ የነገውና የከነገ ወዲያው ትውልድ እንደሚጎዳ ማሰብ ይሳነናል? ወይስ ይህ ሥርዓት ይውደቅ እንጅ ወደ ምዕራብ አገሮች የተሰደዱትና ከኢትዮጵያዊ ባህል ጋር የተራራቁት ወገኖቻችንን አምጥተን ክፍቱን ቦታ እንሞላበታለን ብለን እናስባለን? እንዲያው ለመሆኑ ዕውቀታችንን (ከኖረን) ካልጨመርንበት በስተቀር የአሁኑን ትምህርት ለመንቀፍ የሚያስችለን የኛ ሀቅ ምንድነው?

አባ ቤኒዲክት 16ኛ «የሀቅ ግንዛቤ ጥርጣሬ ላይ መውደቁ እርግጥ ነው:: በእርግጥም ሀቅ ከሚገባው በላይ ተወግዟል:: በምትኩም አለመቻቻልና ጭካኔ በሀቅ ስም ቀርበው ሲተገበሩ ኖረዋል:: ስለዚህም ሰዎች ‹ይህ ሀቅ ነው› የሚለውን ዓረፍተ ነገር ሲሰሙ ወይም ‹እኔ ሀቅ አለኝ› በማለት ሲናገሩ በሚሰሙበት ጊዜ ሥጋት ያድርባቸዋል:: ሀቅ

ብትይዘን እንጅ እኛ ይዘናት አናውቅም:: ስለሆነም አንድ ሰው እውነት አለኝ ብሎ ሲናገር መጠንቀቅ እንዳለበት የማያጠያይቀውም ለዚህ ነው:: ሀቅን ልንደርስበት አንችልም ብሎ መተው ደግሞ አፍራሽ ነገር ነው:: አዎን ሰው ሀቅን መሻት አለበት:: ሀቅን ማግኘትም ይችላል ብሎ በድፍረት ለመናገር ወኔው ሊኖረው ይገባል:: ሀቅን ለማብራራትም ሆነ ሀቅ አለመሆኑን ለማሳየት መለካት የሚያስችል መለኪያ እንደሚያስፈልገው ሳይናገሩት የሚሄድ ነገር ነው:: በመቻቻልም መደገፍ ይኖርበታል:: የሰውን ልጅ ታላቅ ያደረገው ዝልቅና ያገኙ እሴቶችም በሀቅ እንደሆነ ያመለክታሉ:: ለዚህም ነው ሰብዕና ሀቅን መገንዘብ ያለባትና የሕይወት መመሪያ አድርጋ በመውሰድ እንደገና መረዳትና መተግበር የሚገባትም ለዚህ ነው:: ሀቅ በአመፅ ሳይሆን በራሷ ኃይል ዳግም ትገዛለች:: የዮሐንስ ወንጌል ዋነኛ መልዕክት የሚያጠነጥነውም ኢየሱስ ከጲላጦስ ፊት ሲቀርብ ሀቅ መሆኑንና የሀቅ ምስክር እንደሆነ በፍቅር ስሜት ነበር፤» ይሉናል::

ከጥንት ጀምሮ ሲያብሰለስለን የነበረው የዓባይ አለመገደብ ጉዳይ ብቻ አልነበረም:: እኛ የአክሱም ጥበብ፣ የላሊበላ ጥበብ፣ የአዳዲ ማርያም ጥበብ ባለቤቶች፣ እኛ የዘርዓ ያዕቆብ ፍልስፍና ባለቤቶች፣ እኛ የይሃ፣ የጎንደር፣ የእንፍራንዝ፣ የደንቀዝ ጥበብ ባለቤቶች ብዙ ሥልጣኔያችን፣ ብዙ ዕውቀታችን፣ ብዙ ጥበባችን፣ ብዙ ፍልስፍናችን ዛሬም ከተቀበረበት ጉድጓድ ሆኖ እንድናወጣው የጥሪ ጩኸት እያሰማን ነው::

የልማት አርበኝነትን በሚመለከት በርካታ ምሁራን ትተውልን ያለፉት አስተምህሮት በእጅጉ ብዙ ነው፤ «በዚች ዓለም ላይ ልዩነት የሌለበትን አንድነት ለማምጣት የሙጥኝ ከማለት ይልቅ ልዩነት ቢኖርም አንድ ለመሆን በመፈልግ አንድነት ሊመጣ ይችላል:: ልዩነትን ለማጥፋት መሞከር ፍፁም የማይቻል ነገር ነው:: በሕይወት ስንኖር ሰላም የማስፈን ምሥጢርም ሰላም የሚያደፈርሱ ነገሮችን በመቻል ነው፤» ከሚሉን መውላና ዋሕዱዲን ኻን የምንማረው አንዱ መሠረታዊ ቁም ነገር የአመለካከት ልዩነት ቢኖረንም ልዩነቶቻችን የልማት አርበኝነታችንን ማስፋፋት እንጅ እኛ ከልጆቻችን የበለጥን መሆናችንን ለማሳየት ልጆቻችንና የልጅ ልጆቻችን ተስፋ እንዲቆጥሩ ማድረግ ከቶ አይገባንም::

የትምህርት አርበኝነትን ማስፋፋት ማለት የማኅበራዊ ኑሮ፣ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ፣ የባህል፣ የሃይማኖት ተመራማሪ አርበኞችን ማለትም በልዩ ልዩ ምክንያቶች አገሪቱን ሊገጥሟት የሚችሉ አርበኞችን ዝግጁ ማድረግ ነው::የሲቪል ሰርቪስ አርበኞች

እርግጥ ነው የሚያስፈልገን አርበኛ ዓይነቱና ብዛቱ ቁጥር የለውም:: ነገር ግን በእጅ ያለው «የሲቪል ሰርቪስ አርበኛ» ጉዳይ በእጅጉ አስፈላጊ ነው:: ስለሲቪል ሰርቪስ አርበኝነት ስንነጋገር ከሁሉ አስቀድሞ መንግሥት ደረቁን ሀቅ መቀበል አለበት:: ይህም ሀቅ በቢሮክራቶች በአያሌው መጭበርበሩ፣ መታለሉና ከፍተኛ ጊዜ ገንዘብና ዕውቀት መክሰሩ ነው:: እስቲ እያንዳንዱ የሲቪል ሰርቪስ መሥሪያ ቤት፣ በሲቪል ሰርቪስ ለማሰልጠን ምን ያህል ጊዜ፣ ገንዘብና ዕውቀት አፈሰሰ? ከዚህስ ምን ውጤት ተገኘ? ሌላውን እንተወውና በአርአያነት የተጠቀሱት ድርጅቶች ቤት ከማፍረስ ከፍተኛ ወጭ ከማውጣታቸው በስተቀር ምን ያህል ተለውጠዋል? ሰዎቹ በመንፈስ ካልተለወጡ ሥራውን ቤቱ ሊሠራው ይችላል? እዚህ ላይ አንድ ተስማሚ ምሳሌ መስጠት የሚያስፈልግ ይመስላል::

የአንድ የምርምር ኢንስቲትዩት ሰፊ ግቢውን በድንጋይ ግጥም አድርጎ ያሠራል:: የሠራው አናፂ ድርጅትም አርኪ ሥራ በማከናወኑ ይደሰታል:: ሆኖም ሥራውን አጠናቆ ሲወጣ ዕቃውን ይቆጥራል:: በዚህ ጊዜ ከጊዜያዊ መጋዘኑ ዕቃ መጥፋቱን ይረዳል:: ለማግኘት ያደረገው ጥረትም ሳይሳካ ይቀራል:: በሽኝቱ ጊዜ ጥሩ የግንብ አጥር በመሥራቱ ሲመሰገን «እርግጥ ነው ጥሩ አጥር ሠርተናል:: ነገር ግን ሌባውን ውስጥ አድርገን በመሥራታችን እናዝናለን፤» የሚል ምላሽ ሰጠ::

ለመሆኑ መሥራት ከሚችሉት በታች እያቀዱ (ዕቅድ የሚባል ነገር ስላላቸው) ከመቶና ከመቶ በላይ አተረፍን ብለው የሚናገሩ ሥራ አስኪያጆች ያሉባት አገራችን እንዴት ነው ሲቪል ሰርቪሱ ሊሻሻል የሚችለው:: ለእያንዳንዱ የሥራ አስኪያጅ ተጠሪ ሥራ አውጥቶ የማይሰጥ ሥራ አስኪያጅ፣ ያወጣው ዕቅድ ለበታች ሠራተኞች ተተንትኖ መስጠቱን የማያውቅ ሥራ አስኪያጅ፣ ያወጣው ዕቅድ በየቀኑ፣ በየሳምንቱ፣ በየወሩ፣ በየሩብ ዓመቱና በየዓመቱ የማይከታተል ሥራ አስኪያጅ፣ ይህ ሳይሆን ቀርቶ የራሱን ቤት ግንባታ ወይም ሌላ ድርጅት ግንባታ ሲከታተል የሚውል ሥራ አስኪያጅ፣ መንግሥት በሀቀኛ መንገድ እንዲሸጥ የሰጠውን ንብረት በጠራራ ፀሐይ በኮሚሽን ወይም በሌላ መንገድ የሚቸበችብ፣ መንግሥት በነፃ ለባለ ንብረቱ እንዲያስተላልፍ የሰጠውን «እንደ ምንም ዘዴ ፈልጌ አስተላልፍልሃለሁ፤ ለዚህ ግን ዋጋየን ትከፍለኛለህ» የሚል፣ የጨረታ ሰነዶችን «ምንና

ምን» በማድረግ ያለ አግባብ የሚበለፅግ ሥራ አስኪያጅ ባለባት አገራችን እንዴት ነው ሲቪል ሰርቪሱ በመልካም ሁኔታ ወይም ሌላ ቅጽል እየተሰጠው የሚገለጠው? የነሱ አጫፋሪ «ካድሬ ተብየዎች» በሚያስተላልፉት የሀሰት ወሬ አገር ከቶ እንደማይገነባ በግልፅ መታወቅ አለበት:: ኢሕአዴግን እውን ካደረጉ ባለሥልጣኖችኮ ዛሬም የሚርባቸውና የሚጠማቸው፣ ዛሬም የራሳቸው የሆነ መጠለያ የሌላቸው አሉ:: እነሱስ ዛሬም አላነጠነጡም:: ወዛቸውም ችፍ አላለም:: ቤታቸው ባለ እንፋሎት መታጠቢያ የለም::

ለመሆኑ የአገራችን የሙስናና ሥነ ምግባር ጉዳይ በምን ሁኔታ ላይ ነው? ንብረቱን ያስመዘገበው ቱጃር የመንግሥት ባለሥልጣንን ከየት እንዳመጣው ለመጠየቅ የሚችል አቅም አለው? በመንግሥት ባለሥልጣን ቱጃሩ ስም ብቻ ሳይሆን በእናቱ፣ በአባቱ፣ በባለቤቱ፣ በልጆቹ፣ ምናልባትም የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እንዳሉት «በውሻው» ያስመዘገበው ሀብት ይኖር እንደሆነስ ቢያንስ ከጎረቤቱ በመነሳት ለማየት ሞክሯል?

የራሱ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትስ ምናልባት መሥሪያ ቤቱ ሩቅ ካልሆነበት እስኪ ከራሱ ቢሮ ጀምሮ ወደ አራት ኪሎ ወዳሉት የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ሁሉ ጎራ ይበልና በስውር ያጥና ጉዳዩ ከቤተ መንግሥቱ በራቀ መጠን የሲቪል ሰርቪሱ ጉዳይም እየራቀ ይሄዳል:: ስለዚህ በሚዲያ የሚያሞኙትን መሥሪያ ቤቶችና ኃላፊዎቻቸው ዞር ብሎ ካላየ የበለጠ እንደሚታለል የታወቀ ነውና በዚህ ረገድ የሲቪል ሰርቪስ አርበኞችን መሻት አለበት::

በጥቅሉ ግን ሲቪል ሰርቪሱ መሻሻል አለበት? አዎን መሻሻል አለበት:: ጉዳዩ ለመንግሥት ብቻ የምንተወውና መንግሥትን የምናማርርበት ዋነኛ ስልት ነው? እንዲህ የሚያደርግ ካለ ከሁሉ አስቀድሞ የአገሪቱና የመጭው ትውልድ የለየለት ጠላት ነው:: በመቀጠልም የዚህ ትውልድ ጠላት ነው:: በሦስተኛ ደረጃ ሥልጣን የያዘው የመንግሥት ጠላት ነው:: ስለዚህ የሲቪል ሰርቪሱ ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ ስለሆነ በአርበኝነት ልንረባረብበት የሚገባ ጉዳይ ነው::ወደ አገራቸው የሚመለሱ አርበኞች

በልዩ ልዩ ምክንያቶች አገራቸውን ትተው የሄዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ብዙ ነው:: እነዚህም በስደት የሚኖሩ ወገኖቻችን በልዩ ልዩ የማኅበራዊ ኑሮ፣ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ ዘርፎች ተሰማርተው እንደሚኖሩ የታወቀ ነው:: ለብዙ ዓመታት በሰው አገር በመኖራቸውም የአመለካከት ልዩነት እንደሚኖራቸው የታወቀ ነው:: ነገር ግን ቢወዱም ባይወዱም አገራቸው ኢትዮጵያ ናት:: ወደዚች አገር ለመመለስ እያሰቡ የሚሞቱ ቢኖሩም እየተመኙ የሚኖሩት ይበዛሉ:: እነዚህ ወገኖቻችን በአንዱ ወይም በሌላው ምክንያት የተዛባ አመለካከት ሊኖራቸው ይችላል:: ለምሳሌ ትምህርቱና ኢኮኖሚው ባላደገበት ሁኔታ የበለፀጉት አገሮች መንግሥታት እንደሚያደርጉት የአገራቸው መንግሥት ሊፈልጉ ይችላሉ:: በመሠረቱ መፈለጋቸው ወንጀል አይደለም:: ነገር ግን የተጠናወታቸው ስሜታዊነት የነሱንም እገዛ እንደሚሻ ከልሏቸዋል:: ጥፋት ቢኖራቸው ወይም አጥፍተዋል ቢባሉም እንኳን «አጥፍተናል፤ ነገር ግን ከወገናችን ጋር ሆነን አገራችንን ለማሳደግ የሚጠበቅብንን እንፈጽም» ወደሚል አቅጣጫ ከማዘንበል ይልቅ ልዩነቱን ወደሚያሰፋ አቅጣጫ ሲሄዱ የሚታዩበት ሁኔታ ይስተዋላል:: የሌላም አርበኝነት

ውዲቱ አገራችን የሚያስፈልጓት አርበኞች በርካታ ናቸው:: ከሁሉም በላይ ወጣት የሥራና የዕድገት አርበኛ መፍጠር ከፊታችን ተጋርጦ የሚጠይቀን ዐቢይ ተግባር ነው::ማጠቃለያ

ውድ አንባቢያን የአርበኝነትን፣ በተለይም የልማት አርበኝነትን ትርጉም ከዚህ ከተጠቀሰው ሁሉ ሰፋ አድርገን ልናየው እንችላለን:: ዋናው ቁም ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ ሰፊ የልማት ሥራዎች እየተካሄዱ ሲሆን እነዚህም ሥራዎች ዓለም አቀፍ አድናቆት የተቸራቸው ናቸው:: ችግሮች እንኳን ሊኖሩ ቢችሉ የልማቱ ትሩፋት ለእያንዳንዳችን ቢደርስም ባይደርስም በአገርና በወገን ፍቅር ስሜት በርትተን ልንሠራ ይገባል:: በእርግጥም ተደጋግሞ ሲነገር እንደሚሰማው ችግር ፈቺዎች እንጅ ችግር ፈጣሪዎች ወይም ጨለምተኞች ሆነን ልንገኝ አይገባም:: በአጭሩ ለማለት የሚቻለው ማንም የፈለገውን ቢል የልማት አርበኝነቱ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት::

ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል::

አዲስ ዓይነት... ከክፍል 2 ገጽ 7 የዞረ

Page 77: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 29 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2

ፎ ቶ ዜ ና

በተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ በሚገኘው ጁልፋር ከተባለ ኩባንያ ጋር በሽርክና የተገነባው ይህ ፋብሪካ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም፣ የጁልፋር ኩባንያ ባለቤት ሼክ ፋይሰል ቢን ሳቅር አል ቋስሚ፣ የተባበሩት ዓረብ ኢሜሬትስ የወጪ ንግድ ሚኒስትር ሉብና አልቃሲሚና ሌሎች የሁለቱም አገሮች ከፍተኛ ባለሥልጣናት በተገኙበት ጥር 29 ቀን 2005 ዓ.ም. ተመርቋል::ፎቶ/ በሪፖርተር ናሆም ተስፋዬ

Page 78: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 30 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

ፎ ቶ ዜ ና

የአራት ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈውና 45 ቤቶችን ከመኖርያ ቤት ወደ አመድነት የተለወጡበት የፒያሳው የሠራተኛ ሠፈር እሳት አደጋ ከፍተኛ ውድመት ጥር 29 ቀን 2005 ዓ.ም. ከሌሊቱ አሥር ሰዓት ደርሶበታል:: በመሀል ፒያሳ በሲኒማ አምፒር ፊት ለፊት ወደ ውስጥ በሚያስገባው አስፋልት በስተቀኝ ይገኛል:: ቃጠሎው የደረሰበት አካባቢ እንኳን በአደጋ ጊዜ በደህናውም ጊዜ በጣም ጠባብ በመሆኑ ሰዎች ተራ በተራ ነው የሚያልፉበት:: ጥንታዊ ባለ ሁለት ፎቅ እንደ ሰርቪስ የተሠራ ቤት፣ በላስቲክና በርካታ ዓመታት ያስቆጠሩ የአፈር ቤቶች ይገኙበታል:: ግቢው ውስጥ ለማደር የገቡ ሦስት ሚኒባሶችና አንድ ላዳ ታክሲ በቃጠሎው ወድመዋል:: በአጠቃላይ 4.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት እንደወደመ ሲነገር፣ ለጊዜው ከሚመለከተው አካል ትክክለኛው መረጃ አልተገኘም:: ፎቶ በታምራት ጌታቸው

Page 79: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 31 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005 ክፍል-2

TenderExhibition Center & Market Development Enterprise

seeks to procure partition materials and accessories,

and invites all eligible suppliers to participate in the

tender.

Bidder with:-

a. Renewed & appropriate Trade License and

b. VAT Registration Certificate and other relevant

documents can obtain Bid documents from the

Enterprise free of charge during office hours.

All bids should be enclosed in wax sealed envelope and

accompanied by a Bid Security Bond of Birr 10,000

(Ten Thousand) in CPO made in favor of “AACCSA-

Exhibition Center & Market Development Enterprise”

or in cash which must be delivered to the Enterprise

along with their bidding price and documents.

Bidders should present their bidding prices and

documents together in a wax sealed and duty stamped

envelopes to the enterprise on or before February

22,2013 at 2:00 p.m and insert in the bidding box

prepared for this particular tender.

The bid will be officially opened in February 22,2013

at 2:30 p.m in the presence of bidders or their legal

representatives.

The Enterprise reserves the right to accept or reject or

modify all or part of the bid.

For further information you can call 0911-21-09-99

Exhibition Center & Market Development

Enterprise

በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ በከፍተኛ ጉጉት የሚጠበቀው የ2006 ዓ.ም አዲስ

ዓመት ዋዜማ “ንግድ ትርዒትና ባዛር” ዝግጅት ለጨረታ ቀረበ!

በአዲስ ዓመት፣ በገና እና በፋሲካ ዋዜማዎች የሚዘጋጁ

“የንግድ ትርዒት፣ ባዛር እና ፌስቲቫል ዝግጅቶች በተሳታፊዎች

(Exhibitors)፣ በጐብኝዎች (Visitors) እና በአዘጋጆች

(Organisers) በየጊዜው እየተወደዱ በመምጣታቸው ፣

ኤግዚቢሽን ማዕከልም የደንበኞችን ፍላጐት ለማርካት

የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

የአዲስ ዓመት ዋዜማ የዘመን መለወጫም በመሆኑ ከፍተኛ

የግዢና የሽያጭ ሥራ የሚከናወንበት ልዩ ዓመታዊ በዓል

ነው፣ በአዝናኝነቱ እና በአዋጭነቱም ግንባር ቀደም እንደሆነ

ይታመናል፡፡

“የንግድ ትርዒት፣ ባዛር እና ፌስቲቫሉ” የሚካሄደው ለ15 ቀን

ሲሆን ነሐሴ 21 ቀን 2005 ዓ.ም ተጀምሮ ጳጉሜ 05 ቀን

2005 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡

በተለይም ለአዳዲስ ደንበኞች አስተማማኝ የምክር አገልግሎት

ስለምናቀርብ አጋጣሚውን እንዲጠቀሙበት እንጋብዛለን፡፡

ተጫራቾች በፕሮሞሽን እና ተጓዳኝ በሆኑ ሴክተሮች የተሰማሩ፣

ለዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው እና የተ.ዕ.ታ (VAT)

ተመዝጋቢ ሊሆኑ ይገባል፡፡

ዝርዝር መረጃ የያዘውን የጨረታውን ሰነድ ከየካቲት 1 ቀን

2005 ዓ.ም ጀምሮ እስከ የካቲት 20 ቀን 2005 ዓ.ም ዘወትር

በሥራ ሰዓት ሜክሲኮ ከሚገኘው ከአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ

ማህበራት ም/ቤት ዋና ፀሐፊ ቢሮ መውሰድ ይቻላል፡፡

በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ የጨረታ ሰነድ ማስገባት

የሚቻለው የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም እስከ ከጠዋቱ 3፡45

ሰዓት ድረስ ነው፡፡

ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት

የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ላይ በኤግዚቢሽን

ማዕከል ሽያጭ ክፍል በይፋ ይከፈታል፡፡

ለበለጠ መረጃ 0911-21-09-99 ላይ መደወል ይቻላል፡፡

ማዕከሉ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ

በህግ የተጠበቀ ነው፡፡

ኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት

ማስታወቂያ

Page 80: Reporter Issue 1334

www.ethiopianreporter.com

ገጽ 32 | እሑድ | የካቲት 3 ቀን 2005ክፍል-2

ማስታወቂያ