study on suitability of some fields for sugarcane production at wolenchiti expansion project of...
TRANSCRIPT
1. Study on Suitability of Some fields for SugarcaneProduction at Wolenchiti Expansion Project of Wonji ShoaSugar Estate– By Girma Abejew
ይህ ቴክኖሎጂ u¨K”Ü+ u}¨c’< Td‹ Là ¾g”¢^
›ÑÇ °Éу ¾kÚÚ G<• በSÑ–ቱ Tdቹ ¾g”¢^ ›ÑÇ
KTU[ƒ }eTT> SJ” ›KSJ“†ው” uSK¾ƒ LÃ
Á}¢[ Ø“ƒ ሲሆን፣ በጥናቱ መሰረት በማስፋፊያ ፕሮጀክቱ
ወደ 75 ሄክታር የሚጠጋ መሬት በባሃ ድንጋይ (Pumice
rock particles) የተሞላ ነው፡፡ የድንጋይ ባህሪ እና ስርጭት
ለአገዳ እድገት ተስማሚ ባለመሆኑ የሸንከራ አገዳ መቀጨጭ
ሊከሰት ችሏል፡፡
በጥናቱ ውጤት ምክንያት አስቀድሞ ባልተተከለበት የመሬቱ
ክፍል ላይ ለመሬት ዝግጅት፣ ለዘር አገዳ ተከላና አንክብካቤ፣
ለመስኖ ውሃ አሰጣጥ፣ ለመስኖ መስመር ዝርጋታ (በአዳዲስ
ማሳዎቸ)፣ ለማዳባሪያና ተያያዥ ሥራዎች ያለአግባብ ሊወጣ
የነበረ ወጪን ከብክነት መታደግ ተችሏል፡፡
2. Assessment of Factory Waste Water Quality forIrrigation: the Case of the New Wonji Shoa Sugar Factory–By Dereje Bishaw and Solomon Mulugeta
ይህ ቴክኖሎጂ ከአዲሱ የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ስኳር
በማምረት ሂደት ውስጥ የሚወጣውን የተወሰነ ውኃ ለመስኖ
እየተጠቀመበት ይገኛል፡፡ በመሆኑም ድርጅቱ ከፋብሪካ
የሚወጣውንና ለመስኖ እየተጠቀመበት ያለውን ውኃ ለመስኖ
ተስማሚነቱ የተዳሰሰበት ጥናት ነው፡፡ በጥናቱ መሰረት
ከፋብሪካ የሚወጣው ውኃ አሁን ባለበት ደረጃ ለፈሮ መስኖ
መዋል የሚችል ሲሆን፣ ይህንን ውኃ በመጠቀም ከአዋሽ ወንዝ
በሞተር የሚሳበውን ውኃ በመቀነስ የውኃ ወጪን እንዲቀንስ
ያስችላል፡፡
3. Irrigation Scheduling for Furrow Irrigated SugarcaneCrop at Welenchiti Expansion Project of Wonji Shoa SugarEstate– By Dereje Bishaw and Solomon Mulugeta
በወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ወለንጪቲ ማስፋፊያ ፕሮጀክት
ደረጃውን የጠበቀ የመስኖ ውኃ አጠጣጥ የጊዜ ሠሌዳ
ስሌለላቸው በሸንኮራ አገዳው እድገት ላይ የውኃ እጥረት
ይታያል፡፡ ይህንን ችግር ለመቅረፍ የመስኖ ውኃ አጠጣጥ የጊዜ
ሠሌዳን በአፈር አይነት፣ በሸንኮራ አገዳ የእድገት ደረጃና
በመስኖ ወራት በመከፋፈል በአዲስ መልክ ማዘጋጀት አስፈላጊ
ሆኖ በመገኘቱ ይህ ምርምር ተዘጋጅቷል፡፡ ምርምሩ
የተዘጋጀውን አዲስ የመስኖ ውኃ አጠጣጥ የጊዜ ሠሌዳ
በመጠቀምና በሸንኮራ አገዳ ላይ የውኃ እጥረት እንዳይከሰት
በማድረግ የሚጠበቀውን የሸንኮራ አገዳ ምርት ማግኘት
ያስችላል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ የውሃ ብክነት እንዳይከሰት በማድረግ በረጅም
ጊዜ ሊከሰት የሚችልን የከርሰ ምድር የውኃ መጨመር
ይከላከላል፡፡
4. Assessment and Management Options of Sugarcane Smutat Tendaho Sugar Factory – By Abiyot Lemma
ለዚህ ምርምር መነሻ የሆነው በተንዳሆ ስኳር ፋብሪካየአረማሞ በሽታ ስርጭት እየተባባሰ መምጣት ሲሆን፣ የጥናቱውጤት እንዳመለከተው የተንዳሆ አየር ንብረት(ደረቅ፣ሞቃታማና ነፋሻማ አየር) ለሸንኮራ አገዳ አረማሞ በሽታ(Sugarcane Smut disease) ዕድገትና ስርጭት አመቺመሆኑ እንዳለ ሆኖ፣ የአገዳ ዘር ዝግጅት ላይ በተለያዩ ችግሮችምክንያት በሞቀ ውሃም ሆነ ኬሚካል ባግባቡ ያልታከመ መነሻዘሮችን መጠቀም የበሽታ ዕድገትና ስርጭቱን አባብሷል፡፡ስለሆነም ቴክኖሎጂው ከዘር አገዳ ዝግጀት ጀምሮ እስከመጨረሻው ቆረጣ ድረስ መተግበር ያለባቸው ስትራቴጂክየሆኑ ዕቅዶችን እና ሥራዎችን አመላክቷል፡፡ በዚህምበአረማሞ በሽታ ምክንያት ሊወጣ ይችል የነበረ በሄክታር9996 ብር ወጪን ማዳን እንደሚቻል ታውቋል፡፡
5. Assessment of Prosopis juliflora infestation andmanagement options at Tendaho Sugar Estate – By Samuel T
ለዚህ ጥናት መነሻ የነበሩ ምክንያቶች እንደሚከተለውቀርበዋል፡-
ሀ. የፕሮሶፒስ አረም ስርጭት በሸንኮራ አገዳ ማሳዎች እናበባዶ ቦታዎች ምን እንደሚመስል የሚያሳይ መሰረታዊ መረጃንበመሰብሰብ ለወደፊት ለሚደረገው የምርምር ስራ መነሻ መረጃንለማስቀመጥ፣
ለ. የአረም ስርጭቱ ልዩነት ምክንያት እና ለወደፊት መደረግስለሚገባው ጥንቃቄ መረጃ ለማመንጨት፣
ሐ. በአካባቢው አረሙን ለመቆጣጠር ስለሚደረጉ መቆጣጠሪያዘዴዎች እና ስላላቸው ደካማ እና ጠንካራ ጎን ለመፈተሸ፣
መ. የአረሙን ጉዳት በእርሻ ስራው ላይ ለመለየት እና በገንዘብለመተመን፣
ሠ. አረሙ የሚሰጣቸውን ጥቅም በመለየት እና አረሙንጥቅም ላይ በማዋል የቁጥጥር ስትራቴጂ ለመንደፍ እና
ረ. በተሰበሰበው መረጃ ላይ በመመርኮዝ ለአረሙ የተቀናጀየአረም መቆጣጠሪያ ዘዴን በምርምር ለማፍለቅ ናቸው፡፡
ቴክኖሎጂው በሰረፀበት ወቅት በሸንኮራ አገዳ ማሳዎች ላይአረሙን ለመቆጣጠር ለሌሎች አረም ዝርያዎች ከሚደረገውቁጥጥር የተለየ ቁጥጥር ሳይደረግ አረሙን መቆጣጠር እናበዚህም እስከ 10 በመቶ የማምረቻ ወጪን መቀነስ እንደሚቻልተገልጧል፡፡
በተጨማሪም ከዚህ እንደሚከተለው የተቀመጡት የመፍትሔአቅጣጫዎች ተግባራዊ እንዲደረጉ ቀርበዋል፡-
ሀ. የሸንኮራ አገዳ ማሳዎች በኦፕሬሽን ስታንዳርድ መሰረትለማሳው መደረግ ያለበት እንክብካቤ ከተደረገ አረሙ ማሳውላይ ጎልቶ ጉዳት እንደማያደርስ ፣
ለ. ከማሳው ወጭ አረሙን ለመቆጣጠር የመንግስት እናመንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት እንዲሁም የህዝብ ከፍተኛተሳትፎ እንደሚያስፈልግ፣
ሐ. አረሙን በመቆጣጠር ሂደት ውስጥ አረሙን ከባዶመሬቶች ላይ በምናጠፋበት ግዜ በምትኩ ጠቃሚ የዕፅዋትዝርያዎችን መትከል አስፈላጊ መሆኑ ናቸው፡፡
6. Improved Sugarcane Varieties Promotion in FinchaSugar Factory- By Zinaw Dilnesaw
በዚህ በፊንጫአ ስኳር ፋብሪካ በተካሄደው የቴክኖሎጂ ሽግግር
ፎረም በአገዳ እና በስኳር ምርት ምታማነታቸው ረዘም ላለ ጊዜ
በምርምር ተፈትሸው አመርቂ ውጤት ያሳዩ አራት ዝርያዎች
እንዲሰርጹ ተደርገዋል፡፡ እነዚህ C132-81፣C86-56 ፣SPO70-
1284 እና C90-501 የተሰኙ ዝርያዎች ከዚህ ቀደም በፋብሪካው
አገዳ ልማት ረዘም ላለ ጊዜ በአገልግሎት ላይ ከቆየው B52298
ተብሎ የሚጠራ ዝርያ ጋር ሲነጻጸሩ በዓመት እንደቅደም
ተከተላቸው 16.8፣ 6፣ 4.8 እና 18 ኩንታል ተጨማሪ የስኳር
ምርት እንደሚያስገኙ ተረጋግጧል፡፡ፊንጫአ ስኳር ፋብሪካ እንዲሰርጹ ከተደረጉት ቫራይቲዎች አንዱ
C86-56 እና C132-81 ይገኙበታል
6. Improved Sugarcane Varieties Promotion in FinchaSugar Factory- By Zinaw Dilnesaw
በዚህ በፊንጫአ ስኳር ፋብሪካ በተካሄደው የቴክኖሎጂ ሽግግር
ፎረም በአገዳ እና በስኳር ምርት ምታማነታቸው ረዘም ላለ ጊዜ
በምርምር ተፈትሸው አመርቂ ውጤት ያሳዩ አራት ዝርያዎች
እንዲሰርጹ ተደርገዋል፡፡ እነዚህ C132-81፣C86-56 ፣SPO70-
1284 እና C90-501 የተሰኙ ዝርያዎች ከዚህ ቀደም በፋብሪካው
አገዳ ልማት ረዘም ላለ ጊዜ በአገልግሎት ላይ ከቆየው B52298
ተብሎ የሚጠራ ዝርያ ጋር ሲነጻጸሩ በዓመት እንደቅደም
ተከተላቸው 16.8፣ 6፣ 4.8 እና 18 ኩንታል ተጨማሪ የስኳር
ምርት እንደሚያስገኙ ተረጋግጧል፡፡ፊንጫአ ስኳር ፋብሪካ እንዲሰርጹ ከተደረጉት ቫራይቲዎች አንዱ
C86-56 እና C132-81 ይገኙበታል
6. Improved Sugarcane Varieties Promotion in FinchaSugar Factory- By Zinaw Dilnesaw
በዚህ በፊንጫአ ስኳር ፋብሪካ በተካሄደው የቴክኖሎጂ ሽግግር
ፎረም በአገዳ እና በስኳር ምርት ምታማነታቸው ረዘም ላለ ጊዜ
በምርምር ተፈትሸው አመርቂ ውጤት ያሳዩ አራት ዝርያዎች
እንዲሰርጹ ተደርገዋል፡፡ እነዚህ C132-81፣C86-56 ፣SPO70-
1284 እና C90-501 የተሰኙ ዝርያዎች ከዚህ ቀደም በፋብሪካው
አገዳ ልማት ረዘም ላለ ጊዜ በአገልግሎት ላይ ከቆየው B52298
ተብሎ የሚጠራ ዝርያ ጋር ሲነጻጸሩ በዓመት እንደቅደም
ተከተላቸው 16.8፣ 6፣ 4.8 እና 18 ኩንታል ተጨማሪ የስኳር
ምርት እንደሚያስገኙ ተረጋግጧል፡፡ፊንጫአ ስኳር ፋብሪካ እንዲሰርጹ ከተደረጉት ቫራይቲዎች አንዱ
C86-56 እና C132-81 ይገኙበታል
7. Design Improvement on Sugarcane Mill By-Pass Systemfor Tandem B of Metahara Sugar Factory – By MinaleGetachew
ይህ ቴክኖሎጂ በመተሃራ ስኳር ፋብሪካ በታንደም ቢ ላይ
ያለውን የባይ ፓስ ሲስተም በቀላሉና በጥቂት የሰው ሃይል
በመጠቀም በአምስቱም ወፍጮዎች ላይ የባይ ፓስ ፕሌቶችን
መስራትና ለሁሉም ወፍጮዎች እየተንቀሳቀሱ የሚገጠሙ ባይ
ፓሶችን መስራት ላይ ያተኮረ ነው፡፡
ቴክኖሎጂው ከመተግበሩ በፊት ሲስተሙን ለማስገባትና
ለማስወጣት በአማካይ ከሁለት እስከ አራት ሰዓታት ብክነት
/down time/ ይመዘገብ የነበረ ሲሆን፣ ቴክኖሎጀው ከተተገበረ
በኋላ (በሪፖርት ደብተራቸው ላይ ተመዝግቦ እንዳገኘነው) ከ15
እስከ 45 ደቂቃዎች ሊወርድ ችሏል፡፡ በዚህም ብዙ ሰዓትና
የሰው ሃይል ብክነት ማዳን የተቻለ ሲሆን፣ በቀጣይ ቀሪ ጥቂት
የእርማት ስራዎች ሲከናወኑ ከአምስት እስከ አስር ደቂቃዎች
እንደሚቀንስ ይታመናል፡፡
8. Assessment of sugar handling performance and alternateutilization of fine sugar– By Kassa Hundito
በዚህ ምርምር እንዲተገበሩ የቀረቡት ዝክረ ሃሳቦች በመተሃራ
ስኳር ፋብሪካ ሮቶክሎንን በሳይክሎን መተካት፣ በደቃቅ ስኳር
መውረጃ ስር ማግኔቲክ ከቸር መግጠም እና 35 ሜሽ ስክሪን
ሲቭን በ45 ሜሽ ስክሪን መቀየር የሚያስችል ነው፡፡
በተሸጋገረው ቴክኖሎጂ የእስካሁኑ አተገባበር በዓመት
ከ1,811,160.00 ብር በላይ ማዳን ተችሏል፡፡